cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ቸርነት አያልቅም መድኀኒታችን ሆይ

ህይወትን የሚያስውቡ ውብ ሰዎች አሉ። ስትደክም : ብርታት ይሆኑሃል ህይወት ሲጨልምብህ ብርሃን ይሆኑልሃል ስትሳሳት ደግሞ ይመክሩሃል ስታጠፋ በይቅርታ ያልፉሃል ቴሌግራማችንን ከወደዱት ይቀላቀሉ ለወዳጅ ዘመድዎ #ሼርና #Join ያድርጉልን። https://www.facebook.com/matmenge78?mibextid=ZbWKwL

Больше
Рекламные посты
617
Подписчики
-124 часа
-87 дней
-1130 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

Фото недоступноПоказать в Telegram
#ሐምሌ_5_ለአባታችን_አቡነ_ገብረ_መንፈስ ቅዱስ_በዓል_ነው። እንኳን ለአባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በጨነቃችሁ ጊዜ ሁሉ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አለሁ ይበላችሁ። ፃድቁ_አባታችን_ስደተኛ_ልጆችህን_በምልጃህ_አስበን_እንደወጣን_አታስቀረን።አሜን።
Показать все...
#በዓታ_ለማርያም_ማለት #እመቤታችን የብጸሐት ልጅ ናት ( የስለት ልጅ) 3 ዓመት ሲሆናት አፍዋ እህል ሳይለምድ ሆድዋ ስው ሳይውድ ብለው እናት አባትዋ ውስደው ለቤተ እግዚአብሔር ስጡዋት ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ይባላል ✞ የእመቤታችን መልኳ እንደ ፅሀይ ሲያበራ አይቶ ይእችን የመስለች ውብ ብላቴና ተረክቤ እንደምን አድርጌ አኖራታለው ብሉ ደውል አስምቶ ካህናትን ስብስቦ የምግቧን ነግር ሲማከሩ መልአኩ ቅዱስ ፋኖኤል ዕብስት ስማያዊ ጸዋ ስማያዊ ይዞ ከላይ እርቦ ታየ ሊቀ ካህናቱ ዛሬ ሀብቴን ክብሬን በስው መካከል ሊገልጥልኝ መስለኝ ብሎ ሊቀበል ቀርበ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀበት ካህናቱም ሊቀበሉ ቀርቡ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው እህሩገ እስራኤልም ቀርቡ መልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው ሐና እያቄምም ሊቀበሉ ቀርቡመልአኩ ወደ ላይ ስቀቀባቸው ሐና ምን አልባት ለዚህች ብላቴና የውርደ መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን አይቀርምና እስኪ ትተሻት ጥቂት እልፍ በይ አሏት ትታት ትንሽ እልፍ ብትል መልአኩ ውርዶ ግራክንፉን አንጥፋ ቀኝ ክንፈን አጉናጸፏ በቆመ ብዕሲ አድርጉ መግቧት አርጓል "ምግቧ ሰማያዊ ነው ሲል ነው " የምግቧ ነግር ከተያዘልን ይህችን ውብ ብላቴ ከስው ጋራ ምን ያጋፈታል ኖሮዋ ከቤተ መቅደስ ይሁን ብለው ከቤተመቅደስ አግብተው አኖርዋት ሄደዋል እመቤታችንም መላእክት ሊቃነ መላዕክት አያጫውትዋት እያርጋጓት 12ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀምጠች ከእናት አባትዋቤት 3ዓመት በአጠቃላይ 15ዓመት ሲሆናት 🌿💖 አይሁዶች መቼም ለምቀኝነት