cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ሳተናው ሚዲያ

Больше
Рекламные посты
1 156
Подписчики
Нет данных24 часа
-57 дней
-2430 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

(ከላይ የቀጠለ .................👆👆👆) አላማውም የኦሮሚያ ልዮ ሃይልን የመከላከያና የፌደራል ፖሊስን ዮኒፎርም በማልበስ ካምፕ በማስገባት አዲስ አበባ ውስጥ የሚፈጠር ችግር ሲኖር እነዚህ ብቻ እንዲሰማሩና ጥቃት እንዲፈፅሙ ለማድረግ ታስቦ እንደሆነ ከውስጥ የወጣው መረጃ ያስረዳል:: መከላከያ ከአማራ ህዝብ ጋር ውጊያ ከተጀምረ እንዴት መዋጋት እንዳለባቸው ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ መከላከያው ህዝቡን እንዴት መዋጋት እንደሚችል ስትራቴጂ እያወጡ መሆናቸውም ተደርሶበታል፡፡ ከአማራ ጋር ጦርነት ከተጀመረ ህዝቡ በሁሉም አቅጣጫ መከላከያውን ሊገጥመውና ሊያሸንፈው ስለሚችል መጀመሪያ የአማራ ብልፅግናን የፖለቲካ ሃይል ከኛ ጋር እንዲቆም ማድረግ ያስፈልጋል የሚል ውሳኔ መወሰናቸውን መረጃዎቹ ጠቁመዋል::
Показать все...
በአዲስ አበባ ከንቲባዋን ጨምሮ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ሴራ እየተሰራ መሆኑ ታውቋል ..‼️‼️           በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቀጥተኛ ትእዛዝ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ 450.000 በሚሆኑ የኦሮሚያ ፖሊሶች ሊተካ ነው ተብሏል፡፡ ይህንን ህገ-መንግስቱንም ሆነ የአዲስ አበባን ቻርተር የጣሰውን አካሄድ፣ ሊቃወሙ ይችላሉ በሚል መነሾም፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችን አስመልክቶ አዲስ መረጃ ወጥቷል፡፡ እንደ መረጃው ከሆነ፣ በቀን ሚያዝያ 10 ቀን 2015አ.ም.  ተፅፎ፣ ለከፍተኛ የመከላከያ አመራሮች ከአብይ አህመድ ቢሮ አዲስ ሰርኩላር የተላከ ሲሆን፤ በዚህ መመሪያ መሰረትም፣ እያንዳንዱ ከፍተኛ የመከላከያ አዛዥ ጠባቂዎች ከደህንነትና ከጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ብቻ እንደሚመደብላቸው መመሪያ ወርዷል:: ከዛ ውጪ የራሳቸውን ጠባቂ መመደብ እንደማይችሉ መመሪያው ያስረዳ ሲሆን፣ ይህም የሆነበት አንዱ ምክንያት ጠቅላይ ሚንስትሩ በወታደራዊ አዛዦቻቸው ላይ እምነት ስለሌላቸው እና እንቅስቃሴያቸውን ለመሰለል በመፈለጋቸው እንደሆነ ተመልክቷል:: በዚህ ሰርኩላር የተነሳም፣ መከላከያው ውስጥ ትልቅ አለመተማመንና ውጥረት መስፈኑ ተሰምቷል:: በተያያዥ መረጃም፣ በመከላከያ እና በፌደራል ፖሊስ ውስጥ የተዋቀረ አዲስ ቡድን መፈጠሩ ተሰምቷል፡፡የዚህ ቡድን ዋና አላማ አዲስ አበባን መቆጣጠር በመሆኑ፣ ለዚህ ቡድን ይሆናሉ ተብለው ከመከላከያ እና ከፌደራል ፖሊስ የተመለመሉት በሙሉ ስርዓቱን ይጠብቃሉ ተብለው የታመነባቸው የኦህዴድ አባላት መሆናቸው ታውቋል::
Показать все...
#ባሩድ_ሲሸተው_ከመፍራት_ይልቅ_ይነሳል‼️ አማራ በሚዲያ ማሥፈራሪያ የሚፈራ ቢሆን ኑሮ እናንተ ጠላቱ ሳትሆኑ እኛ ለማንቃት ብለን "ኦነግ እና ትህነግ በጅምላ ሊያጠፉህ ነው" እያል ስንለፍፍ የሚመጣውን ፈርቶ ቀድሞ ለማጨናገፍ ይነሳ ነበር። ስለዚህ ፊልድ ማርሻሉ፣ ጠቅላዩ፣ ወዘተ ለማስፈራራት ብላችሁ የምታወሩት ፍፁም አይዝላችሁም። ሥሪቱ የተለዬ ህዝብ ነው። እንገልሃለን አርፈህ ተቀመጥ፣ ትጥቅ ፍታ ወዘተ የሚሉት ማስፈራሪያዎች ጭራሽ አልያዙም። ፍርሃት ከየት አባቱ ይምጣ❓ በተቃራኒው አማራ የተኩስ ድምፅ ሲሠማ፣ የባሩድ ሽታ ሲሸተው ከመፍራት ይልቅ ይነሳል። የጥንቱን ተውትና አማራ ለዓመታት አልነሳ ብሎን እንዳልነበር የሴራ ጦርነት ስትከፍቱበት አይደል የተነሣው❓በፊት ተሣሥቶ ከእናንተ ጎን ተሠልፎ፤ ቆይቶ ከእናንተ ተፋቷል። ጦርነት ባትከፍቱብን ይኸን ያህል ፋኖ ይፈላ ነበር❓ በየቀኑ እየፈላ ነው። በአንድ በኩል እኛ ማሥነሣት ያልቻልነውን እንዲነሳ አድርጋችሁታልና ባለውለታችን ናችሁ። ጭቆናው ሲጠነክር አማራ ይጠነክራል። የአማራ ሥሪት ከዓለም የተለዬ ነው በጭቆና ብዛት ከመሠበር ይልቅ የሚጠነክርና የሚፋፋ ነው። የዓለም አንድን ህዝብ የማጥፊያ ሎጂክ ለአማራ አይሠራም ማለት ነው። በልክ ብታደርጉት ተጠቃሚ እናንተው ናችሁ። የት እንደምትገቡ እናያለን።
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
#BREAKING ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ በመታየቷ የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ አርብ ይውላል።እንኳን 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ምንጭ፦ Haramain Sharifain
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ሱዳን #ኢትዮጵያ የሱዳን ጋዜጦች የኢትዮጵያን ጦር የተመለከተ ሀሰተኛ ዜናዎች ሲያሳራጩ ነበር። የተሰራጨው ዜና ምን ነበር ? ከትላንት ምሽት ጀምሮ የሱዳን ሚዲያዎች በተለይም በ " አልሱዳኒ ጋዜጣ " የኢትዮጵያ ጦር በሱዳን ላይ ጥቃት ከፍተ የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲያሰራጩ ነበር። አል ሱዳኒ ፤ በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ ጦር በታንክ፣ በታጠቁ ተሽከርካሪዎች እና በብዙ እግረኛ ወታደሮች በመታገዝ በ " አልፋሽቃ አል-ሱግራ " ላይ ወረራ እና ጥቃት ፈጽሟል ፤ የሱዳን ጦርም ጥቃቱን በመመከተ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሷል ሲል ነው ሀሰተኛ መረጃ ያሰራጨው። ይህንን ዜናም በርካቶች ወዲያውኑ ሲቀባበሉት እና ለብዙሃኑ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ሲያዳርሱ ነበር። ይህ መሰል ዜና እንዲሰራጭ ያደረገው የ " አልሱዳኒ " ጋዜጠኛ በትክክለኛ የፌስቡክ ገፁ የተሰራጨው ዜና ትክክል እንዳልሆነ በመግለፅ አንባቢውን ይቅርታ ጠይቋል። " ዜናው እውነት አይደለም " ያለው ይኸው ጋዜጠኛ " ወረራም አልነበረም ፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ ጦር መካከልም ግጭት አልነበረም " ብሏል። የሰራው ሀሰተኛ ዜና በተፈጠረው ግራ መጋባትና መደናገር እንዳዘነ ይኸው ጋዜጠኛ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ፅፏል። ሱዳን እጅግ በጣም ሰፊ የኢትዮጵያ መሬትን በኃይል ተቆጣጥራው እንደምትገኝ ይታወቃል። ይህን ያደረገችውም በትግራይ ክልል ጦርነት መነሳቱን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም ነበር። ከዚህ በኃላም ኢትዮጵያ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የድንበር ውዝግብ በጠረጴዛ ዙሪያ በሰላም እና በንግግር መፈታት እንዳለበት በተደጋጋሚ አቋሟን ስትገልፅ ቆይታለች። ከሰሞኑን በሱዳን የውስጥ ኃይሎች መካከል በተፈጠረው ጦርነት ሳቢያ ሱዳን ከገባችበት ከፍተኛ ትርምስ እንድትወጣ ለማድረግ ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደምታደርግ አሳውቃለች። ግጭት ውስጥ ያሉት የሱዳን ኃይሎችም ግጭት እንዲያረግቡ የሰላም ጥሪ ያቀረበችው ኢትዮጵያ ላለው ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት አዲስ አበባ በሯ ሁሌም ክፍት መሆኑን አቋሟን ገልጻለች።
Показать все...
Показать все...
ሰበር ዜና፦ ሚስጥራዊው ስብሰባ ተጋለጠ/ፓለቲከኛው ስልጣኑን ለቀቀ

