ru
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Открыть в Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Больше
669
Подписчики
-124 часа
+37 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
ጥቅምት 27 በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል
+9
ጥቅምት 27 በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል

ለመንፈሳዊ ትምሕርት ፈላጊዎች በሙሉ!!!

ለመንፈሳዊ ትምሕርት ፈላጊዎች በሙሉ!!!
ለመንፈሳዊ ትምሕርት ፈላጊዎች በሙሉ!!!

"የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ ! " " ሕሊናቸው የክርስቶስን ሕማም ከማሰብ አቁሞ የማያውቀው አባ መብዓ ጽዮን መድኃኔዓለምን ፦ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ፡፡
+1
 "የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ ! " " ሕሊናቸው የክርስቶስን ሕማም ከማሰብ አቁሞ የማያውቀው አባ መብዓ ጽዮን መድኃኔዓለምን ፦ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ፡፡ ስለ ራሴ ፈጽሞ አለቅስ ዘንድ" ሲሉ ለመኑት፡፡ ጌታም ፦ "መከራ መስቀሌን ለማየት ትፈቅዳለህን? " ብሎ ጠየቃቸው። ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮንም ፦ "አዎ ! አይ ዘንድ እወዳለሁ" አሉት። ያን ጊዜም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እጆቹና እግሮቹ ተቸንክረው ታየ ፣ በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል ደፍቶ ነበር፡፡ እንዲህ ሆኖ በሮም አደባባይ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንደታየው ታያቸው። ይህን የመድኃኔዓለም መከራ የተመለከቱ የጻድቁ ዓይኖችም ፈዝዘው እስኪጠፉ ድረስ ትኩስ እንባዎችን ሲያዘንቡ ኖረዋል። "ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ"  [ ኃይሌና መጠጊያዬ እርሱ ጌታዬ ነው።]

ይሕን ያውቁ ኖሯል? *" አቡነ መብዓ ጽዮን "*+ =>ሃገራችን ኢትዮዽያ እጅግ በርካታ ቅዱሳንን ስታፈራ አንዳንዶቹ ደግሞ የተለዩ ናቸው:: ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮን በ15ኛው መቶ ክ/ዘመን በሽዋ (ሻሞ
ይሕን ያውቁ ኖሯል? *" አቡነ መብዓ ጽዮን "*+ =>ሃገራችን ኢትዮዽያ እጅግ በርካታ ቅዱሳንን ስታፈራ አንዳንዶቹ ደግሞ የተለዩ ናቸው:: ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮን በ15ኛው መቶ ክ/ዘመን በሽዋ (ሻሞ) አካባቢ የተነሱ ጻድቅ ናቸው:: ገና ከልጅነታቸው የእመቤታችንና የጌታችን ፍቅር የሞላባቸው ነበሩ:: +በ3 ዓመታቸው ከእንግዳ የወሰዷት ስዕለ አድኅኖ ተለይታቸው አታውቅም ነበር:: በወጣትነታቸው ጊዜም ብሉያት ሐዲሳትን: ቅኔንም ጨምሮ ተምረው: ከቤተሰባቸው አስፈቅደው በምናኔ ገዳም ገቡ:: ከዚያ በሁዋላ ያለውን ገድላቸውን ማን ችሎ ይዘረዝረዋል! +በተለይ ዐርብ ዐርብ የጌታን 13 ሕማማት ለማዘከር ሲቀበሉት የኖሩት መከራ እጅግ ብዙ ነው:: ድንጋይ ተሸክመው እንባና ላባቸው እየተንጠፈጠፈ ይሰግዳሉ:: በድንጋይ ደረትና ጀርባቸውን ይደቃሉ:: ራሳቸውን ይገርፋሉ:: በዋንጫ ሐሞት (ኮሶ) ሞልተው ይጠጣሉ:: +ከዚህ ሁሉ በሁዋላ ወር በገባ በ27 ስለ መድኃኔዓለም ጠላ ጠምቀው: ንፍሮ ነክረው ወደ ገበያ ይወጡና ይዘክሩ ነበር:: ከዝክሩ የነካ ሁሉ ይፈወስ ነበር:: ከእንባ ብዛት ዓይናቸው ቢጠፋ ድንግል ማርያም መጥታ ብርሃናዊ ዓይንን ሰጠቻቸው:: ስለዚህም "ተክለ ማርያም (በትረ ማርያም)" ይባላሉ:: +ጌታችንም ስለ ፍቅራቸው በአምሳለ ሕጻን ይገለጽላቸው: እርሳቸውም አቅፈው ይስሙት ነበር:: ጻድቁ ተናግረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ ተጋድለው ጌታ በዚህ ቀን ነፍሳትን ከሲዖል እንዲያወጡበት ስልጣንን ሰጣቸው:: አባታችን ቅዱሱና ጻድቁ መብዓ ጽዮን ከብዙ ትሩፋት በሁዋላ ዐርፈዋል::    ጥቅምት 27 ዓመታዊ በዓላቸው ነው። በረከታቸው ትድረሰን!!!

