ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Открыть в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Больше671
Подписчики
+324 часа
+77 дней
+430 дней
Архив постов
✨ ✨✨🍂✨✨🍂✨✨🍂✨ ✨✨🍂
🍂 "ነገር ኹሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን!" 🍂
አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን። የሚያስፈልገንና የማይጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው።"
አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ረሀብና ጥማት፣ ኅዘንና ትካዜ፣ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሜ እንደ ኾነ አድርገን እናስባለን ነገር ግን ይህን የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚ ላይኾን ይችላል።
እንደ ራሳችን ሐሳብ ሳይኾን እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ስንጓዝ ግን ነገር ኹሉ ለበጎ ነው። ነገር ኹሉ ሲባልም በእኛ እይታ በጎ ነው የምንለው ብቻ አይደለም፡ ክፉ ነው የምንለውም ጭምር እንጂ። እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ሲሆን ማግኘትም፣ ማጣትም፣ ጤንነትም፣ በሽታም ለበጎ ነው።
እግዚአብሔር ለእኛ መልካም የሚያደርግልን በጎ ነው ብለን በምናስበው ነገር ብቻ አይደለም። እጅግም ክፉና አስቸጋሪ መስለው ከሚታዩን ኹኔታዎችም ለእኛ ለልጆቹ እጅግ የሚደንቅ በጎ ነገርን ማድረግ ይችልበታል።
✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ✨
✨ ✨✨🍂✨✨🍂✨✨🍂✨ ✨✨🍂
+++እማሆይ ሲንቅለጢቃ እንዲህ አሉ...+++
"ወደ እግዚአብሔር ለሚጓዙ በውጣኔ ጊዜ ብዙ ተጋድሎ እና ብዙ ስቃይ ይኖራል። በኋላ ግን የማያልቅ ደስታ ነው። ልክ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው። በመጀመሪያ በጢሱ ስለሚሰቃይ ያለቅሳል። በኋላ ግን የእሳቱን ሙቀትና ብርሃን በሰላም ያገኛል። መጽሐፍ 'አምላካችን የሚባላ እሳት ነው' (ዕብራ. 12:24) ይላልና። እኛም በውስጣችን መለኮታዊውን እሳት በዕንባና ተግቶ በመሥራት እናቀጣጥለው።"
(ምንጭ - በበረሓው ጉያ ውስጥ ፣ ዲ. ዳንኤል ክብረት ፣ ገጽ 86)
" እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። "
(ትንቢተ ኢሳይያስ 41:10)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
፲፬ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ የቃለ ጉባኤ ማጠቃለያ እና የጋራ የውሳኔ ሐሳብ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ፲፬ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ግንቦት 30 እና ሰኔ 1/ 2017 ዓ.ም ከየአህጉረ ስብከቱ የተወከሉ የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አባላት፣ የዐዲስ አበባ ሀ/ስብከት አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሔዷል። በመሆኑም በጉባኤው ከቀረቡ ዓመታዊ ሪፖርቶች፣ ተዘጋጅተው ከቀረቡ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከየአህጉረ ስብከት ከቀረቡ አስተያየቶች እና ከጉባኤው ተሳታፊዎች ከተነሡ የውይይት ሐሳቦች ግብዓት በመነሣት ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡
1.በጠቅላላ ጉባኤው የቀረበውን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና የአህጉረ ስብከት አንድነቶች የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የተሰጡ የሥራ አቅጣጫዎችን ጠቅላላ ጉባኤው ተቀብሎ ያጸደቀ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች የ5 ዓመት መሪ ዕቅድ አፈጻጸም በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጉባኤው ወስኗል።