አያርፉምና ይእች ብላቴና ለአቅመ ሔዋን ደርሳለች እሷን ያለ ጉልማሳ በቤተ መቅደሳችን አስገብተን ቤተ መቅደስሳችንን ታርክስብናለች እንዲያውም ጠረጠረናት ትውጣልን የጠየቀችሁን አድርግላት አሉት 🌿💖 ሊቀ ካህናቱም ዘካርያስ ከእመቤታችን ሄዶ ልጄ እንደምን ብለሽ መኖር ትውጃለሽ አላት እመቤታችንም ፍፃምተ ፈቃድ ፤ ትሁት ናትና እንግዲህ ከእግዚአብሔር በታች ያለከኝ አባት አንተ ነህ ውደ እግዚአብሔር አመልክትልኝ አለችሁ 🌿💖 ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት ጌታ ስራውን ያለ ምክንያት አይስራውምና ከነገደ ይሁዳ ሚስቱ የሞተችበትን በትር ስብስበ በቀዳማይ ሰዓታት ሌሊት ይዘህ ገብተ ስትፀልይበት እደር ከዚያ ምልክት አሳይካለው ለዕዚያ ስው ስጣት አለው 🌿💖 ሊቀ ካህናቱም በትር ቢስበስብ 9መቶ 1985 በትር ሆነ ያንን በቀዳማይ ስዓት ሌሊት ይዙ ገብቶ ሲጸልይበት ቢያድር + በዮሴፍ በትር ላይ የሎሚ ቅጠል አብባ አፍርታ ታየች + እርግብም በዮሴፍ እራስ ላይ አርፈለች + እጣም ቢጥሉ ለዮሴፍ ደርስው በሦስት ምስክር ለዮሴፍ ደርስች ሱባዬ ገብተን የስጠንክን ሱባዬ ገብተን እስክንቀበልክ ድርስ ጠብቃት ተንከባከባት አሉት የዮሴፍም ይዟት ውደ ቤቱ ሄደ። ከቤቱ አኑሯት ዘመኑ የንግድ ውቅት ነበርና ወደ ንግድ ለመሄድ ዕለቱን ተሸኝቶ አድሯል ዮሴፍ ከ3ወር በሀላ ተመለስ ዮሐንስ የሚባል ፍላስፍ ወዳጅ ነበርው ሊጠይቀው መጣ ጥቂት ተጨዋወተው ሊሄድ ተነሳ ሊሽኘው ውጣ ዮሴፍ ይህች ብላቴና ፀንሳለች ከአንተ ነው ወይስ ከሌላ አለው በምን አውቀው ቢሉ በፈልስፈና የጌታስ ፀንስ በፈልስፈና አይታውቅም ብሎ ሴቶች ሲፀንሱ ከቀደመው ይልቅ መልካቸው ያምራል ጡታቸው ይጦቅራል ከንፈራቸው ይደርቃል በዚያ አውቆ። 🌿💖 ዮሴፍም አር እኔ እንኳን ግቢር ቀርቶ ሐልኦም አልውቅባትም አለው እንግዲያውስ ስስነች ተብላ እንዳትውገርብህ ገብተህ ጠይቀ ተረዳ አለው። ዮሴፍም ውደ ቤት ተመልሶ ድንግል ማርያምን የፀነሽው ከማን ነው ብሎ ጠየቃት ድንግልም ከመንፈስ ቅዱስ ነው አለችሁ ከዚህ በፈት እንዲህ ተደርጉ አያውቅም እና ነገሩ እርቀቀበት ቢርቀው ከደጅ ወድቆ ይኖር የነበር ደርቅ ግንድ አለ ይሀንን አለምልማ አብባ አፈርታ አሳይታዋለች 🌿💖 በዚያውስ ላይ ዐፁቅ በባህሪያቸው እንዲያብቡ ንቦችን እንዲራቡ የሚያደርግ ጌታ እኔንስ በእቱም ድንግልና ፀንሼ በህቱም ድንግልና እንድውልድ ቢያደርገኝ ይሳነዋል ትላለክ??? ብላ ነገሩን እንደዚህ አስርድታዋለች 🌿💖 ይህም አልቀርም ውድያው ለባህል የሚውጡበት ጊዜ ደርስ የሴፍም ትቺያት ብሄድ ያደርገውን አውቆ ትቷት መጣ ይሎኛል ይዥትም ብሄድ ሴስነች ብለው በድንጋይ ወግርወ በእሳት አቃጥለው ይገድሉብኛል ምን ይሻለኛል እያለ ይህን ሲያውጣ ሲያውርድ መላከ እግዚአብሔር በህልም ታየው ተነጋገርው ዮሴፍ ከእርሷ የሚወለደው የአብ አካለዊ ቃል በግብር መንፈስ ቅዱስ ነውና አይዞህ አትፈሪ ይዘሀት ውጣ አለው ይዝዋት ውጥቷል ነገሩም አልቀርም " 🌿💖 ማየ ዘለፈአጠጧት " ይህ በኦሪቱ ልማድ ነው ባልየው መንፍሳዊ ቅናት ተነሳስቶ ከሌላ ውንድ ደርሳለች ብሎ ሚስቱን የጠርጠራት እንደሆነ " አሪፀ ስግምን ውሃ በገንቦ አሲዞ እራሷን አከናንቦ ወደ ቤተ መቅደስ ይዟት ይሄዳል ሊቀ ካህናቱ ከምህዋሩ ለይ ሆኖ ክንብንብሽን ግለጭው ይላታ እንዲህ ይግለጥብኝ በይ ሲያስኛት ነው 🌿💖 ከኦሪቱ የሚደገም የሚነበብ የሚጸለይ አንዳንድ አለ ሊቀ ካህናቱ ያንን ደግሞ ህራር እጣኑን አመደ ምስዋቶን በጥብጦ ባልሽ የጠርጠርሽን አድርገሽ ስውርሽ እንደሆነ ስውነትሽ ይበጥ ፣  ጉንሽ ይላጥ ፣  አጥንትሽ ይርገፍ አላደርግሽው እንደሆነ በውንድ ልጅ ይታርቅሽ ብሎ ይስጣታል እርሷም አሜን ውአሜን ብላ ተቀብላ ትጠጣዋለች ። 🌿💖 እርግማኑ ይደርግብኝ ምርቃኑ ይደርግልኝ ስትል ነው ባልዋ የጠርጠራትን አድርጋ ስውራ እንደሆነ ውድያው ስውነቷ ያብጣል ፣ጉንዋ ይላጣል ፣አጥንቷም ይርግፈል ያላደርገችው እንደሆነ በውንድ ልጅ ይታርቃታል በዚያ ልማድ ነው 🌿💖 ለእመቤታችንም ቢያጠጥዋት ፈትዋ ከፀሐይ ስባት እጅ አብርቶ ተገኘ ታየ ከዚያ የተስበስ ህዝቡ ይህችን ብላቴ ባላደርገችው ነገር በከንቱ አምተናታል ብለው የተናገሩት ለእርሷ ስጥቶ ውይትፀርይ ብሉ ተናገር። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሳለች እንዲህ ብላ ተናገርች መላኩ ቅዱስ ገብርኤል ከነገርኝ ነገር ቃል በቀር ሌላ እንደማላውቅ እግዚአብሔር ያውቃል ብላ ተናገርች ። ✞ ንፅህት ድንግል ማርያም አምላክን ለመውለድ የታመነች ናት ✞ አምላክን ለመውለድ የታመነች ድንግል ማርያም ብቻ ናት ✞ የስውን ልጅ ለማማለድ ድንግል ማርያም የታመነች ናት 🌿💖 ድንግል ሆይ !!! የማይውስነውን ውስንሽ የማይቻለውንን ቻልሽ ምንም ምንም ሊችለው የሌለውን ቻልሽ ምልዕተ ፀጋ ምልዕተ ክብር እመቤታችን የአብ አካላዊ ቃል ማደሪያው ድንግል እመቤታችን የማህፀኗ ፈሬ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለሙን ሁሉ አዳነ ከእኛ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን አጠፈ            🌿💖 እመቤቴ ማርያም ሆይ ዘር ያልወደቀባት ገበሬ ያልጣረባት የቅዱስ ቁርባንን አዝመራ ያፈራሽ ገራህት ሆይ፤ ከትጉሃን መላእክት ጋር ወደኔ ፈጥነሽ ነይ፡፡           🌿💖 ድንግል እመቤቴ ሆይ ብልህ አዋቂ የሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ያፈቅራል፤ ሰነፍ ልበ ቢስ ግን በከንቱ ይጠላሻል፤ ዳሩ ግን በመከረው የተንኮል ምክር ወጥመድ እሱ ራሱ ይጠመድ፡፡ 🌿💖 እመቤታችን ድንግል ማርያም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!! ድንግል ሆይ ከልጅሽ ከውዳጅሽ ከኢየሱስ ከክርስቶስ ለምኝልን ከሀጥያታችንን ያስተስርይልን ዘንድ  አሜን!!! ወስብሓት ለእግዚአብሔርው ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን
Показать все...
👍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ወር_በገባ_በ3_ቅድስት_በዓታ_ቅዱስ_ፋኑኤል_እና_አቡነ_ሊባኖስ_ወርኀዊ_መታሰቢያቸው_ነው። የቅዱሳን በረከት የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን
Показать все...
