Bashewam Primary & Junior School 1-8
Открыть в Telegram
2 749
Подписчики
+624 часа
+367 дней
+4630 день
Архив постов
👉ምክር ለተፈታኞች❤️
👉ተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው ፈተና በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ለእናንተ ወሳኝ ጊዜ ነው። እስካሁን ትምህርታችሁን እያጠናችሁ ቆይታችኋል። መልካም ነው። ነገር ግን በፈተና ወቅት የምታከናውኗቸው ተግባራትም የጥናታችሁን ያህል ውጤታችሁ ላይ ተጽዕኖ አላቸው። ስለዚህ በዚህ ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባችሁና ምን ማድረግ እንደሌለባችሁ ጠንቅቃችሁ ማወቅ ይጠበቅባችኋል። ለዚህም ይረዳችሁ ዘንድ የሚከተሉትን ምክሮችን ከወዲሁ ተረድታችሁ ለመተግበር ዝግጁ ሁኑ!
⓵ በዋዜማው ስልክ መዝጋትና ከሚረብሹ ነገሮች ራስን ማራቅ ያስፈልጋል። ስልካችሁን መዝጋት ሀሳባችሁን ሊሰርቁ ከሚችሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች መራቅ ይገባችኋል። በዚህ ወቅት ትኩረታችሁን ፈተናችሁ ላይ ብቻ አድርጉ፤
⓶ በቂ እንቅልፍ ተኙ። በፈተና ዋዜማ ለማንበብ ብላችሁ በፍጹም አታምሹ። ባጭሩ በዚህ ቀን ተጨማሪ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ ተጨማሪ ሰዓት መተኛት የተሻለ ዉጤት አለው። በቂ እንቅልፍ አለመተኛት በፈተና ወቅት ለድብርትና ለራስ ምታት ሊዳርግና ሥራችሁን ሊያበላሽ ይችላል። ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት ከባድ ምግቦችን አለመመገብ፤ ብዙ ቡና አለመጠጣት፤ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮችን አለመውሰድ ይመከራል፤
⓷ ጠዋት ማልዶ መነሳት: በጊዜ ተነስቶ መዘጋጀት ከመቻኮል ጋር ተያይዞ ከሚመጣ መታወክ ያድናል። በተጨማርም ወደፈተናው አዳራሽ በጊዜ ለመድረስ ያስችላል፤
⓸ ቁርስ በአግባቡ መብላት: በፈተና ወቅት ቁርስ አለመብላት አእምሮአችን የሚፈልገውን ያህል ኃይል እንዳያገኝ ስለሚያደርግ ለማሰብ አቅም እንዲያንስ ያደርጋል። ስለዚህ ቀለል ያሉ ምግቦችን ተመግባችሁ መሄድ ይኖርባችኋል። ከባድ ምግቦችን መመገብ ደግሞ አእምሮአችን ምግብ የመፍጨት ሥራ ላይ ብቻ እንዲወጠር ስለሚያደርግ ድካምና እንቅልፍ ያመጣል፤
