ru
Feedback
Mark Tech Info | Mark Technology Information

Mark Tech Info | Mark Technology Information

Открыть в Telegram

Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot

Больше
6 218
Подписчики
-324 часа
-337 дней
-31730 день
Архив постов
#AASTU የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ፣ በሁለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በቅድመ ምረቃ በመደበኛው መርሐግብ ለመግባት አመልክታችሁ የመግቢያ ፈተና የወሰዳችሁና አዲስ አበባ
#AASTU የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ፣ በሁለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በቅድመ ምረቃ በመደበኛው መርሐግብ ለመግባት አመልክታችሁ የመግቢያ ፈተና የወሰዳችሁና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ምርጫችሁ ላደረጋችሁ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ፦ ኢንጂነሪንግ ትምህርት ለወንዶች 69.5 እና ከዚያ በላይ ለሴቶች 65 እና ከዚያ በላይ አፕላይድ ሳይንስ ትምህርት ለወንዶች 57 እና ከዚያ በላይ ለሴቶች 50 እና ከዚያ በላይ ይህ የመቁረጫ ነጥብ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቻ ነው። የመቁረጫ ነጥብ ስሌት፥ የ12ኛ ክፍል ውጤት ወደ መቶ ፐርሰንት በመቀየር እና የመግቢያ ፈተና ውጤት ከመቶ ፐርሰንት በመውሰድ የሁለቱ ውጤቶች አማካይ (Average) የተማሪው/ዋ ውጤት እንደሆነ ተገልጿል። የተማሪዎችን የምዝገባ ጊዜን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

No በሉ

Is your documentation is done? If...
Anonymous voting

No በሉ

Is your documentation is done? If...
Anonymous voting

እንኳን ደስ ያላችሁ‼️ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ት
እንኳን ደስ ያላችሁ‼️ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች፥ ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ ያሟሉ ሆኖ የተወሰነ መሆኑን በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን መስከረም 20/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ደብዳቤ ያሳያል።  በመሆኑም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስተሩ ገልፀዋል። 💥 ከ297/600 ያመጣቹህ ተማሪዎች አልፋቹኋል 👏

ከፍተኛ ውጤት 592 ነው!! የዘንድሮ የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ተስተካክሎ 592 ሆኗል። የ 2017 የ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ካሊድ በሽር ውጤት ከ 591 ወደ 59
+1
ከፍተኛ ውጤት 592 ነው!! የዘንድሮ የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ተስተካክሎ 592 ሆኗል። የ 2017 የ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ካሊድ በሽር ውጤት ከ 591 ወደ 592.08 ተስተካክሏል። እንደ ሀገር 2ኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ጎሳ ነጌሶ ውጤት ከ 589 ወደ 590.08 ተስተካክሏል። የነዚህ ተማሪዎቹ ውጤት ማስተካከል የተቻለው ተማሪ ካሊድ በሽር እንዴት 9 ነጥብ ብቻ ያጠል በማለት በድጋሚ ታይቶ ውጤቱ 592.08 መሆኑ ተረጋግጧል። ተማሪ ካሊድ በሺርና ጎሳ ነጌሶ እንኳን ደስ  አላችሁ!

" ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ቤቶችን በደንብ መመልከት እንጀምራለን በተማሪ ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝቶ ያላዳረሰ ት/ቤት ካለ የእውቅና ፈቃዱ ይሰረዛል " - ትምህርት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ በከተማዋ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች በተማሪዎቻቸው ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝተው ማሰራጨት ካልቻሉ የእውቅና ፈቃዳቸው እስከመሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል። የቢሮው ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ " በግል ትምህርት ቤቶች አልፎ አልፎ የሚታየው የመጻሕፍት እጥረት ከህትመት ጋር በተገናኘ ምክንያት እጥረት ኖሮ ሳይሆን ገዝተው ለተማሪዎቻቸው ማሰራጨትን እንደ ወጪ እና እንደ ድካም ስለሚያስቡት ነው " ብለዋል። ሃላፊው ይህን ያሉት በአዲስ ቲቪ በተላለፈ " በጠረጴዛ " በተሰኘ ፕሮግራም ላይ በቀረቡበት ወቅት ነው። " የመማሪያ መጻሕፍት በበቂ ሁኔታ ታትመዋል?በተለይ በግል ት/ት ቤቶች ለተወሰነ ጊዜ መጻሕፍት ሽያጭ ይከናወን እና አልቋል ይባላል ይህ ለምን ሆነ ? " የሚል ጥያቄ ለትምህርት ቢሮ ሃላፊው ቀርቦላቸው ነበር። የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን መለሱ ? " በተለይ አዲሱ ስርአተ ትምህርት ተግባራዊ ከሆነ በኋላ በልዩ ሁኔታ ድጋፍ ተደርጎ ለተማሪዎቻችን አንድ ለአንድ እንዲደርስ ተደርጎ ህትመቱ በበቂ ሁኔታ ተሰራጭቷል። የመጻሕፍት ህትመት እና ስርጭት ላይ ለመንግሥት ተማሪዎች መጻሕፍት በነጻ ይሰጣል ለግል ትምህርት ቤቶች በሪቮልቪንግ ፈንድ 250 ሚሊየን ተፈቅዶልን ይህንን ስራ እየሰራን እንገኛለን። የግል ትምህርት ቤቶች ላይ ያለው ችግር ከተማሪዎች የመጽሐፍ ገንዘብ ሰብስበው ከትምህርት ቢሮ ስቶር ገዝተው ትምህርት ቤታቸው ማድረስ እና ማሰራጨት እንደ ትልቅ እዳ ነው የሚቆጥሩት ። እንደከተማ ግን በቂ ህትመት ታትሞ ስቶራችን ሙሉ ነው ችግሩ ት/ቤቶች መጻሕፍቶቹን ከስቶር ወስደው ለተማሪዎች ማከፋል ላይ ነው ያለው። በተለይ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ፈቃድ የሚሰጠው አካል እሱ ስለሆነ መጻሕፍት በተማሪዎቻቸው ቁጥር ልክ ወስደው ለተማሪዎቻቸው ያላዳረሱ ትምህርት ቤቶች ካሉ እውቅና ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ተግባብተናል። በቂ መጻሕፍት አለን በግል ት/ቤቶች እየተሰራጨ ነው አሁንም በስርጭት ላይ ነው የሚገኘው ችግሩ ያለው ትምህርት ቤቶች ላይ ነው እንደ ወጪ እንደ ድካም ስለሚያስቡት ነው። ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ቤቶችን በደንብ መመልከት እንጀምራለን በተማሪ ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝቶ ያላዳረሰ ት/ቤት ካለ የእውቅና ፈቃዱ ይሰረዛል። አንድም ተማሪ ያለ መጽሐፍ መማር የለበትም ይሄንን አንታገስም ይህም የእርምጃችን አንዱ አካል ይሆናል " ብለዋል። https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለደመራ በዓል አደረሳችሁ 🎉
ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለደመራ በዓል አደረሳችሁ 🎉

‼️"ጊዜዬን በአግባቡ መጠቀም ለውጤት አብቅቶኛል" ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበች ተማሪ የሀገር አቀፍ ፈተናን በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ 577 ውጤት ማስመዝገብ ችላለች ተማሪ አና ብሩክ። በ201
+2
‼️"ጊዜዬን በአግባቡ መጠቀም ለውጤት አብቅቶኛል" ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበች ተማሪ የሀገር አቀፍ ፈተናን በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ 577 ውጤት ማስመዝገብ ችላለች ተማሪ አና ብሩክ። በ2017 የትምህርት ዘመን በደሴ ከተማ የመምህር አካለ ወልድ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዋ አና ብሩክ ለተገኘው ውጤት ዋነኛው ምስጢር ጊዜን በአግባቡ መጠቀም እና በቂ ዝግጅት ማድረግ መኾኑን ነው ከአሚኮ ጋር በነበራት ቆይታ የገለጸችው። “ጊዜዬን በአግባቡ እጠቀም ነበር፤ ውጤታማ የኾንኩትም በዚህ ምክንያት ነው፤ ወደፊትም ብቁ ዜጋ ሆኜ ሀገሬን ማገልገል እፈልጋለሁ” ብላለች። ተማሪ አና ለስኬቷ ወላጆቿ ወይዘሮ ብርቱካን ይኸይስ እና አቶ ብሩክ አደራ ያደረጉላት ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጻለች። ወላጆቿ አጋዥ መጻሕፍትን ከመግዛት ጀምሮ ለጥናት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንድታስመዘግብ ትልቅ ሚና እንደተጫወቱም ነው ያስገነዘበችው። መምህራን አሁን ለተገኘው ውጤት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም ገልጻለች። የተማሪ አና ወላጆችም ልጃቸው በትምህርት ላይ እንድታውል አስፈላጊውን ክትትል እና ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ከትምህርቷ ሊያዘናጋ የሚችል ማንኛውንም ነገር እንዳትጠቀም ይመክሯት እንደነበርም ጠቁመዋል። በተለይም የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀሟ ከትምህርት ጋር የተያያዘ ብቻ መኾኑ ለስኬቷ አስተዋጽኦ አድርጓል ነው ያሉት። የአና ስኬት በቤተሰብ ውስጥ አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳረፉን የገለጹት ወላጆቿ ታናሽ ወንድሟ አዶኒያስ ብሩክም የእህቱን አርዓያ በመከተል በ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 98 ነጥብ 33 አማካይ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። #አሚኮ https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