2.በቅዱስ ሲኖዶስ የጸደቀው መሪ ዕቅድን በተመለከተ በትኩረት የምንከታተለውና የብዙ ምሁራን ጊዜ፣ ዕውቀትና ጉልበት የፈሰሰበት ሥራ ወደ ተፈለገው ውጤት እንዳይመጣ የሚደረገው የማሰናከል ሥራ በእጅጉ ያሳዘነን ከመሆኑም ባሻገር እናት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመኑን የዋጀ ስልታዊ አካሔድ እንዳትከተል አሉታዊ ተጽዕኖ እና ከፍተኛ ሥጋት አሳድሯል። የመሪ ዕቅድ ትግበራውን በተያዘበት አግባብ ማፋጠን፣ የሊቃውንቱ፣ የካህናት የምእመናን የሰ/ት/ቤት አባላትና ባለድርሻ አካላትን ሚና በሕግ ማውጣት ሥራ ላይ ከፍ እንዲል በአጽንዖት እንጠይቃለን።
3.በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በቃለ ዐዋዲ የተደነገገው የምእመናን፣ የካህናትና የሰንበት ት/ቤቶች ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ሊኖራቸው የሚገባ የሰበካ ጉባኤ ሱታፌ በጽኑዕ እንዲተገበር እንዲሁም የሰ/ት/ቤት አባላት በጊዜ በጉልበትና በዕውቀት ከሚሰጡት የጎላ አስተዋጽዖ አንጻር ውክልናችን በቁጥር ከፍ እንዲል አበክረን እንጠይቃለን።
4.ልዩ ልዩ የአስተዳደርና የቀኖና ጥሰት እየተፈጸመ የቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነቷ እንዲሸረሸር የሚደረጉ ድርጊቶችን በጽኑዕ እንቃወማለን። የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና እንዲከበር፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዲጸና፣ መለያየት እንዲወገድ ፣በዚህም የተፈጠሩ ልዩነቶች ተቀራርቦ በመነጋገርና የበደለ ክሶ፤ ያጠፋ በቀኖና ታርሞ እንዲስተካከሉ፣ በሀገር ሰላምና አንድነት ላይም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሚናዋን እንድትወጣ እንጠይቃለን።
5.በአብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው የሀብት ሥርጭት ፍትሐዊነት መጉደል ቤተ ክርስቲያን ከገጠር ወደ ከተማ እየተሰደደች መሆኗ በግልጽ የሚታይ በመሆኑ ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት የአጥቢያ ዐቢይ ጉባኤን በማደራጀት ወደ ሥራ እንዲገባ እና በተደጋጋሚ እንደሚነሣው የፋይናንስ አስተዳደሩን የተማከለ የሚደረግበት ሥርዓት እንዲዘረጋ እንጠይቃለን።
6. አብዛኛው የቤተ ክርስቲያኗ ሀብት የሚመነጨው አጥቢያ ላይ በመሆኑ አስፈጻሚ አካላት ገንዘብ መልቀምና መጠበቅ ላይ በሀብት ምደባም ይሁን ለአስተዳደር ሥራ ብቻ ትኩረት በማድረጋቸው ሕፃናትን የማሠማራት፣ ወጣቶችንና ምእመናንን የመጠበቅ ሥራው በአብዛኛው ተዘንግቷል፣ ስለዚኽ ይኽ ጉዳይ በአስቸኳይ እንዲስተካከል እንጠይቃለን።
7.የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር የበጀት ዕጥረት ከፍተኛ በመኾኑ፣ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስፈጸም፣ የመጽሐፍ ስርጭቱንና ሌሎችንም ዘርፈ ብዙ የሰንበት ትምህርት ቤት ሥራዎች ከፍተኛ እንቅፋት በመፍጠሩ መፍትሔ እንዲሰጠው እንጠይቃለን።
8.ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የጠነከረ የኢኮኖሚ አቅምና ማኅበራዊ መስተጋብር ፈጥረው ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁና ለሀገርም ረብ ያለው ነገር ማበርከት እንዲችሉ የማድረግ ሚናዋን ዘንግታለች፣ ስለዚህም ጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በቂ ሀብት በመመደብና ተገቢ አመራር በመስጠት በአባላት ሁለንተናዊ ሕይወት ዙሪያ አስፈላጊ ለውጥ ማምጣት እንዲቻል ጥረት ይደረግ ዘንድ በአጽንዖት እንጠይቃለን።
9.የሰንበት ት/ቤቶችም ኾነ ሌሎች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን የቅርብ ክትትል የሚፈልግ ኾኖ እያለ ሀገረ ስብከቶቻቸውን በዓመት ለውስን ጊዜያት አንዳንዴም አንዴ ብቻ በሚጎበኙ ሊቃነ ጳጳሳት የተነሣ አገልግሎቶች እየታወኩ ይገኛሉ፤ ስለዚህ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ ሀገረ ስብከቶቻቸውን በተገቢው መልኩ እንዲከታተሉ የሚመለከተው አካል ተገቢ ቁጥጥር እንዲያደርግ በአጽንዖት እንጠይቃለን።
