ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Открыть в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Больше669
Подписчики
+124 часа
+37 дней
-330 дней
Архив постов
✨✨✨🍁✨✨✨
✨አላወቁትም ነበር✨
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በሃያ አምስተኛው ቀን ደቀ መዛሙርቱን በገሊላ ባሕር ዳርቻ አገኛቸው።
አስቀድሞ እሱ ቢያውቃቸውም እነሱ ያወቁት ዘግይተው ነው። “ጌታ እኮ ነው” ዮሐ. 21፥7 ብሎ ጌታ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ እስኪናገር ድረስ ማንም ያወቀው አልነበረም።
በአጠገባቸው ቆሞ አላወቁትም፤
“ልጆች ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን?” ሲላቸውም አላወቁትም፤ “የለንም” ብለው መለሱለት።
“መረባችሁን በመርከቡ በስተቀኝ በኩል ጣሉት ታገኙማላችሁ” አላቸው፤ ስምዖን ጴጥሮስ እና ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ለቃሉታዝዘው መረባቸውን ሲጥሉ ጌታ መሆኑን አውቀውት አይደለም፤ በባሕር አጠገብ ስላገኙት ዓሣ የማጥመድ ልምድ ያለው ሰው መስሏቸው ነበር እንጂ።
✨✨🍁
ለሚያውቃቸው ጌታ ሳያውቁት ታዘዙለት፤ በባሕር ውስጥ ያለውን የሚያውቅ ጌታ በባሕር ውስጥ ያሉ ዓሣዎችን በደቀ መዛሙርቱ መረብ እንዲገቡ አዘዛቸው።
ዮናስ ወደ ባሕር በተጣለ ጊዜ የሚውጠው ታላቅ ዓሣ ያሰናዳ እርሱ ነው፤ ዛሬም የደቀ መዛሙርቱን መረብ የሚሞላ ዓሣ በባሕር ውስጥ ያሰናዳ እርሱ ነው።
ያኔ ባሕር በቃሉ የተገሠጸችለት ማቴ. 8፥23 ዛሬም ዓሣ የገበረችለት እርሱ ነው። ይህ እስኪሆን ድረስ ደቀመዛሙርቱ አላወቁትም ነበር።
ሌሊቱን ሙሉ ባዶ የነበረው መረብ በአንድ ጊዜ በዓሣ ተሞላ፤ ስቦ ማውጣት ተሳናቸው። በዚህ ጊዜ ነው ደቀ መዛሙርቱ ጌታ መሆኑን መነጋገር የጀመሩት። መልኩን አይተው ባያውቁትም ሥራውን አይተው አወቁት።
✨✨🍁
ከባሕሩ ዳርቻ ሲቆም ከገሊላ ሰዎች እንደ አንዱ ሆኖ ነበርና በምን ያውቁታል?
