ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Открыть в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Больше670
Подписчики
-224 часа
+57 дней
+130 дней
Архив постов
“በዚያም ጊዜ ትምረን ይቅርም ትለን ዘንድ በበላነው ሥጋህ በጠጣነውም ደምህ ተማጽነናል አንተ ሥጋዬን ለበላ ደሜንም ለጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ብለሃልና ። ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማጽነናል ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት አንተ መታሰቢያሽን ያደረገ ስምሽንም የጠራ የዘላለም ድኅነትነ ይድናል ብለሃታል”
ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ደብረ ዘይት
ደብረፅዮን ዘይት የወይራ መብቀያ፣ በወይራ ደን የተሸፈነ ተራራ ማለት ነው። «ደብር» ማለት «ተራራ» ማለት ሲሆን «ዘይት» ማለት ደግሞ «ወይራ» ማለት ነው። በዚህም «ደብረ ዘይት» ማለት የወይራ ዛፍ የሞላበት፣ የበዛበት፣ የወይራ ተራራ ማለት ይሆናል።
ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኘው ተራራ በደብረ ዘይት በመካከል የቄድሮን ሸለቆ ብቻ አለ። ከግርጌው ጌቴ ሴማኒ የተባለው የአትክልት ስፍራ ይገኛል። የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበት ነው።
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋዋ ያረፈበት ወይም የድንግል መካነ መቃብር በዚህ ተራራ ግርጌ ይገኛል። ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምሥራቅ ዳገት ላይ ይገኛሉ። ይህ ተራራ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጸ ብዙ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ቦታ ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናገሯል። (ማቴ.፳፬፥፫) በዚሁ ተራራ ላይ ወደ ሰማይ ዐርጓል። በዚሁ ተራራ ላይ ቀን በከተማና በገጠር ሲያስተምር ውሎ ሌሊት የሚያድርበት የኤሌዎን ዋሻ ይገኛል። በኋለኛው ምጽአቱ በዚሁ ቦታ እንደሚገለጥ ትንቢት ተነግሯል። (ሉቃ.፳፬፥፶፣ዘካ.፲፬፥፫-፭)
#የታላቁ ጾም አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት በመባል ይጠራል በዚህ ሳምንትም በልዩ ሁኔታ የጌታ ምጽአት ይነገርበታል። በቅድስት ቤተክርስቲያን ሁሌ የጌታ ምጽአት ሳይነገርባት ውሎ አይታውቅም፦
በጸሎተ ሃይማኖት ... ወዳግመ ይመጽእ በቅዳሴዋ ንዜኑ ሞትከ....ወዳግመ ምጽአትከበማለት ሁሌ ስትናፍቅ እና ስታነሳው ትኖራለች የሙሽራዋንም ምጽአት በተስፋ ትጠብቃለች። ቅድስት ቤተክርስቲያን በዓመት ሦስት ጊዜ የመሽራዋን ምጽአት በዘመን ውስጥ በማካተት ነገረ ምጽአትን ከሌላው ዕለታት ለይታ ታስተምራለች ፦ የጌታችን ዳግም ምጽአት በዓመቱ ውስጥ ሦስት ጊዜ ይታሰባል፦ -ከታኅሣሥ አራት እስከ ስድስት ባሉት ቀናት በሚገኘው ሰንበት -ጾመ ኢየሱስን በጀመርን በአምስተኛው እሑድ/ዛሬ/ -በዓመቱ ፍጻሜ በወርኃ ጳጉሜን ናቸው።