2 ቀን ቀረው Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እናርግ። የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
2 ቀን ቀረው Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እናርግ። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

በ1 ሰዉ መመለስ በሰማይ ታላቅ ደስታ ከሆነ በምድር እንዴት አይሆንም?! 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ሁሌም ቢሆን የልባችንን ስላም ከሚያፀኑት ነገሮች መካከል አንዱ የነፍስ
+4
በ1 ሰዉ መመለስ በሰማይ ታላቅ ደስታ ከሆነ በምድር እንዴት አይሆንም?! 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ሁሌም ቢሆን የልባችንን ስላም ከሚያፀኑት ነገሮች መካከል አንዱ የነፍስ ድህነት ተግባር ነው። የፀጋው ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የነበረው የቀድሞው ፓስተር ናትናኤል ቢተው ከአብራከ መንፈስቅዱስ ከቅድስት ቤተክርስትያን እናትነት እንደ አዲስ ተወልዶ አንዲት ወደሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ሀይማኖት ልጅ ሆኖ ተቀላቅሏል። የእግዚአብሔር ስም የተመሠገነ ይሁን። ካደ ከሚል ዜና ይልቅ አመነ የሚለው ዜና መስማትን የሚመስል ደንቅ ፍስሃ ምን አለ?! እግዚአብሔር በቤቱ ያፅናው!! ሁላችንም በፍቅር እንጂ በፀብ እና በስድብ ወንድሞችን ወደ ቤተክርስቲያን ለመመለስ አንሞክር።የተመለሱትም በፍቅር ስርዓተ ቤተክርስቲያን እናስተምር። ስለ ጥረታችን ሁሉ ዋጋችን በሰማይ ነው። ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!! ይሄ ዜና ለሁሉ አድርሱ ያኔ የሰማዩ ደስታ በምድር ይደገማል። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

ዝጎራ ገፅ 315 " የምሥጢር ሙዳይ ሁን እንጂ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን ። ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸውና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፣ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን ። ለዕውቀት ትጋ ። በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስክን እንደ አዋቂ አትቁጠር ። በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል ። ሥራ ስትሠራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይም ብሠራ የሚጠቀመው ሌላ ነው በሚል ተስፋ ቢስ ሆነህ ሳይሆን ዘላለም እንደምትኖር ያክል በመትጋት ነው ። ትጋት ጥሩ ነው ። ችኮላህ ግን ውጤት አያመጣም ፣ በችኮላ መሥራትና በፍጥነት መሥራት የተለያዩ ናቸው ። ርኩሰት የዕውቀትና ስልጣኔ መገለጫ አይደለምና ማንነትንና ሰብዓዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ አድርግ ። " " እናም በየዕለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ። ያለጸጸት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ ፤ ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውንና ለማከናዎን የምትመርጠውን ዐይነት ሕይወት ለመኖር ሞክር ። .... "

