ru
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Открыть в Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Больше
669
Подписчики
-124 часа
+37 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
"ለሰላም ፣ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ አዲስ አበባ) በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ! ‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› (ሉቃ. 1÷28-30") የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ገልፆል፤ የማዳን ስራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኳል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን! ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤ ‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡ እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ስራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሠርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሠርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት  ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡ ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5) መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡ በእግዚአብሔር  ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡ በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባኤም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡ እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡ ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡ በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤ እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባኤ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ

#እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሳን አደረሳቹ ። † "በጽዮን መለከትን ንፉ:: ጾምንም ቀድሱ:: ጉባዔውንም አውጁ:: ሕዝቡንም አከማቹ:: ማሕበሩንም ቀድሱ:: ሽማግሌዎችንም ሰብስቡ:: ሕጻናቱንና ጡት የ
#እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሳን አደረሳቹ ። † "በጽዮን መለከትን ንፉ:: ጾምንም ቀድሱ:: ጉባዔውንም አውጁ:: ሕዝቡንም አከማቹ:: ማሕበሩንም ቀድሱ:: ሽማግሌዎችንም ሰብስቡ:: ሕጻናቱንና ጡት የሚጠቡትን አከማቹ:: ሙሽራው ከእልፍኙ: ሙሽራይቱም ከጫጉላዋ ይውጡ::"          †(ኢዩ. 2:15) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

"አልረሳውም ያንን ዕለት" - እጅግ ድንቅ መዝሙር - ዘማሪ ዲ/ን ሙሉቀን ከበደ | Zemari Muluken Kebede https://youtube.com/watch?v=N1VzmJTFZg4&si=0DcF-rNMR9DvVrfJ

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም መነሻ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም መመለሻ ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም መስተንግዶን ጨምሮ እግረ መንገዳችንን እንጦ
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም መነሻ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም መመለሻ ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም መስተንግዶን ጨምሮ እግረ መንገዳችንን እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት እንሳለማለን ለበለጠ መረጃ:- 0943620923                       :- 0955252034 ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። ▭▭▭▭▭▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭

ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 27/11/2016 ዓ.ም ኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር  ብፁዕ አቡነ አብርሃም በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መ/ፖ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የባ/ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋሪያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያና የድርጅት ሐላፊዎች ፤ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሐላፊዎች አባቶች ካህናት መምህራንና ተመራቂ ተማሪዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሒዷል። በመርሐ ግብሩም የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት  ለተማሪዎች ያስተላለፉ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናውም የሥልጠናውን ዓላማና ቀጣይ ከሰልጣኞች የሚጠበቀውን ሥራ በአጭሩ ለታዳሚዎች ገለፃ አድርገዋል። ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለሰልጣኞች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር ተልዕኳውን እንድታሳካ ኃላፊነታችሁን በትጋት ፈጽሙ በማለት የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል። "ለራሳችሁ አይደላችኹም ስለዚህ፥በሥጋችኹ እግዚአብሔርን አክብሩ።" 1ቆሮ 6፥20 መነሻ በማድረግ የዕለቱን ቃለ ወንጌል ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ አብርሃም  "ቤተ ክርስቲያን ከናንተ ብዙ ትጠብቃለች በሔዳቹበት ሁሉ አገልግሎታችሁ በትዕግስትና በፍቅር ይሁን" በማለት አባታዊ ቡራኬና መመሪያ ለተመራቂ ተማሪዎች አስተላልፈው  ለተማሪዎች የምሥክር ወረቀት ሰጥተዋል። ተመራቂ ተማረዎች መሠረተ ሃይማኖት ፣ አስተዳደር፣ ክህሎትና ሥርዓተ ት/ትን በሚመለከቱ 3 ዘርፎች ከ 20 በላይ ኮርሶችን በተከታታይ ለ20 ቀናት በቀንና በማታ መርሐ ግብር የወሰዱ ሲሆን በምርቃት መርሐ ግብራቸውም ላይ አጠቃላይ ቆይታቸውን በሪፖርት መልክ እንዲሁም ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)