ባሕሩ ሲታዘዝለት ግን ከገሊላ ሰዎች ተለየባቸው።
“አንዳች የሚበላ አላችሁን?” ብሎ ሲጠይቃቸው ከተራቡ ሰዎች እንደአንዱ መስሏቸው ነበር፤ የተራበውን መረባቸውን በአንድ ቃል ሲሞላላቸው ግን ጌታ መሆኑን አወቁት።
መረብ የለውም፤ ነገር ግን መረብ ላላችቸው ሰዎች መረብ መጣልን የሚያስተምር ሆኖ ቢያገኙት አወቁት።
ዓሣ ሲያጠምድ አላዩትም፤ ነገር ግን ዓሣ ለሚያጠምዱ ሰዎች ዓሣ ማጥመድን ሲያስተምር ሲሰሙት አመኑበት።
“በስተቀኝ በኩል ጣሉት ታገኙማላችሁ” ሲላቸው እስኪ ካገኘህ አንተሞክር “እኛስ ሌሊቱን ሙሉ ደከምን ያገኘነው ምንም የለም” ያለው የለም።
“ባሕሩን የምናውቀው እኛ ነን አንተ ዓሣ ያለበትን እንዴት ታውቃለህ?” አላሉትም። ለማያውቁት ታዘዙለት፤ ከመካከላቸው ላልነበረው፤ ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ቀና ሲሉ ከባሕሩ ዳርቻ ቆሞ ለተመለከቱት ሰው ቃል እሺ በጄ ብለው መረባቸውን ጣሉለት።
ቃሉን መስማታቸው የቃሉን ባለቤት ወደ ማወቅ አደረሳቸው። እሱም የነገራቸው የሚያውቀውን እንጂ የገመተውን አልነበረምና መረባቸውን በጣሉ ቅጽበት ከሚያስፈልጋቸው በላይ የተትረፈረፈ ስጦታን ሰጣቸው።
ጴጥሮስና ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ዓሣ ለማጥመድ የመረጡት ጊዜ ዓሣ አጥማጆች የሚመርጡት ጊዜ ነው፤ ብዙ ጊዜ ዓሣዎች ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ጊዜ ሙቀት የሌለበትን ጊዜ ስለሚመርጡ ነው። ነገር ግን ክርስቶስ የመጣበትም ሰዓት ሲነጋ ስለመጣ ሊመረጥ የሚችል ሰዓት ነበር፤ የፀሐይ ሙቀት ገና በስሱ ምድርን እየተቆጣጠረ የነበረበት ጊዜ ነበርና። ይኽ ሰዓት የሌሊቱ ድካማቸው ውጤት የሚያስገኝበት ጊዜ ቢሆንም ስላጡት ነገር በመጨነቅ ላይ ስለነበሩ ስለሚያገኙት ነገር ተስፋ በልባቸው አልነበራቸውም።
✨✨🍁
መረባቸው ብቻ ሳይሆን ልባቸውም ባዶ ነው።
የደቀ መዛሙርቱ ታሪክ መንገዱን የሚለውጠው ከዚያ ሰዓት ጀምሮ ነው፤ የታሪክ መጀመሪያህ እግዚአብሔርን በማወቅ የሚጀምር ከሆነ የተለወጠውን ታሪክህን ሊያበላሽ የሚችል ምንም ነገር የለም። ያለፈውን ሌሊት የሚያስረሳ ዘመን ይመጣል፤ ባዶ መረብ ይዞ መመላለስ የሚያቆምበት ሰዓት ይደርሳል፤ ያሰብነውን ብቻ ሳይሆን ያላሰብነውንም ሊሰጠን መድኃኔ ዓለም ወደ እኛ ይመጣል።
አስቀድሞ ራሱን አይገልጥም፤ በዚህ ዓለም እንዳሉ አጭበርባሪዎችም ከስጦታው አስቀድሞ የምናገኘውን እያሰብን በማይሆን ተስፋ ሆዳችንን አይሞላም። እንዲያውም ምንም እንደሌለን እያወቀ “የሚበላአላችሁን?” የሚል ምስኪን ሰው ሊመስለን ይችላል። ያስተዋለ ሰው ብቻ የሚያገኛት በረከቱን መታዘዝ ስንጀምር ብቻ መቀበል እንጀምራለን።መታዘዝ እንጀምር፤ የጠየቅነውን እንቀበላለን። ታሪክ የሚለወጠው በእግዚአብሔር ቃል ስንኖር ነው። በታንኳችን በስተቀኝ በኩል የጣልነው መረብ በመለኮታዊ ስልጣን የምትተዳደር ነፍስ ምሳሌ ነው፤ ነፍሳችንን ለመለኮታዊ ፈቃዱ እናስገዛ፤ ያንጊዜ ለውጡ በሕይወታችን ይጀምራል። 📝ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ ✨✨✨🍁✨✨✨
♥ መድኃኔዓለም ♥
💠«መድኃኔዓለም ማለት ዓለምን ያዳነ የዓለም መድኃኒት ማለት ነው።ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀደመ ክብሩ መለሰው።ምን ዓይነት ፍቅር ነው????? ወንድሜ/እህቴ አስባችሁታል ግን ስለእኛ ብሎ እኛን ለማዳን ብሎኮ ነው የተሰቀለው።ራቁትን መሰቀል ምን ያህል አሳፋሪ ነገር እንደሆነ እናውቀዋለን።ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ ራቁትን መሰቀልን ናቀው። በፈጠራቸው ፍጥረታት ተተፋበት።እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት እየቻለ እርሱ ግን በፍቅር እያየ የማያውቁትን አያውቁምና አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር። ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድቡት አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም ሲታበዩበት ሁሉ እርሱ ግን በትሕትና ያያቸው ነበር።ታድያ እኛ ደግሞ ራሳችንን ለማዳን ሰዎች ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩብን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀመዝሙር እንባላለን። በ5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያምና ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ።አንተም በመስቀሉ ስር ለመገኘት ከፈለግህ ትዕግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።
