ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Открыть в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Больше669
Подписчики
-224 часа
+57 дней
+130 дней
Архив постов
❤️አባ ጥጦስ❤️
አንድ ወንድም አባ ጥጦስን "እንዴት ልቤን መጠበቅ እችላለኹ?" ሲል ጠየቀው ።
አባ ጥጦስም "አፋችንና ሆዳችን ክፍት ከኾነ እንዴት ልባችንን መጠበቅ ይቻለናል?" ሲል መለሰለት።
💡💡💡💡💡💡💡💡💡💡💡💡
ኹለት ከመናገር አንድ ማድመጥ ይላሉ አበው። አንደበታችንን ሳንገታ ቅድስና የለም!
መልካም ቀን
+3
በምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት የሚሰራው መንበረ ጵጵስና ሕንጻ design ይህን ይመስላል።
ከጥር 17 እስከ ጥር 25/2017 ዓ.ም ድረስ ይህን ከላይ የምትመለከቱትን መንበረ ጵጵስና ህንጻ ለመስራት ታላቅ የሆነ የገቢ ማስገኛ ባዛር ተዘጋጅቷል።
በዚህ መንፈሳዊ ባዛር ላይ በአርሲ እና በአካባቢው ያሉ ምዕመናን እንዲገኙ ሼር በማድረግ፤ በተለያዩ ማሕበራዊ ሚዲያዎች ላይም በመልቀቅ ኦርቶዶክሳዊ የልጅነት ድርሻችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
«ወንድምህን አትናቀው»
ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን? እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው። እህትህን አትናቃት። ምንም ይሁን ምን ሰው አትናቅ። ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከሆነ ክርስቶስን እየሰደብከዉ እንደሆን አስተውል።
"እንዴት?" ያልከኝ እንደሆንም ይህ የምትንቀው ወንድምህ የከደርስቶስ ሕዋስ (ብልት) ኾኗል። የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እሱን ናቅኸው ማለት ክርቶስን ናቅኸው ማለት ነው።
ወንድምህን የምትንቅ ከሆነም በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት፣ እራቁቱን ከሰቀሉት፣ ሐሞትንና ከርቤን ቀላቅለው ከሰጡት፣ በፊቱ ላይም ከተፉበት ሰዎች በምንም አትተናነስም። ስለዘህ ወንድምህን ከመናቅ ተጠንቀቅ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሰናይ ሰንበት!
✨️️️️✨️️️️✨️️️️💐💐💐✨️️️️✨️️️️✨️️️️💐💐💐✨️️️️✨️️️️✨️️️️
✨️️️️💐💐የፍቅር ሥራ ይህች ናት✨️️️️💐💐
፧፧፧፧፧፧፧፧፧
✨️️️️✨️️️️💐
ባልንጀራውን የሚረዳውን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ይረዳዋል፡፡ ለወንድሙ የሚነቀፍበትን ስም የሚያወጣውን ፈታሒ በርትዕ እግዚአብሔር እንዲሰደብ ያደርገዋል፡፡ ክፉ ስለ ሠራ ወንድሙን በቤቱ ለብቻው ሆኖ የሚመክረው ሰው ግን በምክሩ ዐዋቂ ይሆናል፡፡ ወንድሙን በዐደባባይ የነቀፈ ግን ኀዘን ያጸናበታል፡፡ ከሰው ተለይቶ ወንድሙን የሚመክር ሰው እነሆ የፍቅሩን ብዛት ያስረዳል፤ በባልንጀሮቹ ፊት የሚነቅፈው ግን የቅናቱን ጽናት ያስረዳል፣ የምቀኝነቱን ጽናት አስረዳ፡፡
✨️️️️✨️️️️💐
ወዳጁን ተሠውሮ የሚመክር ሰው ብልህ ባለመድኃኒት ነው:: ያ እንዳዳነው መክሮ አስተምሮ ያድነዋልና፡፡ ወንድሙን በብዙ ሰው ፊት የሚያመሰግነው ሰው እሱ እውነተኛ ጠላቱ ነው፣ በውዳሴ ከንቱ ይጎዳ ብሎ ነውና።
✨️️️️✨️️️️💐
ኀዘን ያለበት የርሕራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለት ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው፡፡ ወደ ክብር የሚያደርስ ረብህ ጥቅም ያግኝ ብሎ የሚመክር፣ የሚያስተምር በፍቅር ይመክረዋል፣ ያስተምረዋል፡፡ ቂም በቀል የሚሻ ሰው ፍቅር የለውም፡፡ አንድም እበቀለዋለሁ ብሎ የሚመክር ከፍቅር የተለየ ነው፡፡
✨️️️️✨️️️️💐
ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር በፍቅር ይመክራል፣ ያስተምራል፣ እበቀላለሁ ብሎ ያይደል፡፡ እሱስ በምሳሌው የተፈጠረው ሰውን ለማዳን ይገሥጻል፡፡ አንድ ጊዜስ እንኳን ቂም አይዝም፣ መዓትን አያዘጋጅም፡፡ የፍቅር ሥራ ይህች ናት፣ በቅንነት ትገኛለች፡፡ ቂም ለመያዝ እበቀላለሁ አትልም፣ በፍቅር ሰውን መናገር ነው።
✨️️️️✨️️️️💐
ብልህ የሚሆን ቅን ሰው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይመስለዋል፡፡ ሰውን ክፉ ስላደረገ እበቀለዋለሁ ብሎ አይገሥጸውም፣ ሊመክረው ወዶ ነው እንጂ ሌሎችንም ለማስፈራት ነው እንጂ። ተግሣጽስ በፍቅር ካልሆነ ተግሣጽ አይባልም፡፡ በጎ ነገር ያደርግልኛል ብሎ በጎ የሚሠራ ኋላ ፈጥኖ ይተዋል፡፡
✨️️️️✨️️️️💐
✍ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ
✨️️️️✨️️️️✨️️️️💐💐💐✨️️️️✨️️️️✨️️️️💐💐💐✨️️️️✨️️️️✨️️️️
እንኳን ለጌታችን እና ለመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ነገ ማለትም ሀሙስ (1/05/2017 ዓ.ም) በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የቀዳሜ ሰማዕት የሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ይከበራል።
ሁላችንም የአሰላ ምዕመናን በመገኘት አብረን እናክብር ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
+4
ፎቶ :- 29/2017 ዓ.ም
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት የጌታችን እና የመድኃኒታችን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን ልደት በዓል በማስመልከት ከ500 በላይ ነድያንን ምገባ አካሄደ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
