Bashewam Primary & Junior School 1-8
Открыть в Telegram
2 747
Подписчики
-224 часа
+207 дней
+4230 день
Архив постов
የተከበራችሁ ወላጆች፡2018ዓ.ም:ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት የጀመርን፡መሆኑን እየገለፅን፡ቦታ ሳይያዝባችሁ፡በወቅቱ መጥታችሁ እንድትመዘገቡ፡በአክብሮት እንገልፃለን።
ባሸዋም ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ እና ፤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የተማሪዎች የክፍል ውስጥ ስነ-ምግባር ደንብ (Ground Rule)
➢ ዩኒፎርም መታወቂያና አስፈላጊውን የትምህርት ቁሳቁስ አሟልቶ በሰዓቱ ትምህርት ቤት መገኘት(አለማርፈድ ፤አለመቅረት)፣ በአለባበስና በፀጉር አቆራረጥ ትምህርት ቤቱ ያስቀመጠውን ደንብ ማክበር፤
➢ በሰንደቅ ዓላማ ስነስርዓት ላይ በሰዓቱ በመገኘት(ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት) ብሄራዊ መዝሙር በመዘመር ተገቢውን ክብር መስጠት፤ በሚኒ ሚዲያ የሚተላለፋ መልዕክቶችን በጥሞና ማዳመጥ፤ ለወላጅ የሚተላለፉ መልዕክቶችን በወቅቱ ማድረስ
➢ የክፍል ፅዳትንና ፀጥታን በመጠበቅ ለመማር ማስተማሩ ሂደት ሰለማዊና ምቹ ሁኔታን መፍጠር፤ ከተመደቡበት ክፍል ውጭ አለመግባት፣የሚገቡ ካሉ ለመምህራን ማሳወቅ
➢ የግል የጋራ እና ማንኛውንም የትምህርት ቤቱን ንብረት ከጥፋት መከላከል መጠበቅና በአግባቡ መጠቀም፤ በግዴለሽነት ለሚበላሹ ንብረቶች በግልና በጋራ የመጠገን የመተካት ኃላፊነት መወሰድ፡፡ አጥፊዉን ለክፍል ሃለፊ መምህር ማሳወቅ
< ➢ ምክንያታዊ መሆን በህግ የበላይነት ማመን፤ እርስ በርስ መከባበር መቻቻል፣ ለመምህራንና ሰራተኞች ተገቢውን ክብር መስጠት፣ ከእርስ በርስና ከቡድን ጠብ መራቅ፤ ትምህርት ቤት ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ማራመጃ አለመሆኑን መገንዘብ
➢ ማንኛውንም ጎጂ አደንዛዥና ሱስ አስያዥ የሆኑ ነገሮችን እንዲሁም ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶችን ይዞ ወደ ትምህርት ቤት አለመምጣት፣ አለመጠቀም፤ ሀገራዊ እሴትን ከሚሸረሽሩ መጤ ባህሎችና ጎጂ ልማዶች መራቅ መቆጠብ፤
➢ የግል የክፍልና የግቢ ንፅህናን መጠበቅ፣ በማንኛውም ወረርሽኝ በሽታ ላለመያዝ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ፤ የጤና ባለሙያዎችን ምክር ተግባራዊ ማድረግ፤
► በግልና በቡድን በክፍል ውስጥ እንዲሁም በክበባት ንቁ ተሳትፎ በማድረግና በመተጋገዝ መምህራን የሚሰጡአቸውን የትምህርት ተግባራት በወቅቱ በማከናወን ውጤትን ማሻሻል፡፡ ለሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ትኩረት መስጠት
➢ በሶስትዬሽ ስምምነት መሰረት የተቀመጠውን የውጤት ማሻሻያ ግብ ለማሳካት ሁል ጊዜ መትጋት የግል ጥረት ማድረግ ፤ የንባብ ባህልን ማዳበር፤
➢ በትምህርት ሰዓት ያለምክንያት በኮሪደርና በግቢ ውስጥ አለመዘዋወር መምህር በማይኖርበት ጊዜ በክፍል ውስጥ ሆኖ በግልና በቡድን ማጥናት፤ መረዳዳት
➢ ከኩረጃ ከስርቆት እና ከመሳሰሉት አስነዋሪ ተግባራት መቆጠብ፤
➢ በትምህርት ቤቱ ማህበረሰብና በተቋሙ ላይ ጉዳት ሊያደርስ የሚችሉ ነገሮችን ሲያዩ ወይም ሲመለከቱ መከላከል ወይም ለሚመለከተው ክፍል ፈጥኖ ማሳወቅ፤
➢ በበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ አቅም በፈቀደ መጠን መሳተፍ፤
➢ በልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀቶች በንቃት በመሳተፍ፤ ለትምህርት ቤቱ መሻሻል የሚረዳ ማናቸውንም የራስን አስተዋፅኦ በተነሳሽነት ማበርከት፤
➢ ሌሎች የትምህርት ቤቱ ህግና ደንቦችን እንዲሁም በትምህርት ቢሮ የወጣውን የተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ ማክበር፤
ለተማሪዎቻችን ዉጤትና ስነ ምግባር መሻሻል በጋራ እንስራ!!