ልዩ መንፈሳዊ መርሐግብር እነሆ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የህፃናትና አዳጊያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ 33ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ
ልዩ መንፈሳዊ መርሐግብር እነሆ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የህፃናትና አዳጊያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ 33ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በካቴድራሉ አውደምህረት ልዩ የሆነ መርሀ ግብር ተዘጋጅቷል። ነገ ቅዳሜ ከቀኑ 10 ሰዓት እንዲሁም እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል። እርሶም የዚህ ልዩ መርሐግብር ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዛችኋል። ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። ▭▭▭▭▭▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_27_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ዕብራውያን 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤ ⁸ ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤ ⁹-¹⁰ ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው። ¹¹ ስለ እርሱም የምንናገረው ብዙ ነገር አለን፥ ጆሮቻችሁም ስለ ፈዘዙ በቃል ልንተረጕመው ጭንቅ ነው። ¹² ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም። ¹³ ወተት የሚጋት ሁሉ ሕፃን ስለ ሆነ የጽድቅን ቃል አያውቅምና፤ ¹⁴ ጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በስራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ 1ኛ ዮሐንስ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ዓመፃ ሁሉ ኃጢአት ነው፥ ሞትም የማይገባው ኃጢአት አለ። ¹⁸ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን እንዳያደርግ፥ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የተወለደው ራሱን እንዲጠብቅ ክፉውም እንዳይነካው እናውቃለን። ¹⁹ ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን። ²⁰ የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ሐዋርያት 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ እናንተ በሰቀላችሁት እግዚአብሔርም ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደኅና ሆኖ በፊታችሁ እንደ ቆመ፥ ለእናንተ ለሁላችሁ ለእስራኤልም ሕዝብ ሁሉ የታወቀ ይሁን። ¹¹ እናንተ ግንበኞች የናቃችሁት፥ የማዕዘን ራስ የሆነው ይህ ድንጋይ ነው። ¹² መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። ¹³ ጴጥሮስና ዮሐንስም በግልጥ እንደ ተናገሩ ባዩ ጊዜ፥ መጽሐፍን የማያውቁና ያልተማሩ ሰዎች እንደ ሆኑ አስተውለው አደነቁ፥ ከኢየሱስም ጋር እንደ ነበሩ አወቁአቸው፤ ¹⁴ የተፈወሰውንም ሰው ከእነርሱ ጋር ቆሞ ሲያዩ የሚመልሱትን አጡ። ¹⁵ ከሸንጎም ወደ ውጭ ይወጡ ዘንድ አዝዘው፦ በእነዚህ ሰዎች ምን እንሥራ? ¹⁶ የታወቀ ምልክት በእነርሱ እጅ እንደ ተደረገ በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ ሁሉ ተገልጦአልና፥ እንሸሽገው ዘንድ አንችልም፤ ¹⁷ ነገር ግን በሕዝቡ ዘንድ አብዝቶ እንዳይስፋፋ፥ ከእንግዲህ ወዲህ ለማንም ሰው በዚህ ስም እንዳይናገሩ እየዛትን እንዘዛቸው ብለው እርስ በርሳቸው ተማከሩ። ¹⁸ ጠርተውም በኢየሱስ ስም ፈጽመው እንዳይናገሩና እንዳያስተምሩ አዘዙአቸው። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_27_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ "ወቅዱሰ እስራኤል ንጉሥነ። ውእቱ አሚረ ተናገርኮሙ በራእይ ለደቂቅከ። ወትቤ እሬሲ ረድኤተ በላዕለ ኃይል"። መዝ 88፥18-19። "ረድኤታችን ከእግዚአብሔር ከንጉሣችንም ከእስራኤል ቅዱስ ነውና። በዚያ ጊዜ ለልጆችህ በራእይ ተናገርህ እንዲህም አልህ፦ ረድኤቴን በኃይል ላይ አኖርሁ፤ ከሕዝቤ የተመረጠውን ከፍ ከፍ አደረግሁ"። መዝ 88፥18-19። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_27_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ዮሐንስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁰ እኔና አብ አንድ ነን። ³¹ አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ። ³² ኢየሱስ፦ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው። ³³ አይሁድም፦ ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት። ³⁴ ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፦ እኔ፦ አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? ³⁵ መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥ ³⁶ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን፦ ትሳደባለህ ትሉታላችሁን? ³⁷ እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤ ³⁸ ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ። ³⁹ እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ። ⁴⁰ ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ። ⁴¹ ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው፦ ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ አሉ። ⁴² በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የአምላካችን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለቱ መታሰቢያ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

ልዩ መንፈሳዊ መርሐግብር እነሆ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የህፃናትና አዳጊያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ 33ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ
ልዩ መንፈሳዊ መርሐግብር እነሆ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የህፃናትና አዳጊያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ 33ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በካቴድራሉ አውደምህረት ልዩ የሆነ መርሀ ግብር ተዘጋጅቷል። ነገ ቅዳሜ ከቀኑ 10 ሰዓት እንዲሁም እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል። እርሶም የዚህ ልዩ መርሐግብር ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዛችኋል። ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። ▭▭▭▭▭▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭

ሐምሌ 25/2016 #ሰማእቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ "ስለአንተ ብለን ሁል ጊዜ ተገድለናል እለት እለት እንደሚታረዱ በጎች ሆነናል" መዝ.43፥22 👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት ለሰማእቱ #ቅዱስ_መርቆርዮስ የልደቱና ቅዳሴ ቤቱ መታሠቢያ አመታዊ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን 👉ወር በገባ በ25 ታላቁ ሰማእት #ቅዱስ_መርቆርዮስ መታሰቢያ በዓል ሲሆን ቅዱስ መርቆርዮስ የቀድሞ ስሙ ፒሎፓደር ሲሆን ትርጉሙም "የአብ ወዳጅ የወልድ አገልጋይ ማለት ነዉ" 👉በወጣትነቱ ከሃዲው ንጉስ ኡልያኖስ ላቆመው ጣኦት አልሰግድም ብሎ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለውን መከራ ተቀበለ በመጨረሻም ህዳር 25 ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት #ደም_ውኃና_ወተት ከአንገቱ ፈሰሰ 👉ንጉሱ በዚያዉ ዘመን ክርስቲያኖችን በጣም ያሰቃይ ነበር ቅዱስ ባስልዮስም ይገስጸዉ ነበር በዚህም ምክንያት ንጉሱ ቅዱስ ባስልዮስን አሰረዉ ጳጳሱ በታሰረበት እስር ቤት የቅዱስ #መርቆርዮስ ሥዕል ነበር 👉ቅዱስ ባስልዮስም ከሥዕሉ ስር በመሆን ፀለየ ሥዕሉም ከቦታዉ ታጣ ያ ሥዕል ወደ ዑልያኖስ ቤት ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለዉ በስዕሉ ላይ ያለዉ ጦር ጫፉ ደም ይንጠባጠብ ነበር ቅዱስ ባስልዮስም ከሀዲ ዑልያኖስን #ቅዱስ_መርቆርዮስ በሥዕሉ አማካኝነት እንደገደለዉ አዉቆ #እግዚአብሔርን አመሰገነ 👉ይህ ሰማዕት በአገራችን በስሙ በርካታ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት አሉት በተለይም ቅዱስ ላሊበላ ካነጻቸው 11 ውቅር አብያተክርስቲያናት አንዱን #ቤተ_መርቆሬዎስ ብሎ ሰይሞለታል በዚህ በሰሜን ሸዋ ደግሞ የሚገርም ገዳም አለው ካህናት በማህሌት ወረብ ሲያቀርቡ ስዕሉ ያሸበሽባል ይዘላል ይህንንም አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል በመዲናችን አዲስ አበባ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ታቦቱ አለ 👉መርቆሬዎስ ከሞተ በኋላ ፈረሱ ለሰባት ዓመት ወንጌልን አስተምሯል በኋላም አንገቱን ቆርጠው ገድለውታል እንዴት ብሎ የሚገረም የበልአምን አህያ ይጠይቃት እኛስ #ለእግዚአብሔር የሚሳነዉ ነገር የለም ብለን እንመልሳለን ዘኁልቁ.22፥28 ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አለ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነብዩን ቁጣ አገደ ይላል 2ጴጥ.2፥16 👉የሰማእቱ #ቅዱስ_መርቆርዮስ ምልጃና ፀሎት አይለየን ረድኤትና በረከቱ ይድረሰን ቃል ኪዳኑ ይጠብቀን "አሜን"

