የሁሉ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ህ/ስ/ማ
Открыть в Telegram
2 239
Подписчики
Нет данных24 часа
+27 дней
+2330 дней
Архив постов
"ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት!"
የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል!!
አካታች እድገት በሁሉ ለሁሉ !!
ለበለጠ መረጃ :-
በነፃ የስልክ መስመራችን 9859 ይደውሉ !!
መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ !
የየሁሉ ቁጠባ እና ብድር ህብረት ስራ ማህበር የማህበራዊ ትስስር ገፆችን ይከታተሉ እንዲሁም ለሌሎችም ያጋሩ!
FOLLOW US 👇
👉 Our YouTube channel
https://youtube.com/@yehulusacco?si=S-tMZf3ocp5P6TSz
👉Our Telegram Group
https://t.me/yehulusaccosltd
👉Our tiktok Account
https://www.tiktok.com/@yehulu_saccosltd...
👉Our website
https://yehulusaccos.et/en/home
ለበለጠ መረጃ፦
በነፃ የስልክ መስመር 9859 ይደውሉ።
https://t.me/yehulusaccosltd
የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር በአለታ ወንዶ ከተማ 11ኛ ቅርንጫፉን አስመረቀ።
ህዳር 20/2018 ዓ/ም
የሁሉ ቁ/ብ/መ/ሕ/ሥራ/ማህበር
አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅና ለአባላቶቹ ተደራሽ በማድረግ ምሳሌ የሆነው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት 11ኛ ቅርንጫፉን በዛሬው ዕለት በአለታ ወንዶ ከተማ ዴላ ቀበሌ ህዝብ አዳራሽ አጠገብ አለሙ አመኑ ህንፃ ላይ በይፋ አስመርቋል።
በሲዳማ ክልል የሕብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሽመልስ አቲሶ ሕብረት ሥራ ማህበራት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የላቀ ሚና እንዳላቸው አንስተው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር ትልቅ ራዕይ የያዙ ወጣቶችን በማሰባሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ እድገት በማስመዝገብ ለነገ ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድበት ሕብረት ሥራ ማህበር መሆኑን ገልፀዋል።
በሲዳማ ክልል 2 ሺህ 197 የሕብረት ሥራ ማህበራት የሚገኙ ሲሆን የሁሉ ቁጠባና ብድር በአለታ ወንዶ ከተማ 11ኛ ቅርንጫፉን በይፋ መክፈቱ ለሁሉም ማህበረሰብ ተደራሽነቱን በማስፋት ፣ የአባላትን የቁጠባና የብድር ባህል በማሳደግ እንዲሁም የተመቻቸ የፋይናንስ አማራጮችን በመፍጠር ረገድ የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው አንስተዋል።
ቁጠባን ባህል ማድረግ ዛሬ ላይ ሆነን ነገን የምንሰራበት ተግባር ነው ያሉት የአለታ ወንዶ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ሳሙኤል ቦጋለ በበኩላቸው አለታ ወንዶ ከተማ ሰፊ የገንዘብ ዝውውር ያለባት የሲዳማ ክልል እንብርት ከተማ ስትሆን በተለይም በዝቅተኛው የኑሮ ደረጃ ላይ ካሉ ማህበረሰቦች ጀምሮ የቀን ገቢ ያላቸውን ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ ያለመው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማህበር በከተማችን ቅርንጫፉን በመክፈቱ ደስ ብሎናል እንደ ከተማ አስተዳደር አሁን ካለን አልሚ ሃይል ጋር በጋራ በመስራት እንዲሁም በሚፈለገው ሁሉ ሕብረት ሥራ ማኅበሩን በማገዝ በጋራ ሆነን ከተማችንን ለማሳደግ በእኛ በኩል ዝግጁ ነን በማለት ተናግረዋል።
የየሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብርሃም ቃሬሶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ባስተላለፉበት ወቅት ለሁሉም ሰው የፋይናንስ ተደራሽ የመሆን ራዕይ ይዞ የተነሳው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር በአሁኑ ጊዜ ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ያሰራጨ ሲሆን ከ25 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል።