ማራናታ: ዳግመ ይመፅዕ በስብሐት
(በትዕግስት ጨርሳቹ አንቡት ጠቃሚ ነው)
ጥንታዊቷና ብቸኛዋ የክርስቶስ አካሉ የሆነችው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ ላይ ከምታውጀውና ከምትመሠክረው ምስክርነት አንዱ የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምፅዓት ነው። “…ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ቅዱስ ኃያል፤ ቅዱስ ህያው ዘኢይመውት። ዘተንሥአ እም ሙታን አመ ሣልሥት ዕለት፤ ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ ወነበረ በየማነ አቡሁ፤ ዳግም ይመፅዕ በስብሐት፤ ተሰአለነ እግዚኦ…።” / “ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ቅዱስ ኃያል፣፤ ቅዱስ የማይሞት። በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሳ፤ በምሥጋና ወደ ሰማያት ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ፤ ዳግመኛም በምሥጋና ይመጣል…።” ከፊታችን የምንቀበለውን የደብረ ዘይት ሳምንት ምክንያት በማድረግ ከክርስቶስ ዳግም ምፅዓት ጋር የተያያዙ ዐሳቦችንና ክስተቶችን እንዳስሳለን አብራችሁን ሁኑ። መጽሐፏን አንብቦና መርምሮ በሕይወት፣ በእውነትና በእውቀት ቤተክርስቲያንን የወደዳት ቅዱስ ያሬድ ትምህርቷን ለየወቅቶቹ በደለደለበት ድጓው የጌታችንን ዳግም መምጣት በእኩለ ፆመ እግዚእ እና በወርሐ ጳጉሜ እንዲታሰብ ሥርዓት ሠርቶልናል። በእነዚህ ወቅቶች አብዝተን እንድናስበው አድርጎናል እንጂ ቤተክርስቲያን የጌታ መምጣት ለቅፅበት እንኳን ዘንግታው አታውቅም። ራሱ ባስተማራት ጸሎት “መንግሥትህ ትምጣ” እያለች የወርቅ ልብስን ተጎናፅፋ በቀኙ የምትቆምበትን ቀን ትናፍቃለች። ዳግመኛም በአዋጇ “ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ፣ወትንሣኤከ ቅድስት፣ነአምን ዕርገተከ፣
ወዳግመ ምፅአትከ….።” (“ጌታችን ሆይ ሞትህንና ቅድስት የምትሆን ትንሳሣህን እንናገራለን፤ ዕርገትህንና ዳግም መምጣትህንም እናምናለን” በጸሎተ ሃይማኖቷ ላይም “…. ዳግመኛም በምሥጋና ይመለሳል፣ በህያዋንና በሙታን ለመፍረድ…… የሙታንን መነሣት ተስፋ እናደርጋለን….” በማለት ነገረ ምፅዐቱ በፍቅር የምትጠብቀው እምነቷና ተስፋዋ መሆኑን ታነሳለች። በእርግጥ የክርስቶስ ዳግም መምጣት ለቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለዓለምም ተጠባቂ ነገር ነው። ምንም እንኳን ይመጣል የሚሉበት ሁኔታና ምክንያት ቢለያይም በዓለም ላይ ያሉ ከሦስት ቢሊዮን በላይ የሆኑ የክርስትና፣ የእስልምና፣ የይኾዋ ምስክሮችና ልዩ ልዩ እምነቶች የክርስቶስን ዳግም መምጣት ይጠባበቃሉ። ይህንን መሠረት በማድረግ በርካቶች በተቀነባበሩ ሤራዎችና ሀሰተኛ ትንቢቶች ክርስቶስ በዚህ ቀን ይመጣል ሲሉ ተደምጠዋል። የክርስቶስ ዳግም ምፅዓት ግምቶችና ሃሳዊ ትንቢቶች መነገር የጀመሩት ክርስቶስ ካረገ ፵ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ነበር። በ፸ ዓ.