የተአምረ ማርያም መጽሐፍ በኦሮምኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ ! ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በብፁዕ አቡነ ናትናኤልና በዲ/ን እንዳለው መለሰ ወደ ኦሮምኛ የተተረጎመው ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ዛሬ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተመርቋል፡፡ መጽሐፉ በኦሮምኛ ፣ በግዕዝና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶና በማኅበረ ቅዱሳን የኤዲቶርያል አገልግሎት ተመርምሮ ለኅትመት የበቃ ሲሆን አሳታሚና አከፋፋይ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑ ተገልጿል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቤተ ክርስቲያን በቋንቋ ማገልገልንና መገልገልን ከሐዋርያት ተቀበላ እያስቀጠለች መሆኗን ገልጸው እኛም የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያንን መሠረት ያደረገውን መጽሐፍ  እንደ አቅማችን ተርጉመን ለኅትመት አብቅተናል ብለዋል፡፡ ብዙ ከማውራት ትንሽ መሥራት የተሻለ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ይህንን አድርገናል፣ በቀጣይ ደግሞ የትርጉም ሥራዎችን ከዚህ በበለጠ ለመሥራት መጻሕፍትን እየመረጥንና እየተመካከርን ነው ብለዋል፡፡ ቋንቋ ተግባብተን የምንለወጥበትና የምንስማማበት እንጅ መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት አይደለም ሲሉም አጽዕኖት ሰጥተዋል። ብፁዕነታቸው የኦሮምኛ  ቋንቋ ተናጋሪዎችን መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን አክለዋል፡፡ እኛ ይህንን የትርጉም ሥራ ለመሥራት ያነሳሳን ምክንያት የቤተ ክርስትያንን ተደራሽነት በመረዳት ምእመናን በቋንቋቸው እንዲገለገሉ በማሰብ ነው ያሉት የመጽሐፉ ተርጓሚ ዲ/ን እንዳለው ቋንቋን ምክንያት በማድረግ በአጉል ትርክት የተጠቁ ሁሉ ሊማሩበት የሚገባ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ  በበኩላቸው ማኅበረ ቅዱሳን መንፈሳዊ አገልግሎትን ለማስፋፋት መጻሕፍትን በተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎም ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን መሥራቱንና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ፀሐይሽ አትጠልቅም መንፈሳዊ ማኅበር ለብፁዓን አባቶችና መጽሐፉ ለሚያስፈልጋቸው አብያተ ክርስቲያናት እንዲደርስ 100 መጻሕፍትን ወስደዋል። በዕለቱ በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ፣ ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይና የማኅበራት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን በጎፋ ዞን ለተጎዱ ወገኖች የ11.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎ
+3
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን በጎፋ ዞን ለተጎዱ ወገኖች የ11.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ11.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የስብክተ ወንጌልና ሀዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብጹእ አቡነ ማርቆስ ጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በመገኘት ድጋፉን አስረክበዋል፡፡ በደረሰው አደጋ ቤተ-ክርስቲያኗ ማዘኗን የገለጹት አቡነ ማርቆስ፤ ለተጎጂ ወገኖችም መጽናናትን እንደሚመኙ ተናግረዋል፡፡ አሁን እንደተቋም ቤተ-ክርስቲያኗ ካደረገችው ድጋፍ በተጓዳኝ ምዕመኑን በማስተባበርም በቀጣይ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ ድጋፊን የተረከቡት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳግማዊ አየለ፤ ቤተ-ክርስቲያኗ አደጋው ከደረሰ ጀምሮ ተጎጂዎችን ከማጽናናት ጀምሮ ባደረገችው ያልተቋረጠ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ©ebc