🌸🌸🌸🌸🌸🌸 🌸 ካነበብነው  🌸 🌸🌸🌸🌸🌸🌸 " አምላክ ከሚጠላው ከሁሉም ኃጢአት ዕወቅ እንደሚበልጥ ሰውን ማጣላት " 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 ጣፋጭ ጥበብ ገጽ ፪፻፴፭ ቁጥር ፩ ሽ ፰፻፭ 🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸 ❤ ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ ❤ እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች ናቸው፥ ሰባትንም ነፍሱ አጥብቃ ትጸየፈዋለች፤ ፩) ትዕቢተኛ ዓይን ፥ ፪) ሐሰተኛ ምላስ ፥ ፫) ንጹሕን ደም የምታፈስስ እጅ፥ ፬) ክፉ አሳብን የሚያበቅል ልብ ፥ ፭) ወደ ክፉ የምትሮጥ እግር ፥ ፮) በሐሰት የሚናገር ሐሰተኛ ምስክር ፥ ፯) በወንድማማች መካከልም ጠብን የሚዘራ። ምሳሌ ፮ ÷ ፲፮ - ፲፱

ፕሮፌሰሩ መኖክሴ *** የመጠሪያ ስማቸው አባ ሃይለ ገብርኤል ይባላል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መኖክሴ ናቸው። ዓለም ከዘረጋችው እውቀት አፍሰው የያዙ በሁለት ጎን በእውቀት ሰይፍ
+2
ፕሮፌሰሩ መኖክሴ *** የመጠሪያ ስማቸው አባ ሃይለ ገብርኤል ይባላል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መኖክሴ ናቸው። ዓለም ከዘረጋችው እውቀት አፍሰው የያዙ በሁለት ጎን በእውቀት ሰይፍ ተስለው የሾሉ አባት ናቸው ። ከ20 ዓመታትን በላይ በውጪ ሀገር በመቆዬት ከInformation studies እስከ international development ከeducational adminstration and leadership እስከ counceling psychology ድረስ በመማር እና ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ እስከ ፕሮፌስርነት ማዕረግ ደርሰዋል። አሁን ላይ በቅድስት ሥላሴ መንፈሣዊ ኮሌጅ እያገለገሉ ይገኛል። ዓለምን መናቅ ማለት ይህ ነው።ዓለምን ከስስ ብልቷ እስከ ምትኩራራበት ክብሯ ድረስ ዘልቆ ደርሶ እና አውቆ  ምንም እንደማይጠቅም በመኖክሴ ቆብ ንቆ መግለጥ ማለት ይህ ነው ። እግዚአብሔር ይመስገን!!!

ቤተክርስቲያን ስንገባ ምን ማድረግ አለብን? ሥርዓት የሃይማኖት መገለጫ እንደመሆኑ ከመሠረቱ የምናምንባቸውን ተግባራዊ የምናደርግበት መንገድ ነው። ጸሎት ፣ ቅዳሴ፣ ቁርባን፣ ጾም፣ ስግደት እንዲሁም ሌ
ቤተክርስቲያን ስንገባ ምን ማድረግ አለብን? ሥርዓት የሃይማኖት መገለጫ እንደመሆኑ ከመሠረቱ የምናምንባቸውን ተግባራዊ የምናደርግበት መንገድ ነው።  ጸሎት ፣ ቅዳሴ፣ ቁርባን፣ ጾም፣ ስግደት እንዲሁም ሌሎች የሃይማኖት ምሥጢራትን ለመፈጸም በማመን ብቻ የሚያበቁ ሳይሆኑ የአፈጻጸምና አተገባበር መንገድ  (ሥርዓት) ያስፈልጋቸዋልና፡፡ ቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ከመግባታችን በፊት "ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ምሳአል ወምስጋድ ወምሥተሠርይ ኃጢአት" ይህም ማለት  "ልመና እና ስግደት የሚቀርብብሽ፣ የኃጢአት ሥርየት የሚገኝብሽ የኢየሩሳሌም ሰማያዊት አምሳያ የምትሆኚ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሆይ ሰላምታ ላንቺ ይገባሻል።" ብለን መግባት አለብን።     በአሁኑ ጊዜ ሥርዓቱን እየተገበርን አይደለም ለምሳሌ: የቅዳሴ ሥርዓትን አቋርጦ  መግባትና መውጣት፣ በትምህርተ ወንጌል በቅዳሴም እንዱሁም በሌሎች የጸሎት ሰዓታት ላይ ማውራትና ሌሎችንም አላስፈላጊ ተግባራት ማስተዋል ከጀመርን ቆየን። ሥርዓቱን ማወቅ ሲገባ ግን  የመተላለፋችን ምክንያት አንድም ሥርዓቱን ባለማወቅ ስለሆነ እያንዳንዱ ምእመን መጠበቅ ያለበትን ሥርዓት ማወቅና መተግበር ይጠበቅበታል። Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እናርግ። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

