cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

💞አውደ💞 ቃል 💞💖

የግጥም መንደር አብረን በቃላት ስሜታችንን እንገላላፃለን join & share እንዳይረሳ

Больше
Рекламные посты
452
Подписчики
Нет данных24 часа
+147 дней
+4930 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ከአትሮንሱ ስር አንድ ሁልጊዜም መማር የማይታክታቸው አባት ነበሩ። በጣም የተማሩ ቅኔ አዋቂ መፃሕፍትን የመረመሩ ሊቅ ቢሆኑም ሁሌም ከአትሮንስ ስር የማይጠፉ ተማሪ ነበሩ።ይህንን ልምዳቸውን ያየ አንድ ሰው፦ "እርስዎ ብዙ የተማሩና ያነበቡ ሰው ነዎት ከዚህ በኃላ ማረፍ ሲገባዎት ለምን ጊዜዎን በትምህርት ያጠፋሉ?" አላቸው። እርሳቸውም ፦ "መልዓከ ሞት መጥቶ ወደ ፈጣሪ በወሰደኝ ጊዜ 'የት አግኝተህ አመጣኸው?' ሲባል ከአትሮንስ ሥር ቁጭ ብሎ የአንተን ቃል ሲሰማ አገኘሁት ብሎ እንዲነግርልኝ ነው"አሉ።    መልዓከ  ሞት አሁን በዚህ ሰሞን መጥቶ ቢወስድህ ምን ሲያደርግ አገኘሁት የሚል ይመስልሃል ? ሲፀልይ? ሲመፀውት? ሲመርቅ? ሰዎችን በፍቅር ቃል ሲናገር? ሲያማ?ሲሳደብ?ሲያስታርቅ? ሲያጣላ?እውነትም የእኚህ አባት ጭንቀት እጅግ ተገቢ ጭንቀት ነበር። እኛም ወደራሳችን እንመልከት  🙏🙏🙏 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
Показать все...
🔥 1
አይጥ ጠላ ጠምቃ ጠጥታ ጠጥታ ⚒ዱላ ስጡኝ አለች ድመት ልትመታ 🐱 ♡ ㅤ  ⎙ㅤ  ⌲  http//me:/AWDEKALALT_2112 @AWDEKALAT_2112      
Показать все...
          ዘመም ይላል እንጂ (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ጊዜው መክፋት እንደ ግፉ መስፋት እንዳገሩ ክስመት እንዳገሬው ጥመት እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ:: የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት ጉድጏድ ተምሶለት ሰብእና ሲቀበር፤ በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር:: ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ ታረደ ነደደ ከዘብጥያ ወጥቶ ዘብጥያ ወረደ የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው ሰው በገዛ ጥላው በርግጎ ሲሸበር በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር:: አዎ ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል በደል ያስተክዛል ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል በነገ ያመነ ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል:: ይቅርታና ምህረት ፍቅርና ህብረት ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም የመኖር ፍላጎት ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም:: Join us https://t.me/AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
Показать все...
💞አውደ💞 ቃል 💞💖