"አልረሳውም ያንን ዕለት" - እጅግ ድንቅ መዝሙር - ዘማሪ ዲ/ን ሙሉቀን ከበደ | Zemari Muluken Kebede https://youtube.com/watch?v=N1VzmJTFZg4&si=0DcF-rNMR9DvVrfJ

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_24_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ 2ኛ ቆሮ 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ በመልእክቴ ያሳዘንኋችሁ ብሆን እንኳ አልጸጸትም፤ የተጸጸትሁ ብሆን እንኳ፥ ያ መልእክት ጥቂት ጊዜ ብቻ እንዳሳዘናችሁ አያለሁና አሁን ለንስሐ ስላዘናችሁ ደስ ብሎኛል እንጂ ስላዘናችሁ አይደለም፤ ⁹ በምንም ከእኛ የተነሣ እንዳትጎዱ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አዝናችኋልና። ¹⁰ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ 1ኛ ጴጥሮስ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ እኔ፥ ከእነርሱ ጋር ሽማግሌ የክርስቶስም መከራ ምስክር ደግሞም ሊገለጥ ካለው ክብር ተካፋይ የሆንሁ፥ በመካከላቸው ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤ ² በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሳይሆን፥ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ በመመኘት ሳይሆን ጐብኙት፤ ³ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማኅበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ፤ ⁴ የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ። ⁵ እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ሐዋርያት 16 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁵ በነጋም ጊዜ ገዢዎቹ፦ እነዚያን ሰዎች ፍታቸው ብለው ሎሌዎቻቸውን ላኩ። ³⁶ የወኅኒውም ጠባቂ፦ ትፈቱ ዘንድ ገዢዎቹ ልከዋል፤ እንግዲህ አሁን ወጥታችሁ በሰላም ሂዱ ብሎ ይህን ቃል ለጳውሎስ ነገረው። ³⁷ ጳውሎስ ግን፦ እኛ የሮሜ ሰዎች ስንሆን ያለ ፍርድ በሕዝብ ፊት ደብድበው በወኅኒ ጣሉን፤ አሁንም በስውር ይጥሉናልን? አይሆንም ራሳቸው ግን መጥተው ያውጡን አላቸው። ³⁸ ሎሌዎቹም ይህን ነገር ለገዢዎች ነገሩ። የሮሜ ሰዎችም እንደ ሆኑ በሰሙ ጊዜ ፈሩ፤ ³⁹ መጥተውም ማለዱአቸው፥ አውጥተውም ከከተማ ይወጡ ዘንድ ለመኑአቸው። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_24_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ "ማእምርየ ወዐውቅየ። ዘኅቡረ አስተጠዓምከ ሊተ መባልዕተ። ወነሐውር ቤተ እግዚአብሔር በአሐዱ ልብ"። መዝ 54፥13-14። "አንተ ግን፥ እኩያዬ ሰው፥ ባልንጀራዬና የልቤ ወዳጅ፤ መብልን ከእኔ ጋር በአንድነት ያጣፈጥህ፤ በአንድ ልብ በእግዚአብሔር ቤት ተራመድን"። መዝ 54፥13-14። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሐምሌ_24_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ማቴዎስ 19 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ እነሆም፥ አንድ ሰው ቀርቦ፦ መምህር ሆይ፥ የዘላለምን ሕይወት እንዳገኝ ምን መልካም ነገር ላድርግ? አለው። ¹⁷ እርሱም፦ ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው። ¹⁸ እርሱም፦ የትኞችን? አለው። ኢየሱስም፦ አትግደል፥ አታመንዝር፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ ¹⁹ አባትህንና እናትህን አክብር፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው። ²⁰ ጐበዙም፦ ይህንማ ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ፥ ደግሞስ የሚጐድለኝ ምንድር ነው? አለው። ²¹ ኢየሱስም፦ ፍጹም ልትሆን ብትወድ፥ ሂድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፥ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ሠለስቱ_ምዕት_ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ኖብ የዕረፍት በዓል፣ የሊቀ ጳጳስ ስምዖን የዕረፍት በዓልና የአቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