2⃣1⃣ እናቴ ♥️🕯️ ድንግል_ሆይ ! በበደል ምሳር የማትቆረጪ ከኃጢኣት አውሎ ነፋስ የተነሣ የማትነዋወጪ ዘወትር ፍጹም የምትለመልሚ በዘመኑ ኹሉ የምታፈሪ በወሮች ኹሉ የምትለቀሚ ከእጽዋት ኹሉ ይል
2⃣1⃣ እናቴ ♥️🕯️ ድንግል_ሆይ ! በበደል ምሳር የማትቆረጪ ከኃጢኣት አውሎ ነፋስ የተነሣ የማትነዋወጪ  ዘወትር ፍጹም የምትለመልሚ  በዘመኑ ኹሉ የምታፈሪ በወሮች ኹሉ የምትለቀሚ  ከእጽዋት ኹሉ ይልቅ የምታምሪ እመቤቴ ማርያም ኾይ የተባረክሽ ዕፅ ነሽ።" /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/" 🌹የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን አማላጅነቷ አይለየን አሜን ፫

🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲 አቤቱ የሚበድሉኝን በድላቸው÷ የሚዋጉንኝም ተዋጋቸው። ጥሩርና ጋሻ ያዝ እኔንም ለመርዳት ተነሦ ሰይፍህን ምዘዝ የሚያሳድዱኝንም መንገዳቸውን ዝጋ ነፍሴን መድኃኒ
🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲 አቤቱ የሚበድሉኝን በድላቸው÷ የሚዋጉንኝም ተዋጋቸው። ጥሩርና ጋሻ ያዝ እኔንም ለመርዳት ተነሦ ሰይፍህን ምዘዝ የሚያሳድዱኝንም መንገዳቸውን ዝጋ ነፍሴን መድኃኒትሽ እኔ ነኝ በላት።             መዝ ፴፭፥፩-፫ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

አንድን በክፉ ምግባር የተያዘን ሰው ወደ መልካም ነገር ልትመልሰው ብትወድድ መጀመርያ ሰላሙን እንዲያገኝ አድርገው፡፡ በፍቅር ቃል ከፍ ከፍ አድርገው። እንዲህ ያለን ሰው ከክፉ ስራው እንዲመለስ ለማድረግ ከዚህ የተሻለ ዘዴ የለምና። ሰው በተግባር የሚያደርገው ፍቅር ሰዎችን የመለወጥ ፍጹም ሀይል አለውና። ቀጥለህ በፍቅር አንድ ሁለት ቃልን ንገረው፣ በቁጣ አትንገረው። በእርሱ ላይ አንዳች የጠላትነት ስሜት አታሳይ። ፍቅር ሰዎችን ለመለወጥ መንገዱን እርሱ ያውቅበታል። ብቻ እንተ እድሉን ስጠው። የፍቅር ሰውም ሁን። (መክስምያኖስ ባህታዊ ዘሶርያ - የበረሃ ፈርጦች)

የቀዳሜ ሰማዕት ፣ የሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ አመታዊ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
+9
የቀዳሜ ሰማዕት ፣ የሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ አመታዊ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።