አለታ ወንዶ ከተማ ላይ ያለውን ከፍተኛ የገንዘብ ፍሰት አግባብ ባለው መንገድ በመጠቀም ማንኛውም ግለሰብ በመቆጠብ እና የተለያዩ የብድር አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል 11 ኛ ቅርንጫፋችንን በይፋ አስመርቀናል በቅርቡ ሆሳዕና እንዲሁም ሌሎች ከተሞች ላይ ተጨማሪ ቅርንጫፎችን እንከፍታለን በማለት ገልፀዋል።
https://t.me/yehulusaccosltd
የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር በአለታ ወንዶ ከተማ 11ኛ ቅርንጫፉን አስመረቀ።
ህዳር 20/2018 ዓ/ም
የሁሉ ቁ/ብ/መ/ሕ/ሥራ/ማህበር
አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅና ለደንበኞቹ ተደራሽ በማድረግ ምሳሌ የሆነው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት 11ኛ ቅርንጫፉን በዛሬው ዕለት በአለታ ወንዶ ከተማ ዴላ ቀበሌ ህዝብ አዳራሽ አጠገብ አለሙ አመኑ ህንፃ ላይ በይፋ አስመርቋል።
በሲዳማ ክልል የሕብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሽመልስ አቲሶ ሕብረት ሥራ ማህበራት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የላቀ ሚና እንዳላቸው አንስተው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር ትልቅ ራዕይ የያዙ ወጣቶችን በማሰባሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ እድገት በማስመዝገብ ለነገ ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድበት ሕብረት ሥራ ማህበር መሆኑን ገልፀዋል።
በሲዳማ ክልል 2 ሺህ 197 የሕብረት ሥራ ማህበራት የሚገኙ ሲሆን የሁሉ ቁጠባና ብድር በአለታ ወንዶ ከተማ 11ኛ ቅርንጫፉን በይፋ መክፈቱ ለሁሉም ማህበረሰብ ተደራሽነቱን በማስፋት ፣ የአባላትን የቁጠባና የብድር ባህል በማሳደግ እንዲሁም የተመቻቸ የፋይናንስ አማራጮችን በመፍጠር ረገድ የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው አንስተዋል።
ቁጠባን ባህል ማድረግ ዛሬ ላይ ሆነን ነገን የምንሰራበት ተግባር ነው ያሉት የአለታ ወንዶ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ሳሙኤል ቦጋለ በበኩላቸው አለታ ወንዶ ከተማ ሰፊ የገንዘብ ዝውውር ያለባት የሲዳማ ክልል እንብርት ከተማ ስትሆን በተለይም በዝቅተኛው የኑሮ ደረጃ ላይ ካሉ ማህበረሰቦች ጀምሮ የቀን ገቢ ያላቸውን ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ ያለመው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማህበር በከተማችን ቅርንጫፉን በመክፈቱ ደስ ብሎናል እንደ ከተማ አስተዳደር አሁን ካለን አልሚ ሃይል ጋር በጋራ በመስራት እንዲሁም በሚፈለገው ሁሉ ሕብረት ሥራ ማኅበሩን በማገዝ በጋራ ሆነን ከተማችንን ለማሳደግ በእኛ በኩል ዝግጁ ነን በማለት ተናግረዋል።
የየሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብርሃም ቃሬሶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ባስተላለፉበት ወቅት ለሁሉም ሰው የፋይናንስ ተደራሽ የመሆን ራዕይ ይዞ የተነሳው የሁሉ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ሕብረት ሥራ ማህበር በአሁኑ ጊዜ ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ያሰራጨ ሲሆን ከ25 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል።
አለታ ወንዶ ከተማ ላይ ያለውን ከፍተኛ የገንዘብ ፍሰት አግባብ ባለው መንገድ በመጠቀም ማንኛውም ግለሰብ በመቆጠብ እና የተለያዩ የብድር አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል 11 ኛ ቅርንጫፋችንን በይፋ አስመርቀናል በቅርቡ ሆሳዕና እንዲሁም ሌሎች ከተሞች ላይ ተጨማሪ ቅርንጫፎችን እንከፍታለን በማለት ገልፀዋል።
https://t.me/yehulusaccosltd