"ትፈልገኛለህ" - ገጣሚ ክብሮም (ኬቢሻ) | New Ethiopian Orthodox Poem by Kebisha - ኬቢ... https://youtube.com/watch?v=T1ihXl1L7iE&si=yRK_XKVsRdWCx8dx

ጉባኤ ዘጸአት ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን
+3
ጉባኤ ዘጸአት ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። ▭▭▭▭▭▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭

በ2024 የዓለም ኦሎምፒክ ስፓርታዊ ውድድር መክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ የተካሄደውን አስነዋሪ ትዕይንት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ “ይእዜ ኀሥረ ክብሮሙ ወተኀፍረ ገጾሙ ወተቃወመቶሙ ኀጢአቶሙ ከመ ኀጢአተ ሰዶም ወገሞራ አስተርአየት ወተዐውቀት ላዕሌሆሙ፤ አሌ ላ ለነፍሶሙ እስመ መከሩ እኩየ ምክረ ላዕለ ነፍሶሙ፡- ዛሬ ክብራቸው ተዋረደ፣ የፊታቸውም ዕፍረት ይመሰክርባቸዋል ኀጢአታቸው እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ኀጢአት ተቃወመቻቸው በላያቸውም ተገልጣ ታወቀች፡፡ ክፉ ምክርንም መክረዋልና ለነፍሳቸው ወዮላት፡፡ ኢሳ.3 ፥ 9”   የ2024 የዓለም ኦሎምፒክ ስፓርታዊ ውድድርን በማስመልከት ባለፈው ዓርብ በአውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር July 26 በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በተካሄደበት ወቅት በመላው ክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ክብር የሚሠጠውን ምስጢረ ቊርባንን ያቀለለ፣ የተመሳስይ ጾታ ጋብቻን፣  የግብረ ሰዶማውያንን እኩይ ተግባር በወገንተኛነት የተደገፈ ትርኢት ማሳየታቸውን በዓለም ዜና ማሰራጫ ተመልክተናል።       በየዐራት ዓመቱ በሚከናወነው የዓለም ኦሎምፒክ ስፖርታዊ ውድድር የመክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ የቀረበው የረከሰ ድርጊት ሲታይ በተቀደሰው ምሥጢረ ቊርባን ላይ የተፈጸመ የድፍረት ኃጢአት ነው፡፡ በተጨማሪም የሃይማኖትን ነጻነት የሚጋፋ፣ ጾታ የሚለውጡ ሰዎችን የሚያበረታታና በአጠቃላይ በክርስትና ሃይማኖትና በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ቀጥተኛ ጥቃት ስለሆነና ከሰለጠነው ዓለም የማይጠበቅ፣ የሌሎችን የእምነት የባህልና የማኅበራዊ ዕሴት ማክበር ልዩ ቦታ በሚሰጠው የኦሎምፒክ ስፖርታዊ ጨዋነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር፣ በቅዱሳት መጻሕፍት፣ በሰው ልጅ ሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው፡፡       በመሆኑም አንዱ የሌላውን የእምነትና የአምልኮ ነጻነት በማክበር እንዲኖር በሃይማኖት ቀኖናት ብቻ ሳይሆን በዓለማችን ላይ ባሉት ሀገራት የሰብአዊ መብትና የእምነት ሕግጋት የተደነገገ ሆኖ ሳለ ከኦሎምፒክ ስፖርት ጋር በማይገናኝ ሁኔታ በውድድሩ መክፈቻ ትዕይንት የተፈጸመው አስነዋሪ ተግባር ሃይማኖታችንን የሚጋፋ፣ መንፈሳዊ እሴቶቻችንን የሚያጠፋ ክብረ ነክና ሊወገዝ የሚገባው ሰይጣናዊ ድርጊት በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ አውግዞታል፡፡ የዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ ኮሚቴና ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላትም ይህንን በመላው ክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ የቀሰቀሰውን ጸረ-ሃይማኖት የሆነ አስነዋሪ ድርጊት በመኮነን የአምኮልን መብትና ነጻነት እንዲያስከብሩ፣ ድርጊቱን በግልጽ እንዲቃወሙ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡                 ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም.                     አዲስ አበባ ኢትዮጵያ