ባሸዋም ትምህርት ቤት ፡ ትውልድ እንቀርፃልን፡ ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ ነን!
Bashewam School Administrator
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🌼🌼🌼🌼🌼🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ባሽዋም ት/ቤት ትምህርት ሚኒስቴር ባወረደዉ የትምህርት ካላንደር መሰረት ዛሬ መስከረም 05/2018 ዓ.ም የ2018 ዓ.ም የት/ት ዘመን ት/ቤቶች ተከፍተዉ ትምህርት የሚጀመርበትን ቀን የት/ቤቱ አመራር, የአስተዳደር ሰራተኞች, መምህራን, ተማሪዎች እና ወላጆች በተገኙበት በደማቅ ስነስርዓት ተከብሯል::
👉.በስነስርዓቱ የተከናወኑ ሂደቶች::
✅ 1. በት/ቤቱ ባለቤ እና ዋና አስተዳዳሪ አቶ በርታ ስፍር እና በት/ቤቱ አመራር አካላት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ተካሂዷል
✅.2 የአዲስ ተማሪዎች እና የነባር ተማሪዎች እንዲሁም የአዲስ መ/ራን እና የነባር መ/ራን የእንኳን ደህና መጣችሁ የችቦ መብራት ርክክብ ስነስርዓት ተካሂዷል
✅.3.ተማሪዎች ከቤት ወደ ት/ቤት ሲመጡና በትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ሊከተሏችዉ የሚገቡ የት/ቤቱ ሕግና መመሪያዎች
✅.4 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች የዲስፕሊን መመሪያ 150/2016 ላይ የሰፈሩ የተማሪዎች መብትቶች እና ግዴታዎች እንዲሁም መብታችዉን በአግባቡ በማይጠቀሙ እና ግዴታችዉን በማይወጡ ተማሪዎች ላይ የሚወሰዱ ተጠያቂነትና የዲስፕሊን ቅጣቶች ተማሪዎች እንዲያቋችዉ በቂ ግንዛቤ ተፈጥሮ የእለቱ ትምህርት እጅግ በጣም ጤናማ በሆነ ሂደት ተጀምሮ ተጠናቋል::
ባሸዋም ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ እና ፤ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የተማሪዎች የክፍል ውስጥ ስነ-ምግባር ደንብ (Ground Rule)
➢ ዩኒፎርም መታወቂያና አስፈላጊውን የትምህርት ቁሳቁስ አሟልቶ በሰዓቱ ትምህርት ቤት መገኘት(አለማርፈድ ፤አለመቅረት)፣ በአለባበስና በፀጉር አቆራረጥ ትምህርት ቤቱ ያስቀመጠውን ደንብ ማክበር፤
➢ በሰንደቅ ዓላማ ስነስርዓት ላይ በሰዓቱ በመገኘት(ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት) ብሄራዊ መዝሙር በመዘመር ተገቢውን ክብር መስጠት፤ በሚኒ ሚዲያ የሚተላለፋ መልዕክቶችን በጥሞና ማዳመጥ፤ ለወላጅ የሚተላለፉ መልዕክቶችን በወቅቱ ማድረስ
➢ የክፍል ፅዳትንና ፀጥታን በመጠበቅ ለመማር ማስተማሩ ሂደት ሰለማዊና ምቹ ሁኔታን መፍጠር፤ ከተመደቡበት ክፍል ውጭ አለመግባት፣የሚገቡ ካሉ ለመምህራን ማሳወቅ