።
መድኃኔዓለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።
"የወንድማማች መዋደድ ይኑር። እንግዶችን መቀበል አትርሱ ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።"
ዕብ 13÷4
"እርስ በእርሳችን መፋቀር ይገባናል ይህች ፍቅር ደክመን የምንሰራውን ስራ ያለ ድካም እንድንሰራው ታደርጋለች እና።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በጥንታዊው በአሰላ ደ/መ/ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እየተከበረ ይገኛል።
እንኳን ለሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ
ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኅበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሀረድዎ ወገመድዎ ወዘረው ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኅበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግስተ ክብር ወረሰ፡፡
✨✨✨🍁✨✨✨
✨የእኔ ቤት ይቀርባል ✨
አንዲት እናት ቁጭ ብላ ለልጇ መጽሐፍ ቅዱስ ታነብላታለች። ይህ የዘወትር ተግባራቸው ነበር። እናት ካነበበች በኋላ ለልጇ ‘እስቲ አሁን የሰማሽውን በራስሽ አገላለጽ ንገሪኝ’ የማለት ልማድ ነበራት። ከእለታት በአንዱ ቀን ከኦሪት ዘፍጥረት እያነበበች እያለች የጻድቁ ሄኖክ ታሪክ ጋር ደረሰች። “ሄኖክም የኖረበት ዘመን ሁሉ ሦስት መቶ ስድሳ አምስት ዓመት ሆነ። ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” (ዘፍ 5፡23-24) የሚለውን ካነበበች በኋላ ‘እስቲ ይህንን በራስሽ አገላለጽ ንገሪኝ’ ብላ እድሉን ለልጇ ሰጠቻት።
ልጇም እንዲህ በማለት በራሷ መንገድ ገለጸችው።
✨✨🍁
“የውልሽ እናቴ… ሄኖክ ከእግዚአብሔር ጋር ኖረ፤ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ይሄድ ነበር። በጣም ወዳጆች ነበሩ። አንዳቸው ለሌላቸው ምስጢራቸውን ይናገሩ ነበር። ለብዙ ዘመን ተነጋገሩ። ቀናት ወደ ወራት፥ ወራት ወደ ዓመታት ተቀየሩ። እንዲህ እያሉ ለሦስት መቶ ስድሳ አምስት ዓመት አብረው እየተጓዙ ተነጋገሩ። አንድ ቀን ሄኖክ ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገረ እያለ፥ ቆም አለና፦ “የተወደድክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ቀኑ በጣም ገፋ፥ እየመሸ ነው። እስቲ ወደ እኔ ቤት ጎራ እንበልና በዚያ እንቀመጥ።” አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ በማለት መለሰ፦ “ልጄ ሄኖክ ሆይ፥ ለሦስት መቶ ስድሳ አምስት ዓመታት ተነጋግረናል፤ አብረንም ተጉዘናል። አሁን ከአንተ ቤት ይልቅ ለእኔ ቤት ቀርበናልና፤ ለምን ከእኔ ጋር አብረኸኝ አትመጣም? ወዳጄ ሄኖክ ሆይ፥ ወደ እኔ ቤት ና። መላእክቱ ሳይቀር ሊያዩህ እጅግ ጓጉተዋልና።” አለው። ሄኖክም ከእግዚአብሔር ጋር ተስማማ፥ “አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፥ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” (ዘፍ 5፡24)
✨✨🍁