ም. ከኢየሩሳሌም መጥፋት ጋር ተያይዞ የክርስቶስ ዳግም ምፅዓት መድረሱን ያወጁ ብዙዎች ነበሩ። በ፭፻ ዓ.ም. በተመሳሳይ ክርስቶስ እንደሚመጣ ያስተማሩ ነበሩ። የፍሎሪው (የጣልያን) እያቄም የክርስቶስ ዳግም ምፅዓት በ፲፪፻፷፰ ዓ.ም. እንደሚከናወን ሲተነብይ ጆን ዴ ሪኩታሊድ እስከ ፲፫፻፸ ዓ.ም. ጌታ እንደሚመጣ ተንብዮ ነበር። ኢማኑኤል ስዊዲንበርግ የተሰኘው ሀሰተኛ ነብይ ኢየሱስ በ፲፯፻፶፯ እንደሚመጣ የተነበየ ሲሆን ይህ ትንቢቱ ሲከሽፍበት ጊዜውን አሻሽሎ በ፲፯፻፸ ዓ.ም. የክርስቶስን መምጣት “በሥጋ ሳይሆን በመንፈስ ይመጣል” ሲል አሻሽሎታል ምንም እንኳን ይሄም ቅዥት ቢሆንበትም። የክርስቶስ መምጣት ዙሪያ የተደረጉ ትንቢቶች ብዙ ቢሆኑም የይሖዋ ምስክሮች አስገራሚ ትንቢት ነው። የቤተ እምነቱ መሥራች ቻርለስ ራስል የክርስቶስ መምጣት በ፲፱፻፲፬ ዓ.ም. እንደሚሆን የተናገረ ሲሆን እርሱም እንደቢጤዎቹ ትንቢቱ ሳይሰምርለት ሲቀር ዝም ከመሰኘት ወይም ሌላ ቀን ከመተንበይ ይልቅ የመጨረሻው ቀን ቅዱሳን ወደ ላይ መነጠቃቸውንና የጌታ ምፅዓት መከናወኑን በ “ካፈርሁ አይመልሰኝ” ትምህርቱ ቀጥሎበት ነበር። የአድቬንቲስት፣ የመጨረሻው ቀን ቅዱሳን የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሥራቾችም የጌታን መምጫ ቀን ቢተነብዩም ከመንፈስ ቅዱስ ያልሆነው ትንቢታቸው አሳፍሮ መልሷቸዋል። በ፳፻፲፪ በማያ ቀመር መሠረት ክርስቶስ እንደሚመጣና ዓለም እንደምትጠፋ የተሰበከው ስብከት ለበርካቶች እውነት የመሰለ ቢሆንም ለሆሊውድ ፊልም መሥሪያ ከመሆን አልተረፈም ነበር። በዘመናችንም በርካቶች በተለይ በፈረንጆቹ ፳፻፳፭ እና ከእዛ በኋላ “ዓለም ትጠፋለች” ብለው በመስበክ የአማኞቻቸውን ንብረት በማሸጥና በመዝረፍ የከበሩ በርካታ ሃሳውያን መሲሆች ተገኝተዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት “ክርስቶስ ሊመጣ ነው፤ ወደ ተራራ ወጥተን በፆም እንቀበለው” በሚል ስብከት የምእመናኑን ነብስ የቀጠፈውን አፍሪካዊ ፓስተር ጨምሮ። ቤተክርስቲያን ግን “ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ። ያን ግን እወቁ፤ ባለቤት ከሌሊቱ በየትኛው ክፍል ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፣ ቤቱም ሊቈፈር ባልተወም ነበር። ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።” ማቴ ፳፬÷፵፪-፵፬ በማለት የጌታዋን ቃል በማስተማር “በዚህ ቀን ይመጣል፤ በዚህ አይመጣም” በሚል ትምህርት በመደናበር እንዳይስቱና ሁሌም ተዘጋጅተው እንዲኖሩ ታስተምራለች። እኛ ክርስቲያኖች የዳግም ምፅዓት በነቢይ አስቀድሞ “እግዚአብሔር ገሃደ ይመፅዕ” (“እግዚአብሔር ግልፅ ሆኖ ይመጣል”) ተብሎ እንደተነገረ በግርማ መለኮት፣ በክበበ ትስብእት ለፃድቃን ሊፈርድላቸው ለኃጥአን ሊፈርድባቸው እንዲሁም ይህን ዓለም አሳልፎ የማያልፈውን ዓለም ሊሰጥ እንደሆነ እናምናለን። በመሆኑም ይህችን ወደፊት ያለች ቀን በየዓመቱ ሰንበተ እግዚኡ – የጌታ ሰንበት እያልን በዓልን እናከብራለን። ስለዚህ ቀን በዓል በኢትዮጵያ በትግራይና በሰሜን ሸዋ ንግሥ የሚካሄድ ሲሆን በጉራጌ አካባቢዎች የሚገኘው ማኀበረሰብም በዮሐንስ ራዕይ ምዕራፍ ፲፱ ላይ ያለውን እራት በማሰብ በደብረ ዘይት ዕለት ድግስ፣ በዚህም ስለክርስቶስ መምጣት ፍስሀ ያደርጋሉ።