➢ የግል የጋራ እና ማንኛውንም የትምህርት ቤቱን ንብረት ከጥፋት መከላከል መጠበቅና በአግባቡ መጠቀም፤ በግዴለሽነት ለሚበላሹ ንብረቶች በግልና በጋራ የመጠገን የመተካት ኃላፊነት መወሰድ፡፡ አጥፊዉን ለክፍል ሃለፊ መምህር ማሳወቅ
< ➢ ምክንያታዊ መሆን በህግ የበላይነት ማመን፤ እርስ በርስ መከባበር መቻቻል፣ ለመምህራንና ሰራተኞች ተገቢውን ክብር መስጠት፣ ከእርስ በርስና ከቡድን ጠብ መራቅ፤ ትምህርት ቤት ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ማራመጃ አለመሆኑን መገንዘብ
➢ ማንኛውንም ጎጂ አደንዛዥና ሱስ አስያዥ የሆኑ ነገሮችን እንዲሁም ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶችን ይዞ ወደ ትምህርት ቤት አለመምጣት፣ አለመጠቀም፤ ሀገራዊ እሴትን ከሚሸረሽሩ መጤ ባህሎችና ጎጂ ልማዶች መራቅ መቆጠብ፤
➢ የግል የክፍልና የግቢ ንፅህናን መጠበቅ፣ በማንኛውም ወረርሽኝ በሽታ ላለመያዝ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ፤ የጤና ባለሙያዎችን ምክር ተግባራዊ ማድረግ፤
► በግልና በቡድን በክፍል ውስጥ እንዲሁም በክበባት ንቁ ተሳትፎ በማድረግና በመተጋገዝ መምህራን የሚሰጡአቸውን የትምህርት ተግባራት በወቅቱ በማከናወን ውጤትን ማሻሻል፡፡ ለሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ትኩረት መስጠት
➢ በሶስትዬሽ ስምምነት መሰረት የተቀመጠውን የውጤት ማሻሻያ ግብ ለማሳካት ሁል ጊዜ መትጋት የግል ጥረት ማድረግ ፤ የንባብ ባህልን ማዳበር፤
➢ በትምህርት ሰዓት ያለምክንያት በኮሪደርና በግቢ ውስጥ አለመዘዋወር መምህር በማይኖርበት ጊዜ በክፍል ውስጥ ሆኖ በግልና በቡድን ማጥናት፤ መረዳዳት
➢ ከኩረጃ ከስርቆት እና ከመሳሰሉት አስነዋሪ ተግባራት መቆጠብ፤
➢ በትምህርት ቤቱ ማህበረሰብና በተቋሙ ላይ ጉዳት ሊያደርስ የሚችሉ ነገሮችን ሲያዩ ወይም ሲመለከቱ መከላከል ወይም ለሚመለከተው ክፍል ፈጥኖ ማሳወቅ፤
➢ በበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ አቅም በፈቀደ መጠን መሳተፍ፤
➢ በልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀቶች በንቃት በመሳተፍ፤ ለትምህርት ቤቱ መሻሻል የሚረዳ ማናቸውንም የራስን አስተዋፅኦ በተነሳሽነት ማበርከት፤
➢ ሌሎች የትምህርት ቤቱ ህግና ደንቦችን እንዲሁም በትምህርት ቢሮ የወጣውን የተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ ማክበር፤
ለተማሪዎቻችን ዉጤትና ስነ ምግባር መሻሻል በጋራ እንስራ!!
ባሸዋም ትምህርት ቤት ፡ ትውልድ እንቀርፃልን፡ ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ ነን!
Bashewam School Administrator
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