⓹ ወደ መፈተኛ ቦታው ፈተናው ከሚጀምርበት ሰዓት በፊት ቀድሞ መድረስ ያስፈልጋል። ይህም ለመረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው፤
⓺ ከቤት ስትወጡ የፅህፈት መሳሪያዎቻችሁንና የመታወቅያ ካርዳችሁን መያዛችሁን እርግጠኛ ሁኑ። ይህም ከመንገድ ከመመለስና ከማርፈድ ያድናችኋል። ትርፍ እርሳሶችን እና የእርሳስ መቅረጫዎች መያዝ በጣም አስፈላጊ ነው፤
⓻ ወደ ፈተና አዳራሽ ከመግባት በፊት ወደ መፀዳጃ ቤት መሄድ መልካም ነው። ምናልባት የፈተናው ሰዓት ረዥም ቢሆንና ሽንት ቢይዛችሁ መጨናነቅን ያመጣል። አቋርጣችሁ መውጣት ላይፈቀድላችሁ ይችላል፤
⓼ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ስማችሁን በአግባቡ መጻፋችሁን እርግጠኛ ሁኑ። አንድ ፊደል እንኳን ብትሳሳቱ ኋላ የት/ት ማስረጃችሁ ላይ ስለሚቀመጥ ለማስቀየር ዋጋ ያስከፍላል፤
⓽ መመሪያዎችን (instructions) በአግባቡ ማንበብና መተግበር ያስፈልጋል። በእያንዳዱ ፈተና ወረቀት ላይ ወይም የፈተናው ክፍሎች ላይ የሚሰጡትን መመሪያዎች በአግባቡ ማንበብና መተግበር ይኖርባችኋል፤
⓾ አትደንግጡ! በደንብ ተንፍሱ! ብዙ ኦክስጂን ወደ ውስጣችን ማስገባት ብዙ ምግብ እንዲቀጣጠልና ኃይል እንዲመረት ስለሚያደርግ ጉልበትና ድፍረት ይጨምርላችኋል፤
⓬ አንዱ ጥያቄ ከከበዳችሁ ዝለሉት፤ አንድ ጥያቄ ላይ ተጠምዳችሁ ብዙ ጊዜ የምታጠፉ ከሆነ ቀጥለው ለሚጠብቋችሁ ጥያቄዎች ጊዜ ሊያጥራችሁ ይችላል። ስትዘሉት ግን የጥያቄ ወረቀቱ ላይ ምልክት ማድረጋችሁን እንዲሁም መልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ከተሰጡት አማራጮች አንዱን መልስ በግምት ማጥቆራችሁን አትርሱ። አጥቁሮ ማለፍ ምናልባት በኋላ የተሰጠው ጊዜ ቢያልቅና ወደ ጥያቄው መመለስ ቢያቅታችሁ መልስ መስጫ ቦታው ባዶ ሆኖ እንዳይቀር ያደርጋል፤
⓭ ቶሎ ለመውጣት አትቸኩሉ፤ ምንም አይጠቅማችሁም፤ ሰዓታችሁን አሟጥጣችሁ መጠቀማችሁን፤ ሁሉንም ጥያቄዎች በአግባቡ መመለሳችሁንና ማጥቆራችሁን አረጋግጡ። ጊዜ ቢተርፋችሁ ጥያቄዎቹን ለመከለስ ተጠቀሙበት፤
⓮ ያልገባችሁ ማንኛውንም ነገር ሲኖር ፈታኞችን ለመጠየቅ አትፍሩ (ከመልስ በስተቀር😉)፤
⓯ ልክ የፈተና ወረቀቱን ከመለሳችሁበት ጊዜ ጀምሮ የዚያ ትምህርት (subject) ነገር ማክተሙን በመገንዘብ ለቀጣዩ ፈተና እራስን ማዘጋጀት ይገባል። እንጂ፤ ስላለፈው ፈተና እያሰላልሰሉ መጨነቅ ለቀጣዩ ፈተና በምታደርጉት ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል።
መልካም የቅድመ ዝግጅት ጊዜ ይሁንላችሁ !!!