እኛም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በመጣ ጊዜ እንዳያሳፍረን የሕይወት ቃሉን ያሰማን ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱን እየተማፀንን ስለነገረ ምፅዓቱ አምልቶ በፃፈው ባለራዕዩ ቅዱስ ዮሐንስ ቃል ጽሑፋችንን እንዘጋለን። ማራናታ! አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና
መጋቢት ፲፪ [ 12 ]
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ወደ ጠንቋዩ በለዓም ተልኮ አህያዋን በሰው አንደበት አናግሮ የእስራኤልን እርግማን ወደ በረከት የመለሰበት ዕለት ነው፡፡
በለዓም እስራኤልን ይረግማቸው ዘንድ ባላቅ በጠራው ጊዜ ፤ በጐዳናም በፊቱ ቅዱስ ሚካኤል ቆሞ ስለተገለጠ አስደነገጠው ፤ አህያው በሰው አንደበት እስከተናገረች ድረስ ፤ መርገሙንም ወደ በረከት መለሰው።
" እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ ፤ ሰገደም ፥ በግምባሩም ወደቀ።" [ዘኁ.፳፪፥፴፩]
የቅዱስ ሚካኤል በአማላጅነቱ ለዘላለሙ ይጠብቀን አሜን።
በእንተ ቅዱስ ቁርባን
❓ቁርባን ማለት ምን ማለት ነው?
◾️ ሰዎች ለኃጢያት ስርየት ፣ ለምስጋና ወይም በስለት ምክንያት ለእግዚአብሔር የሚሰጡት አምኃ ወይም ስጦታ ቁርባን ይባላል።
❓ቁርባን በብሉይ ኪዳን
◾️በብሉይ ኪዳን ዘመን ይቀርብ የነበረው የመስዋዕት ቁርባን ፤ ከበግ ፤ ከላምና ፤ ከተለያዩ እንስሳት ነበር ።
ዘፍ 8፥20 ፣ ዘፍ 14፥18.... ፤ ዕብ 5 ፥ 6 ፤ ዕብ 6 ፥ 1
❓ቁርባን በሐዲስ ኪዳን
◾️በሐዲስ ኪዳን እንስሳት በቤተ መቅደስ ውስጥ መስዋዕት (ቁርባን) ሆነው አይቀርቡም መስዋዕት ሁሉ በክርስቶስ ሥጋና ደም ተጠቃሏል ።
❓ምስጢር ለምን ተባለ?
◾️ኅብስቱና ወይኑ ተለውጦ ሥጋና ደመ ወልደ እግዚአብሔር መሆኑ ታላቅ ምስጢር ነውና።
❓ምስጢረ ቁርባን መቼና እንዴት ተመሠረተ?
◾️የመሠረተው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሲሆን የመሠረተው በእለተ ሐሙስ ነው።
ማቴዎስ 26
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁶ ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ።
²⁷ ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
²⁸ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
🔱🍀🔱🍀🔱🍀🔱🍀🔱🍀🔱🍀
"መጋቢት ፲ ቀን - መስቀለ ኢየሱስ"
✍️ በዚኽች ዕለት ጌታ የተሰቀለበት መስቀል በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ሰዎች አማካይነት ኹለት ጊዜ ከተቀበረበት እንዲወጣ ኾኗል፡፡
መጀመሪያ በንግሥት ዕሌኒ ከኢየሩሳሌም!
ኹለተኛ ደግሞ በንጉሥ ሕርቃል ከፋርስ!