10.የሰንበት ት/ቤቶች ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነቶች ተወካዮች ተሰባስበው የሚመክሩበት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚወያዩበት ቀጣይ ሥራዎች የሚተልሙበት ጉባኤ ነው። ይኽ ጉባኤ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ከቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ከሌሎች የሥራ ሓላፊዎች ጋር የሚወያዩበትም ጭምር ነው። ይኹን እንጂ ይኽ ጉዳይ በትክክል ተፈጻሚ እየሆነ አይደለም። ስለዚኽ ይኽ ጉባኤ ከዚህ በኋላ የሚካሔዱ ጠቅላላ ጉባኤያት በቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎተ ቡራኬ ተከፍቶ፤ በቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ ምዕዳን የሚዘጋ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትም ተገኝተው የሚመሯቸው እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች እና የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች ተገኝተው የሰ/ት/ቤቶችን ጉዳይ በሓላፊነት የሚከታተሉባቸው እንዲኾኑ በአጽንዖት እንጠይቃለን።
11.. በዚኸ ጉባኤ ላይ በተለያዩ ምከንያቶች ያልተገኙ የአህጉረ ስብከት ተወካዮች እንዳሉ ቢታወቅም በተለይ ግን በትግራይ ከልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት ጋር በተፈጠረዉ እጅግ አሳዛኝ መለያየት የተነሣ የክልሉ አህጉረ ስብከት ተወካይ ወንድሞች እና እኅቶች ባለመገኘታቸዉ ጉባኤው ከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶታል። ከዚህም በላይ ችግሩ ወደ ምእመናን እየሰፋ መሔዱ ጉባኤውን በእጅጉ አሳስቦታል፡፡ በ13ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ አበክረን፣ ከወንበራችን በመነሣት በልመናና በልጅነት መንፈስ መፍትሔ እንዲያገኝ ብንጠይቅም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ባለማየታችንና ይኸ መለያየት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ሔዶ በአንዲቷ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከፍተኛ አደጋና የማይጠገን ስብራት እያደረሰ በመሆኑ ልዩነቶችን አስወግዶ በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አግባብ የክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት ወደ መዋቅራቸው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ይመለሱ ዘንድ፤ በእኛ በኩል የተቻለንን ኹሉ እንደምናደርግ ቃል በመግባት አሁንም ችግሩን ለመፍታትና እርቀ ሰላሙን ለማምጣት ከፍተኛዉን ድርሻ ሊወጡ የሚችሉት ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን እንደኾኑ እናምናለን፡፡ ይኽንኑ ለመፈጸም ቅዱስነትዎ ቃል ይገቡልን ዘንድ የቤተ ክርስቲያን ልደት ተብሎ በሚታወቀው በዛሬው በዓለ ጰራቅሊጦስ ስም ልክ እንደ አምናው ኹሉ ከመቀመጫችን በመነሣት በታላቅ አከብሮት እና ትሕትና እንጠይቃለን።
12.እነዚህ የ14ኛው ሀገር ዐቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የጋራ የውሳኔ ሐሳብ በቀጣይ የሲኖዶስ ስብሰባ አጀንዳዎች እንዲሆኑ አበክረን እንጠይቃለን።
ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
የሰንበት ት/ቤት ጥያቄ በሚኒሻና በደንብ አስከባሪ አይቆምም
በአደባባይ በዓውደ ምህረት አገልግሎት በውስጥ አስተዳደር ሚዛን በማስጠበቅ በትምህርተ ሐይማኖት ያነበበ እምነቱን የሚያውቅ ትውልድ በመገንባት የዚህ ሰልፈኛ ትውልድ ጥያቄው አይቆምም።አስተምሩን ያለ እናገልግል ያለ ሰንበት ት/ቤት አስተዳደራዊ ጉዳዬች ይስተካከሉ ያለ ሰንበት ት/ቤት ጥያቄ በህግ አስከባሪ ሐይል ጥያቄው አይቆምም።የሰንበት ት/ቤት ጥያቄ በሚኒሻና በደንብ አስከባሪ አይቆምም
ምክንያቱም ጥያቄያችን በመንፈስ ቅዱስ የምትመራዋ ቤተ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስ በመረጣቸው አገልጋዮች ትመራ ነው?