የግጥም መንደር አብረን በቃላት ስሜታችንን እንገላላፃለን join & share እንዳይረሳ

Фото недоступноПоказать в Telegram
ወንድሞቼን በኢሞጂ እኔ 🥰❤ እናንተስ ?? @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
Показать все...
🥰 2
‍ እያጣሁኝ እንጂ እያነሰኝ አቅሜ እንዲህ አልነበርንም እኔና ቅዳሜ ኑሮ እየጨመረ ሲራቆት ሕይወቴ ቅዳሜን በስራ እሁድን በቤቴ አሳልፈው ጀመር በሀሳብ በትካዜ የዚ ሁሉ ምክኒያት አንቺ ነሽ ደሞዜ የሚል ሲንግል ልልቀቅ አልልቀቅ? ? 😁🤔🤔 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
Показать все...
👍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
Показать все...
👍 2
00:53
Видео недоступноПоказать в Telegram
እዚህ ውስጥ ስምሽ የሌለ ኢትዮጵያዊ አደለሽም ግን የኔም የለም ስምሽ የሌለ ዳይ ወደ comment @ @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme 😅
Показать все...
             💔ናፍቀሽኛል_ሆዴ💔                                  መንገድሽ መንገዴ                      ሆኖ የዘለቀው                    ፍቅርሽ ስለገዛኝ                ባሪያሽ ስለሆንኩ ነው                    ሆዴ ናፍቀሽኛል                   ምፈልገው ቢሟላ                  የጠየኩትንም ባገኝ                   አልጠግብም እኔ                  አይንሽ ነው የራበኝ                    ፍቅር ናፍቀሽኛል                    ሆዴ ናፍቀሽኛል                   አንቺን ለማግኘት                ልቤ አጥብቆ ይመኛል፡፡    👇👇👇👇👇👇👇👇     join us @awdekalat_2112 join us @awudekalat_2112    
Показать все...
👍 1
ውሸታም ይገርማል ሰው ነገረኝ ሰማሁ የእውነት ወድጄህ በውሸት አለም ጠፋሁ ደሞ አምኜሀለሁ ያንቺ ነኝ ስትለኝ በቃልህ ሸንግለህ ልቤን ስትሰርቀኝ ግን እውነቱ ይሄ አደለም አንተ የሌላ እንጂ የኔ አይደለህም አለች ደሞ እንደኔ የምታደማት እወድሻለሁ እያልክ የምታታልላት ግን ውሸታም ነህ አስመሳይ ለቀረበህ ፃዲቅ መሳይ እንደኔ ያመነህን ደሞ አታላይ አሁን ግን አውቂያለሁ እውነቱን ሁሉ ሰምቻለሁ ፍቅረኛ እንዳለህ የሌላ እንደሆንክ ተረድቻለሁ ግን ስላሳለፍናቸው የውሸት ጊዚያት አመሰግናለሁ።።።።። 💔💔💔💔💔💔💔💔 @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme
Показать все...
👏 1
Repost from N/a
🕊 [ † እንኳን ለነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኤርምያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † †  🕊  ቅዱስ ኤርምያስ  🕊 †    † ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ከዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በስድስት መቶ አካባቢ የነበረ ነቢይ ነው:: አባቱ ኬልቅዩ ይባላል:: ከካህናተ እስራኤል አንዱ ነበር:: እግዚአብሔር ኤርምያስን የጠራው ገና በሕፃንነቱ ነበር:: "ከእናትህ ማኅጸን ሳትወጣ መርጬሃለሁ: ቀድሼሃለሁ" ሲልም በገሃድ መስክሮለታል:: [ኤር.፩፥፭] (1:5) ከቅዱሳን ነቢያት እንደ ኤርምያስ የተሰቃየና ያለቀሰ የለም:: ከሰባ ዘመናት በላይ ስለ ወገኖቹ አልቅሷልና ሊቃውንት "ነቢየ ብካይ" [ባለ እንባው ነቢይ] ይሉታል:: ዘመኑ ዘመነ-ኃጢአት [ዘመነ ዐጸባ] ነበር:: እሥራኤላውያን ከመሪዎቻቸው ከነ ሴዴቅያስ ጋር በክፋት ተባብረውም ነበርና ኤርምያስን አልሰሙትም:: ይልቁኑ ክፉ ቦታ ውስጥ አስረው አሰቃዩት:: እግዚአብሔር ግን በኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አማካኝነት ከመከራው አዳነው:: የተሰበከላቸውን የንስሐ ጥሪ አልሰሙምና ስልምናሦር የሚባል የአሕዛብ ንጉሥ መጥቶ አሥሩን ነገድ ማርኮ በ፯፻፳፪ [722] አሦር [ነነዌ] አወረዳቸው:: በኋላ ደግሞ በኃይለኝነቱ የታወቀው የባቢሎን ንጉሥ ይማርካቸው ዘንድ ወደ ሁለቱ ነገድ ኢየሩሳሌም ደረሰ:: ኤርምያስ ወደ ከተማዋ ዳር ወጥቶ ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አለቀሰ:: ከቤተ መቅደስ ንዋያት እኩሉን ለምድር አደራ ሰጣትና ሸሸገችው:: ነቢዩ የተናገረው አይቀርምና ንጉሡ ናቡከደነጾር እኩሉን ገድሎ: እኩሉንም ማርኮ: ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ: የአሕዛብ መዘባበቻ አድርጐ በ፭፻፹፮ [586] ባቢሎን አወረዳቸው:: ቅዱስ ኤርምያስን ግን ትሩፋን [ከመከራው የተረፉት] ይዘውት ወደ ግብጽ ወረዱ እንጂ አልተማረከም:: በዚያም ተአምራትን አድርጐ አራዊትን አጥፍቷቸዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን እውነተኛ አባት : ነቢይ : መምሕርም ነውና ወደ ሕዝቡ [ወደ ባቢሎን] ወረደ:: በዚያም ትንቢትን እየተናገረ : ሕዝቡን ከሰባ ዓመታት በኋላ ወደ ሐገራቸው እንደሚመለሱ እያስተማራቸው በባቢሎን ቆይቷል:: ያለ በደሉም በመከራቸው ተካፋይ ሆኗል:: ሰባው ዘመን ሲፈጸም እግዚአብሔር እንደ ቃል ኪዳኑ በኤርምያስ መሪነት እሥራኤል ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: አሁንም ግን ክፋታቸውን ይተው ዘንድ ፈቃደኞች አልነበሩምና ኤርምያስ ገሠጻቸው:: በዚህ ተበሳጭተው ሊወግሩት ሲሉ ጸጋ በዝቶለት : ምሥጢርም ሰፍቶለት ስለ ነገረ ሥጋዌ [ስለ ክርስቶስ የማዳን ሥራ] አምልቶና አጉልቶ ትንቢት ተናገረ:: አንዴ ልቡናቸው ታውሮ ኤርምያስ ነው ብለው ድንጋዩን በድንጋይ ሲወግሩት ውለዋል:: ዘግይቶ ግን ኤርምያስ ራሱን ገለጠላቸው:: ስለ እነርሱ ሲል ሰባ ዘመን ያለቀሰውንና ምትክ የሌለውን አባታቸውን ወግረው ገደሉት:: ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ሃምሳ ሁለት ምዕራፎች ያሉት ሐረገ ትንቢት ተናግሯል / ጽፏል:: ዜና ሕይወቱ ከራሱ የትንቢት መጽሐፍ በተጨማሪ በተረፈ ኤርምያስ : በመጽሐፈ ባሮክ : በገድለ ኤርምያስ : በዜና ብጹዐን : በመጽሐፈ ስንክሳርም ተጽፏል:: † ቸር እግዚአብሔር በኤርምያስ ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿን ከስደትና ከመቅሰፍት ይሰውርልን:: 🕊 [ † ግንቦት ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ [ከታላላቆቹ ነቢያት አንዱ] [ † ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት ፪. ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ፫. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ ፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ † " ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል : ወደ እርሷ የተላኩትንም የምትወግር : ዶሮ ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም:: እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል:: እላችሁአለሁና : በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም :: " [ማቴ. ፳፫፥፴፯-፴፱] [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Показать все...
👍 1