"ወበዛቲ ዕለት እንበለ ይዕዱ ጌሠመ፤ መስቀል ተረክበ እምዘተ ኀብዐ ወገብረ ሰላም በኢየሩሳሌም ቅድመ ወበፋርስ ዳግመ"
✍️የፋርሱ ግን እነኾ መሳፍንተ ፋርስ ግብጽ ዘምተው ድል ነሥተው ሲመለሱ ከመካከላቸው አንዱ "ኢየሩሳሌም ወርጄ አይሁድን ማርኬ እመጣለኹ" ብሎ እግረ መንገዱን ወደ ኢየሩሳሌም ወርዶ አይሁድን ማርኮ ሲመለስ ንግሥት ዕሌኒ በጎልጎታ ካሠራችው ቤተ መቅደሥ ቢገባ መስቀሉን እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡ ቢይዘው አቃጠለው፡፡ ከዚኽ በኋላ ኹለቱን ዲያቆናት አሸክሞ ሌላውንም ንዋያተ ቅድሳት ዘርፎ ወደ ሃገሩ ተመለሰ፡፡
✍️ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይኽን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ግብር ገብቶ ቀኖና ይዞ አንድ ሱባዔ ሲፈጸም ፈቃደ እግዚአብሔር መኾኑን ተረድቶ በአዋጅ ዘምቶ ድል ነሣው፡፡ መስቀልም ያለበት ጠፍቶት ሲቸገር ቅዱስ መስቀሉ ሲቀበር እና ዲያቆናቱን ሲገድል በመስኮት ኾና ያየች ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ ቁስጥንጥንያ ወስዶታል፡፡
ታሪኩ የተፈጸመው በ614 ዓ.ም. ነው
ከቅዱስ መስቀሉ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን!!!
የተወደደ ቀን ይኹንልን!
💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿
“በምትሄድበት ሁሉ እግዚአብሔር አምላክህ ከአንተ ጋራ ነውና አይዞህ፤ በርታ፤ ጽና፤ አትፍራ፤ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?””
ኢያሱ 1:9
መልካም ቀን🙏
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ"
ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
መልካም ዕለተ ሰኞ🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
መዝሙር ዘመፃጒዕ
''አምላኩሰ ለአዳም ለዕረፍት ሰንበተ ሠርዐ ወይቤልዎ አይሁድ በዓይ ሥልጣን ትገብር ዘንተ ወይቤሎሙ ኢየሱስ አነኒ እገብር አንትሙኒ እመኑ ለግብርየ ወይቤሎሙ አነ ውእቱ እግዚአ ለሰንበት እግዚኣ ለሰንበት ወልድ ዋሕድ ወይቤሎሙ ብውሕ ሊተ እኅድግ ኃጢአተ በዲበ ምድር እስብክ ግእዛነ ወእክሥት አዕይንተ ዕውራን አቡየ ፈነወኒ"ትርጒም፦ የአዳም ፈጣሪ ለዕረፍት ሰንበትን ሠራ አይሁድ ይህንን በማን ሥልጣን ታደርጋለህ ብለው ጠየቁት ኢየሱስም እኔ እሠራለሁ እናንተም ሥራዬን እመኑ የሰንበት ጌታ እኔ ነኝ አላቸው የሰንበት ጌታዋ ወልድ ዋህድ ነው አላቸው በምድር ላይ ኃጢአትን እተው/ይቅር እል ዘንድ ሥልጣን አለኝ ነጻነትን እሰብክ ዘንድ የዕውራንን ዓይን አበራ ዘንድ አባቴ ላከኝ አላቸው'' ✨✨✨የዕለቱ ምስባክ
"እግዚአብሔር ይረድኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ ወይመይጥ ሎቱ ኲሎ ምስካቤሁ እምደዌሁ አንሰ እቤ እግዚኦ ተሣሃለኒ " መዝ ፵፥፫ትርጉም እግዚአብሔር በሕማሙ አልጋ ሳለ ይረዳዋል መኝታውንም ከደዌው የተነሣ ይለውጥለታል እኔስ አቤቱ ይቅር በለኝ እላለሁ:: ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🔔ዐቢይ ጾም 🔔
🔔አራተኛ ሳምንት🔔
🔔መጻጉዕ🔔
ምስባክ
የዕለቱ ምንባባት
ገላ 5÷1-ፍ
ያዕ 5÷14-ፍ
ሐዋ 3÷1-13
የዕለቱ ምስባክ
እግዚአብሔር ይረጽኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ ወይደመጥ ሎቱ ኩሎ ምስካቤሁ እምጼዋሁ እንሰ እቤ እግዚኦ ተሠሃለኒ መዝ 40÷3
ትርጉም
እግዚአብሔር በሕማሙ አልጋ ውስጥ ላለ ይረዳዋል መኝታውም ከደዌው የተነሣ ይለውጥለታል እኔስ አቤቱ ይቅር በለኝ እላለሁ ።
የዕለቱ ወንጌል ዮሐ 5÷1-25
ቅዳሴ ዘእግዚእነ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🤲🤲🤲🕯🕯🕯🕯🕯
ዕለተ ሰንበት በማስቀድስ እናሳልፍ
ያንን ተስፋ ያልነበረውን በሽተኛ ከደዌ ሥጋው ፈውሶ ሕይወትን የሰጠው አምላክ፣ እኛንም በውስጥ በአፍአ ካለብን ደዌ ሥጋና ደዌ ነፍስ እንዲፈውሰን፤ ቁስለ ኃጢአታችንን እንዲያደርቅልን፣ በሕይወትና በጤና እንዲጠብቀን የእርሱ የጌታች ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፡፡
ኑ እያስቀድስን ድውይ ነን አንተ አድነን እንበለው 🤲
✨✨✨
እንኳን ለአባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓለ እረፍታቸው በሰላም አደረሰን!