ስለረዳሽኝ እመቤቴ ስለረዳሽኝ እመቤቴ አወድስሻለው ከኔ ጋር ስለሆንሽ  እመቤቴ አወድስሻለው ምስጋኛሽን ይዤ ጠዋት ማታ ፊትሽ እቆማለው ምስጋናሽን ይዤ እመቤቴ ፊትሽ እቆማለው /አዝ/ ሀዘን ትካዜዬ ባንቺ ተወግዷል ልመና ፀሎቴ ሀሳቤ ተሟልቷል ያጣሁትን ነገር አግኝቼብሻለዉ በእናትነትሽ ዘወትር እመካለው /አዝ/ ባንቺ ደስ ይለኛል ያርፋል ልቦናዬ ሳሊለነ ብዬ ተቃና ጉዞዬ አልፈራም እንግዲህ ገደል እንቅፋቱ ይዘሽኛልና ድንግል አዛኚቱ /አዝ/ የተስፋ መብራቴ አጠፊም ከፊቴ መድኃኒቴ አንቺ ነሽ ለብቸኝነቴ ይቺ አለም ብትከፋ ፊቷን ብትመልስ ጨክነሽ አታውቂም እናቴ በኔስ /አዝ/ ምስክር አልሻም ከእንግዲህ በኋላ ነብሴ ትጮሀለች አማላጄ ብላ አወድስሻለው እናቴ እመቤቴ በኑሮዪ ሁሉ እስከለተ ሞቴ    ዘማሪ ሊቀ ልሳናት ቸርነት ሰናይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ❤
Показать все...
_ስለረዳሽኝ_እመቤቴ_በሊቀ_ልሳናት_ቸርነት_ሠናይ_selredashign_embete_by_Liqe_Lesanat.m4a5.05 MB
2
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ሰኔ_30_የመጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ_የልደት_በዓል_ነው#እንኳን_በሰላም_አደረሳችሁ_አደረሰን፡፡ ነፍሱ በምድር ላይ ለዕለት እንኳ ፈጽማ አድራ ስለማታውቅ (በሰማያዊ ስጦታ ብቻ ለከበረችው)፥ ገና ከእናቱ ማኅጸን ጌታውን ስላወቀ ስለ ዮሐንስ እንግዲህ ምን ልናገር እችላለሁ?'' (ቅዱስ ያሬድ: ድጓ ዘዮሐንስ) ለአዳኛችን መንገድ ጠራጊ በመሆኑ ልደቱ ብዙዎችን ላስደሰተ፥ ለቤተክርስቲያን ሙሽራዋ ሚዜው ለሆነ ለታላቁ ነቢየ ልዑል ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በዓለ ልደት እንኳን አደረሰን። #ጥበቃው_አይለየን🙏
Показать все...
3👍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
#በችግር_በመከራ_ላይ_ያላችሁ_ሁሉ_ቅዱስ_አማኑኤል_በዕለተ_ቀኑ_አለሁ_ይበላችሁ_ይበለን ለሀገራችን ሰላም ለእኛም ፍቅሩን ይስጠን አሜን። ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች  ሰሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡» #የተቀደስክ_አምላካችን_ቅዱስ_አማኑኤል_ሆይ_ለሐገራችን_ሰላም_እና_ፍቅር_ይስጠን_አሜን።
Показать все...
👍 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ነገ_እኮ_16_ኪዳነምህረት_ናት። እናት አለኝ የምታብስ እንባ አያታለሁ ስወጣ ስገባ ኪዳነምህረት (3)አምባ መጠጊያ ናት" ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን። በቃልኪዳንዋ ሀገራችንን ትጠብቅልን አሜንበጨነቃችሁ ጊዜ ሁሉ እናቴ እመቤቴ  ቅድስት ኪዳነ ምህረት አለው ትበላችሁ።
Показать все...
🙏 7
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ሰኔ_12_ለቅዱስ_ሚካኤል_አመታዊ_ክብረ_በዓል_ነው። እንኳን ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን:: ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ (ት-ዳ÷10 https://t.me/Reading100T https://t.me/Lijmatyas
Показать все...
🙏 4🥰 1
❤️ ​​​​#ሰኔ_12_የቅዱስ_ሚካኤል_ዓመታዊ_በዓል ‼️ #እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን። 👉 እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። •• 👉  በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ •• 👉 ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን ፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ •• 👉 ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ •• 👉 ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ •• 👉 ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ •• 👉 በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ •• 👉 ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “ የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ? ” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ •• 👉 ለጊዜው “ በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም ” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ ድረስልኝ ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ •• 👉 የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ 👉 ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ •• 👉 ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ •• 👉 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን ፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን ፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
Показать все...
00:03
Видео недоступноПоказать в Telegram
3.64 KB
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.