በአደባባይ በዓውደ ምህረት አገልግሎት በውስጥ አስተዳደር ሚዛን በማስጠበቅ ትውልዱ ትምህርተ ሐይማኖት ያነበበ በሚገባ ያወቀ እምነቱን የሚያውቅ ትውልድ በመገንባት ረጅም ዘመናትን ያሳለፈ የክርስቶስ ፍቅር በልቡ ዘልቆ ገብቶ በተግባር በየዕለት ተዕለት ህይወቱ የሚተገብር ይህ ሰልፈኛ ትውልድ ጥያቄው የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር ሃሳብ ይመራ ይስተዳደር ነው።
🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱
ጰራቅሊጦስ፦ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኃጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጉምን ይሰጣል መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት።
"ዐቢየ ተስፋ ዘአስፈዎሙ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ እስእሎ ለአቡየ ይፈኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጰራቅሊጦስ።"
ትርጉም፡-
ታላቅ ተስፋ ያደረገላቸው ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን አባቴን እለምነዋለኍ እውነት መንፈስን ይልክላችኋል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።
"ወበ፶ ዕለት ፈነወ ሎሙ መንፈሰ ቅዱሰ ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐዉርት።"
ትርጉም፦
በሃምሳውም ቀን በእሳት አምሳል መንፈስ ቅዱስን ሰደደላቸው በአገሩ ኹሉ ቋንቋ ተናገሩ።
የቅዳሴ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ።
🍃🍂🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂
ፍትህ ለፍኖተ ወንጌል
Ani baratu dilbataati...
Dilbataa hanga dilbataatti baratu.
Ragaa maqaa isaa kabaja isaaf faarfatu.
Waaqeffachuudha hojiin koo barsiisuudha ogummaan koo.
Karaa dhiphaadhaan wangeela hojiin koo.
Isa sodaachuu fi jaalachuudha ogummaan koo.
Kafaltii kooti kennaa isaatiin marfamuun.
Jecha isaan yoo natti dubatu sagalee isaa yoomun dhaga,uu.
Gammaduun fedha akka daa,immanii.
Maqdasiin jiraadha baay,ina arjummaa isaatinii.
Hanga bara baraatti .
isa waliinin jiraadha araara isaatinii.
Walitti qabamuun ayihuudotaa mariin isaanii.
Nan sodaachisu gumgumuun isaanii
Sodaachuisuun aramaawii nan rifachiisu.
Rukuttaan roomaawii nan ajaa,ibsiisu.
Sodaan philaaxoosii nan dinqisisu
Fariisawiin kamuu jaalala isaatirraa adda nan baasu.
Wanti tokkoyyuu isarraa gargar nan fageessu.
Kakuu haaraa kan naaf seene qaraaniyoo gubbaatti.
Iddoo naaf qophaa,e kanan qabu mootummaa isaatti.
Tolaan gooftaa tokko kanan tajaajilu.
Ilma waaqayyoo mootummaa isaa kanan dhaalu
Ani baratu dilbataati...
Sirumaayyuu Finoota wangeelii !
ሰንበት ተማሪነኝ...
ከሰንበት እስከ ሰንበት ተማሪ
የስሙ ምስክር ለክብሩ ዘማሪ
ያምልኮነው ግብሬ ስብከትነው ሞያዬ፣
በጠባቧ መንገድ ወንጌል ነው ስራዬ
እርሱን በመፍራትና በመውደድ ጥበብ
ደም ወዜነው በፀጋው መከበብ
ሲናገረኝ ቃሉ ድምፁን ስሰማ፣
እንደ ህፃናቱ መቦረቅ የምሻ፣
በቸርነቱ ብዛት በመቅደሱ ያለው፣
ዘላለም ከእርሱ ጋር በምህረት ኖራለው።
የአይሁድ ሸንጎ ጉባኤ ምክራቸው፣
አያስፈራኝም ማጉረምረማቸው።
አያስደነግጠኝ ያረማዊው ዛቻ፣
አያስደንቀኝም የሮማዊው ጡጫ፣
ከቶ አለገረምም በጲላጦስ ፍራቻ።
ማንም ፈሪሳዊ አይለየኝ ከፍቅሩ
አይነጥለኝም ምንም ነገር ከእርሱ
ቀራንዮ ሀዲስ ኪዳን የገባልኝ፣
በመንግስቱ የተዘጋጀ ስፍራ ያለኝ፣
በጎ ፈቃደኛ አንዱን ጌታ አገልጋይ፤
የንጉስ ልጅ ወራሽ ነኝ ሰማይ።
.....ሊያዉም የፍኖተ ወንጌል !
‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም፡፡ የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል››
ቅዱስ ሚናስ
ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን?
ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን
ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥
ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።
ወደ ሮሜ ሰዎች 8 :35- 39
ቤተ ክርስቲያንን አንተውም ከቶ
ቤተ ክርስቲያንን አንተውም ከቶ
የሰጠንን አምላክ በደሙ መስርቶ
የሰጠንን ጌታ በመስቀሉ ሞቶ
የአምላካችንን ቤት አንተውም ከቶ/×2/ ❴አዝ❵
አዝ
ሁሉንም በሁሉ ለሚሞላው ጌታ
ሙሽራየነች ቤቱ ተሰኝታ
በክብር በሞገስ በፀጋ ተሞልታ
ደምቃ ትኖራለች ከአለም አብርታ(2)
አዝ
ዳቢሎስ ቢጨርስ ቀስቶቹን በሙሉ
ወጥመድ ቢዘረጋ በጉዟችን ሁሉ
እንሻገራለን የአምላክን ስም ጠርተን
አንዳች አይነካንም እሱን ተጠግተን(2)
አዝ
በስሙ መሰብሰብ በስሙ መስራት
ስለ ስሙ መኖር በስሙ መሞት
ጠላት ዳቢሎስን ምን ባያስደስት
ይህ ነው ክርስትና ይሄነው ህይወት
አዝ
ከትውልድ ለትውልድ የምናስረክበው
ለልጅ ልጅ አውርሰን ደስ የምንሰኘው
አይደል ብርና ወርቅ አይደል ሌላ ሀብት
ሀይማኖት ነው የኛ ርስዕት ጉልት
✨ ✨✨🍂✨✨🍂✨✨🍂✨ ✨✨🍂
✨በበጎነት መጽናት✨
ማር ወግሪስ እንዲህ ይላል፦ "ዳግመኛም ስማኝ ልንገርህ! ለዘለዓለም ላንተ ይብስብሃልና ባደርክበት ኹሉ ቃልህን አትለውጥ። በሰዎች መካከል ጥልን አትዝራ፤ አነዋወርህ ኹሉ በሰላም ይኹን፤ ወደ ልቡናህም ቍጣን አታስገባ፤ ወንድምህ የበደለህን ከቶ አታስብ። የቍጡ ሰው ድካሙ ኹሉ በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ ፈጥኖ ያልፋልና። ቂምን በልቡናው የሚያኖር ሰው የሰይጣን ደቀ መዝሙሩ ነው፤ የዘለዓለም ሕይወትንም አያያትም። ማንንም ማንን አትማ፤ ከማንም ጋር አትከራከር፤ የባልጀራህን ንብረት አትመኝ የሌላውንም አትቀማ።
✨✨🍂
ሐሜተኛ ሰው የእግዚአብሔር ጠላቱ ነው። በጠላትህ ውድቀትና ሞት ደስ አይበልህ፤ ባዘኑት ላይ አትሣለቅ፤ ለዕውሩ መሰናክል አታኑርበት። ስትጸልይ ለመቀመጥ አትቸኩል፤ ለጸሎት ጽሙድ ኾነህ በቆምክበት ቦታ ኹሉ አትነቃነቅ፤ በመካነ ጸሎትህ ላይ አዘውትረህ ቆመህ ተገኝ። ለለመነህ ኹሉ ስጥ፤ ከሌለህ ደግሞ እግዚአብሔር ይስጥህ ካለው ያድርስህ ብለህ በለዘበ ቃል ተናገር። የምትሠራውን ሥራ ኹሉ ፊት አይተህ አድልተህ አትሥራ። የደረሰብህን ኹሉ እግዚአብሔርን አመስግነህ ተቀበል። ይህንን ያደረግህ እንደ ኾነ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት አንተ በእውነት ፍጹም ነህ። እኔስ በእውነት የእግዚአብሔርን ጥበብ አደንቃለሁ።" እንዲል። (ገብረ ኪዳን ግርማ (አባ፣ የአራቱ ጉባኤያት የምስክር መምህር)፣ መጽሐፈ ወግሪስ፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 51)።