የአይሁድ ሊቃውንት የዳዊትን መዝሙር ሲተረጉሙ የሰው ልጅ ንቁ እንቅስቃሴ በመቆም፥ በመቀመጥ፥ በመራመድ መጠቃለል ይችላል ይላሉ። ቅዱስ ዳዊትም በመጀመሪያ መዝሙሩ ሦስቱንም ጠቅሶ 'በክፉቸች ምክር አትሂዱ'፥ 'በኃጢአተኞች መንገድ አትቁሙ'፥ 'በዋዘኞች መንገድ አትቀመጡ' እያለ ይመክረናል። የሚያስመሰግነውን መንገድም ‘በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል’ (መዝ 1፡2) የሚባልለት ሰው መሆን እንደሆነ ይነግረናል። በእግዚአብሔር ሕግ ደስ መሰኘት ከእግዚአብሔር ጋር መሄድ ነው። ሕጉን ቀንና ሌሊት ማሰብና ማሰላሰል ከእግአዚብሔር ጋር መጓዝ ነው። አካሄድ እለት እለት መሆኑን፥ በፈቃድ ላይ የተመሠረተ እንደሆነ፥ ወድደን ፈቅደን የምንተገብረው መሆኑን ማሰብም ብልህነት ነው።
ለመሆኑ የእኛስ አካሄድ ከማን ጋር ይሆን? የሕይወት ዘመናችን ሲገፋ፥ ዓመታቶቻችንም ሲነጉዱ፥ ለማን ቤት እየቀረብን ይሆን? ለሰይጣን ወይስ ለእግዚአብሔር?📝ዲያቆን ፍሬሰንበት አድሀኖም ✨✨✨🍁✨✨✨
"እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ።"
ኢሳ 41÷10
"ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን?"
ማቴ 26÷40
"ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር።"
ማቴ 18፥6
"ኹለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይኽ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለኹ፡፡"
ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
ሚያዚያ ፲፰ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ጋብቻችኹን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸምማችኹት
ወጣት ዳዊት አለማየሁ እና ወይ/ት ሀና ሳሙኤል የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችኹን ይባርክላችኹ፥ ያጣምራችኹ፥ ያዋሕዳችኹ 🙏
መድኃኔዓለም በሕይወታችኹ ሞገስ ይኾናችኹ ዘንድ በፍቅርና በጤና ይባርካችኹ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
"የፍኖተ ወንጌል አባላት "
"ነፍሴ ሆይ፥ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ ታውኪኛለሽ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ።"
መዝ 42÷5
"ኹለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይኽ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለኹ፡፡"
ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
ሚያዚያ ፲፯ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ጋብቻችኹን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸምማችኹት
የፍኖተ ወንጌል ፍሬ የሆንሽው እህታችን መዘምርት ብርሐን ጉደታ እና ሮቤል መኩሪያ የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችኹን ይባርክላችኹ፥ ያጣምራችኹ፥ ያዋሕዳችኹ 🙏
ስታገለግይው የኖርሽው መድኃኔዓለም በሕይወታችኹ ሞገስ ይኾናችኹ ዘንድ በፍቅርና በጤና ይባርካችኹ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
"የፍኖተ ወንጌል አባላት "
"ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፥ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።ከኃጢአቴ ፊትህን መልስ፥ በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።"
መዝ51÷ 8-11
"ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።"
1ኛ ቆሮ 1÷10
"መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር፤ የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም። የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም"
✨መዝ 51:16-17✨