✨✨✨
ቀኑ መጋቢት 5፤ ዕለቱ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ፤ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኗል። አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል።
“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጵያንም ባርክ” ይላል።
ህመም የጀመረው መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው። መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት ዘርአቡሩክ፥ ፍሬ ቅዱስ፥ ያዕቆብ፥ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉሥ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል፤ ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ በሌለበት በረሐ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት። በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ፥ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን፥ ቀይ መልኩ፥ ረዥም የራስ ጠጉሩ፥ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ አስደነቃቸው።
✨✨✨
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ የነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ። ጌታችን መላእክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ። ከሰማይ ወደ ምድር ኅብሩና አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ፀሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር፤ ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ። ምድር ራደች፥ ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ፥ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።
“ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልሃለው። ስምህን የጠራ፥ መታሰቢያህን ያደረገውን፥ ዕጣን ቋጥሮ፥ ግብር ሠፍሮ፥ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው። አንተ ከገባህበት ገነት መንግሥተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው።
አባታችንም “አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጵያን ህዝብ ማርልኝ” አለው። እነሆ ምሬልሃለው፤ አሥራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ፤ በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው።
ከዚህ በኋላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ፤ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት፤ ሥጋውንም ይዘውት ሄዱ፤ የት እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም። አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላል፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል፤ ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም።
ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ ይበዛል። ኢትዮጵያን አብዝቶ ይወዳታል። ምድራዊ ምግብ አልተመገበም፥ የእናቱን ጡት እንኳን አልጠባም፥ ልብስና መጠለያ አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ። በዛሬዋ ቀን #መጋቢት_5 ሩጫውን ጨረሰ።
ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን! አሜን።🤲
✨✨✨🍁🍁🍁
✨✨✨🍁🍁🍁
"ግሩማን መላእክትን ሱራፌል ወኪሩቤል እለ አክናፊሆሙ ነበልባል ወረዱ ዮም ይትቀበሉከ በብሂል አማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገባሬ ኃይል"ትርጉም፦
ኃይልን ተአምራትን የምታደርግ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ሆይ ክንፊቻቸው በነበልባል የሆኑ የሚያስፈራ መላእክት ሱራፊልና ኪሩቤል እውነት በማለት ይቀበሉህ ዘንድ ዛሬ ወረዱ።ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ድጓው ላይ።
+1
ታቦት ጠባቂዋ እናት ዐረፉ 😥😥😥
ገሊላ ደሴት የሄደ ሁሉ የሚያገኛቸው ታላቋ ምልክት እናት፤
በዚች ዓለም 107 ዓመታት ሲኖሩ 87ቱን ዓመታት ብቻቸውን በገሊላ ደሴት ገዳምና ታቦቱን እየጠበቁ አሳለፉት። አዴ ኩሼ ጎንደር የዝዋይ (ባቱ) የገሊላ ደሴት ምልክት ናቸው።
የደሴቱ ሰዎች ወደ ከተማ መሬት ሲሄዱ፤ እርሳቸው ግን ከካህናተ-ሰማይ ታቦት ጋር መኖርን መረጡ‼️
ምንም ባይኖራቸውም በሕይወታቸው ደስተኛ ሆነው የኖሩ ብርቱና ድንቅ እናት ናቸው። ሃይማኖት በምን መልኩ ሰውን እንደሚያኖር ምልክት ናቸው።
ዛሬ ግን ወደሚወዳቸው እግዚአብሔር እቅፍ እረፍት ወዳለበት ወደ ሀገራቸው የሰማይ ቤታቸው ሄደዋል።
እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን🤲🤲🤲
የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሠራር ሚዛናዊ እና ፍትሐዊነት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባ ተመላከተ !