የሕይወት መርሐችን ከላይ በተገለጸው መሠረት ቢኾን በበጎ መጽናት እንችላለን። ክፉ ነገር በሕሊናች ውስጥ በመጣ ጊዜ ወዲያው አስወግደን ብናስወጣው እና ሕሊናችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ኹል ጊዜ ብናስቀምጥ፥ በዚያም ቃል ብንመሰጥበት ሕይወታችን የተስተካከለ ይኾናል። ድንገት ስሜታዊ ኾነን ወደ ክፉ ልንሳብ ስንል ራሳችንን የምንቆጣጠርበት የእግዚአብሔር ቃል ውስጣችን ሊኖር ይገባል። በእርግጥም የሕይወት መርሐችንን በቃለ እግዚአብሔር እያደረግን ስንሄድ ስሜታችን በራሱ በቃለ እግዚአብሔር እየተገራ ይሄዳል። ውስጣችንም በቃለ እግዚአብሔር መመራትን እንደ ግዴታ መቀበል ይጀምራል። እንዲህ ሲኾን ብንጣላ ወዲያው ይቅር እንባባላለን፥ ቢበድሉን እንታገሳለን፥ ቢሰድቡን ስድብ የሚገባን ኃጥእ እንደ ኾን አድርገን እንቀበላለን፣ ቢንቁንም የክፉ ሥራችን ውጤት መኾኑን አምነን ያለተቃውሞ እንቀበላለን። እንዲህ በበጎ እየጸናን ስንሄድ የሚረብሸን ነገር በእኛ ላይ ኃይሉን እያጣ ይሄዳል፤ ሕይወታችንም በፍጹም ሰላምና ዕረፍት ይመላል።
✨✨🍂
እንግዲህ ምክንያታዊ ነኝ ብለን ከምናስበው አጸፋዊ መልስ ኹሉ እየራቅን እንሄዳለን። እንዲህ ያደረግኹት እንዲህ ስላደረገችኝ/ገኝ ነው እያሉ ከመናገር ኹሉ ነጻ እንወጣለን። በሕይወታችን የሚገጥሙንን ችግር የምንላቸውን ነገሮች ኹሉ የመጋፈጥና የማሸነፍ ብርታታችን ታላቅ ይኾናል። የብዙ ዓመታት ሕማም ቢኾን፣ ወይም የገንዘብ እጦት ችግር ቢኾን፣ ወይም ከሰዎች ዘንድ ፍቅር አጣኹኝ ብሎ የማሰብ ፈተናም ቢኾን እንሻገረዋለን። መጀመሪያ መስተካከል ያለበት አስተሳሰብ እና ነገሮችን የምንረዳበት መንገድ ነው። ሲቀጥልም የመኖር ትርጒሙና ዓላማው ግልጽ ኾኖ ሊገባን ያስፈልጋል። ይህ በትክክል ሲገባን ያን መፈጸም ዋና ዓላማችን እየኾነ ይመጣል። ስለዚህ ሰይጣን ሊጥለንና ጥቅም አልባ ሊያደርገን የሚፈጽምብን ጥቃት ኹሉ ይከሽፋል። በበጎነት ጽናታችንም ድል ይነሣል። ስለዚህ ስንኖር ለምንድን ነው የምኖረው? እንዴትስ እንድኖር ነው ፈጣሪ የሚፈልገው? ፈጣሪስ እንደሚፈልገው መኖር ያልቻልኩት ለምንድን ነው? ለመኾኑ በበጎነት ጸንቼ እንዳልኖር የሚከለክለኝ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ለራሴ እየጠየኩ ሕይወቴን እያስተካከልኹኝ ልኖር ይገባኛል። በምን መመሪያ እንዳንል ከላይ ማር ወግሪስ ያስቀመጠልን ድንቅ የሕይወት መመሪያ አለልን።
🖋ዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው
📝ርቱዕ ሐልዮ
✨ ✨✨🍂✨✨🍂✨✨🍂✨ ✨✨🍂