👉ዛሬ በቀን 02/10/2018 ዓ. ም በት/ቤት ደርጃ ለ8ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ተፈኝ ተማርዎች ስለትምህርት ቱሩፋቶች, ስለ ስነ-ልቦና ዝግጅት,በራስ የመተማመን ሞራል ማነሳሳት እና በፈትና ወቅት መተግበር ስላለበት የፈተና ህግና ደንብ መመሪያ ዙሪያ ገለፃ(orientation)ተሰጥቷል::❤️
ማስታወቂያ
ለ6ኛ ክፍል ተማሪ በሙሉ::
👉የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ረቡእ በቀን 03/10/2018ዓ.ም እስከ 9:00 ሰዓት የፈተና ግብረመልስ ወረቀት እና በት/ቤት ደረጃ ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ ሁላችሁም እንድትገኙ በድጋሜ እናሳስባለን::
👉ማሳሰቢያ:-በተለያዩ ምክንያት ክሊራንስ ያላጠናቀቃችሁ እና ኦርጂናል Admission Card ያልወሰዳችሁ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እስከ ቀን 03/10/2018 ዓ. ም በአካል በመቅረብ አጠናቃችሁ እንድትወስዱ በጥብቅ እናሳስባለን::
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
ማስታወቂያ
ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪ በሙሉ::
👉የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ማክሰኞ በቀን 02/10/2018ዓ. ም እስከ 9:00 ሰዓት የፈተና ግብረመልስ ወረቀት እና በት/ቤት ደረጃ ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ ሁላችሁም እንድትገኙ እያሳሰብን:-
👉የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ሰኞ በቀን 01/10/2018ዓ.ም ፈተና ካጠናቀቃችሁ በኃላ የፈተና ግብረመልስ ወረቀት እና በት/ቤት ደረጃ ኦረንቴሽን የሚሰጠዉ ረቡእ በቀን 03/10/2018ዓ. ም ስለሆነ ሁላችሁም በተጠቀሰዉ ቀን እንድትገኙ ከወዲሁ እናሳዉቃለን::
ማሳሰቢያ:-በተለያዩ ምክንያት ክሊራንስ ያላጠናቀቃችሁ እና ኦርጂናል Admission Card ያልወሰዳችሁ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እስከ ቀን 03/10/2018 ዓ. ም በአካል በመቅረብ አጠናቃችሁ እንድትወስዱ በጥብቅ እናሳስባለን::
👉ማሳሰቢያ:-ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች በሙሉ::
ከላይ በወጣው የሞዴል ፈተና መስጫ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት👉 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከግንቦት 27- ሰኔ 01/2018ዓ. ም ሦስቱንም ቀን ጠዋት እና ከሰዓት ፈተና ያላችሁ ስልሆነ እስከ 9:00 ሰዓት ከግቢ ሳይውጡ የሚቆዩ መሆኑን እየገለፅን 👉ለ8ኛ ከፍል ተማሪዎች አርብ ግንቦት 28/2018ዓ. ም ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ላይ ፈተናው እንዳተጠናቀቀ ወደ ቤት የሚለቀቁ ስለሆነ ዉድ-ወላጆች ይህን አውቃችሁ እንድትረከቧችዉና ክትትል እንድታደርጉ እያሳሰብን በሰርቪስ መሄድ የምትፍልጉ ተማሪዎች ካላችሁ ግቢ ዉስጥ ቆይታችሁ 9:00 ሰዓት ላይ መሄድ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን::
ማሳሰቢያ:-ክፍያን በተመለከተ ክሊራንስ ያላጠናቀቃችሁ አንዳንድ ተማሪዎች 👉ከፈተና በፊት ክሊራንሰ አጠናቆ በእጅ መያዝ እጅግ ወሳኝ ስልሆነ ነገ ረቡእ በቀን 26/09/2018ዓ. ም የፋይናስ ክፍል እስከ 6:30 ክፍት ስለሆነ በአካል በመቅረብ እንድታጠናቅቁ እናሳዉቃለን::
BEPS. Bashewam Primary & Junior School 1-8:
ለባሸዋም ትምህርት ቤት ወላጆችና ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡
፡
ውድ ወላጆች ፡ ከመንግስት በወረደው አቅጣጫ መሰረት ከሰኞ ግንቦት 24/2018 እስከ ረቡዕ ግንቦት 26/2018ዓም ድረስ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እያሳወቅን፡ ከሀሙስ ግንቦት 27/2018ዓም ጀምሮ መደበኛ ትምህርት የሚቀጥል እና የ6ኛ ና 8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና ግንቦት 27/2018ዓም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ:- የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት (Tutorial class) የሚሰጥ ስለሆነ ሁላችሁም አንድትገኙ እናሳስባለን:: ግንቦት 21/2018ዓም
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