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
መቻቻልን፣ አብሮነትንና ፍትሕ ላይ የተመሰረተ የአንድነት መስተጋብርን ከምንመለከትባቸው ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሚዛናዊ እና ፍትሐዊነት ላይ ተመሥርቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ።
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ያነጋገራቸው የሃይማኖት አባቶች ከሰሞኑ በተፈጠሩ ኢትዮጵያዊ አንድነትን ከሚሸረሽሩና የሃይማኖትን ነጻነት ከሚጋፉ ተግባራት አኳያ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያወጣው መግለጫ ሚዛናዊነት የጎደለው እና በፍትሐዊነት ላይ ያልተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ቅርብ የሆኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ እንደገለጹት የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤው በሕግ ከተሰጠው ኃላፊነት አሠራር አንጻር ከሰሞኑ በጉባኤው ጽ/ቤት የወጣው መግለጫ በተግባር ያለፉ ነገር ግን ትኩሳታቸው ዛሬም ድረስ ያሉ እውነታዎችን መጋፈጥ ያልቻለ መሆኑን ነው የገለጹት።
የመግለጫው ሀሳብ ይህንን "ማኅበረሰባዊ ትንኮሳ የጀመሩት ኦርቶዶክሳውያን ነን የሚሉ መሆናቸው እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ነን የሚሉትም አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት የገቡበት እንደሆነ" ተደርጎ መቅረቡ አግባብ አለመሆኑ እና ያለፉ እውነታዎችን መሠረት ያላደረገና አንድን ወገን ብቻ ማዕከል አድርጎ መተላለፉ ተቀባይነት የለውም ነው ያሉት።
ከዚህ ቀደም ከማኅበራዊ ትስስር ገጾች ዘመቻ በተጨማሪ ክርስቶስ ማን ነው? 303 ወሳኝ ጥያቄዎች ፣ ሰይፉን ፍለጋ፣ ኢየሱስ የኢስላም ነቢይ፣ መጽሐፍ ቅዱስን ማን በረዘው፣ ክርስትና መለኮታዊ ሃይማኖት ነውን?፣ ክርስቶስ በኢስላም ፣ ሙሐመድ የታላላቆች ታላቅ የሚሉና ሌሎችም የክርስትናን አስተምህሮ በቀጥታ የሚዘልፉ፣ የሚያንቋሽሹ እና የሚያጥላሉ የጥላቻ ሀሳቦችን የያዙ መጻሕፍት ጭምር ሲዘጋጁ እና ለተዘጋጁትና ለተሰራጩትም ባለቤት እያላቸው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤው በእነዚህ የክርስትና መሠረተ እምነት ላይ ጥላቻን በሚያቀነቅኑ ተቋማትና ግለሰቦች ላይ አንድም እርምጃ ሳይወስድና እነዚህ የጥቃት መነሻዎች እያሉ ኦርቶዶክሳውያን ነን የሚሉ ግለሰቦች የጀመሩት የጥላቻ ንግግር በሚል አጥቂንና ተጠቂን በቅጡ ያልለየ ፍረጃ ተቀባይነት ዝቅተኛ መሆኑን አመላክተዋል።
ሌላኛው የሃይማኖት አባት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት መልአከ ምሕረት ወልደ ገብርኤል ናቸው ለሚዲያችን በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባለፈው ማክሰኞ ያወጣው መግለጫ ሚዛናዊነት የጎደለው መሆኑን እና ተቋሙ ይህንን ድርጊት በተለመለከተ በድጋሚ አጢኖት ይቅርታ ሊጠይቅ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በዚህና በሌሎች የሕዝብ አስተያየቶች ላይ የሚለው ነገር እንዳለ ብለን የተቋሙን ሃሳብ ለማካተት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
በተጨማሪም ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት በሆኑ ጉዳዮች መሰደብና መጥላላት ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮችን በተመለከተ ያለው ነገር የለም።
“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።”
— 1ኛ ቆሮ 10፥13