Feta Daily/Nisir International Broadcasting/Blue Nile tv/Ethio 360 media/Ancur media

Фото недоступноПоказать в Telegram
ብርሃኑ ጁላ ተጋለጠ ቦሌ ሆምስ አካባቢ ከሚኖርበት ልጥጥ ቪላ ቤት አጠገብ 3ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከሊዝ ነፃ ተደርጎ የወሰደበት መረጃ በድብቅ ወጥቷል።ብርሃኑ ጁላ "ሸገር ሲቲ" ተብሎ በተከለለው የአዲስ አበባ ክፍል ከ6ሺህ በላይ ካሬ ሜትር ተጨማሪ ቦታ እንደወሰ ተረጋግጧል።በገንዘብ ሲተመን በቢሊየን እንደሚያወጣ ተገልጿል። ሰፊው የመከላከያ ሠራዊት አባላት 2ሺህ ብር ባልሞላ ደሞዝ በእርስ በርስ ጦርነት ከ6 መቶሺህ በላይ ሠራዊት እንዲያልቅ ያደረጉት ለዚህ መሆኑን መረዳት አለበት ተብሏል።ከትግራይ ጦርነት የተረፈው መከላከያ ሠራዊት በቀጣይ ከፋኖ እና ከአማራ ልዮ ኃይል ጋር ዳግም እንዲተላለቅ አለቃው ዐብይ እና ብርሃኑ ጁላ የሚደነፉት የራሳቸውን የዘረፉት ሀብት ለማስጠበቅ መሆኑን አውቆ የድሃ ልጅ የሆነው መከላከያ ሠራዊት ከወንድሞቼ ጋር አልዋጋም በማለት ነፈጡን ይዞ እየከዳ አንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።ሲከዳ የሚቀበለው ሰፊ የፋኖ አደረጃጀት መኖሩን ማወቅ አለበት ተብሏል።
Показать все...