‼️አዎንታዊ ድጋፍ የሚሹ አመልካቾች መስፈርቶች የመስማት/የማየት ችግር ያለባቸው ተማሪዎች፦ ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ እና የማየት ወይም የመስማት ችግርን የሚገልጽ የህክምና ማስረጃ። የሚያጠቡ እናት አመልካቾች ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ እና ከወለዱበት የጤና ተቋም 6 ወር ያልሞላው የህጻኑ/ኗ የክትባት ካርድ። ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ እና ከወሳኝ ኹነት የተገኘ የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ። የአካል ጉዳት ላለባቸው አመልካቾች ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ እና ከመንግሥት የጤና ተቋማት የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና ማስረጃ። የጤና ዕክል ያለባቸው አመልካቾች ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ እና ከመንግሥት የጤና ተቋማት የቦርድ ውሳኔ የተሰጠበት የህክምና ማስረጃ። 🔔 በ https://student.ethernet.edu.et በኩል እስከ መስከረም 16/2018 ዓ.ም ድረስ ያመልክቱ።

❗️የዩኒቨርሲቲ ምርጫ በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በ
❗️የዩኒቨርሲቲ ምርጫ በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፡- 1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። 2. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።

❗️በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ተበረከተ። በሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ በ2017 የትምህርት ዘመን በ12ኛ ክ
+4
❗️በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ተበረከተ። በሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ በ2017 የትምህርት ዘመን በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች እውቅናና ሽልማት አበርክቷል። (መስከረም 09/2018 ዓ.ም) በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተመዘገበው 22 በመቶ ውጤት አበረታች መሆኑን ጠቁመው ክልሉ ለትምህርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው ብለዋል። እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ የሰራና የለፋ ብቻ ውጤት የሚያገኝበት ሥርዓት እየተዘረጋ መጥቷል ያሉት ሚኒስትሩ ዛሬ የተሸለማችሁ በአቋራጭ ሳይሆን በስራና በድካም ያገኛችሁት ውጤት በመሆኑ ልትኮሩ ይገባችኋል ብለዋል። በቀጣዩ የ2018 የትምህርት ዘመንም የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በክልሉ ሙሉ በመሉ ከወረቀት ነፃ በሆነ መልኩ በኦላይን ለመስጠት ከክልሉ አመራር ጋር መግባባት መደረሱንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል። በመሆኑም በክልሉ አሁን በተገኘው ውጤት መዘናጋት ሳይኖር የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ይሄ ትውልድ የሥራ ትውልድ፣ በራሱ የሚኮራ ትውልድ እንዲሆን እንደ ሀገር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል። በዕውቅናና ሽልማት መርሀ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

ቅሬታዎን ያስገቡ❗️ በ12ኛ ክፍል ውጤትዎ ላይ ያለዎትን ቅሬታ በኦንላይን በቀጥታ ያስገቡ! ➫ https://result.eaes.et ላይ ይግቡ፣ ➫ የአድሚሽን ቁጥርዎን ያስገቡ፣ ➫ የመጀመሪያ ስምዎን
ቅሬታዎን ያስገቡ❗️ በ12ኛ ክፍል ውጤትዎ ላይ ያለዎትን ቅሬታ በኦንላይን በቀጥታ ያስገቡ! ➫ https://result.eaes.et ላይ ይግቡ፣ ➫ የአድሚሽን ቁጥርዎን ያስገቡ፣ ➫ የመጀመሪያ ስምዎን ያስገቡ፣ ➫ ውጤትዎን ይመልከቱ፣ ➫ እዛው ገፅ ላይ ወደታች ስክሮል ያድርጉ፣ ➫ 'Submit Complaint' የሚለውን ይጫኑ፣ ➫ 'My Complaints' የሚለውን ይጫኑ፣ ➫ ቅሬታዎን ከማስገባትዎ በፊት ከዚህ በፊት ቅሬታ አስገብተው ከነበረና ምላሽ ከተሰጠዎ ይመልከቱ፣ ➫ የተሰጠዎን ምላሽ ይመልከቱ።

‼️ከህመም ጋር እየታገለ ፈተናውን የወሰደው ተማሪ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥቷል የበደሌ ኢፈ ቦሩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አሉዲን ሁሴን፤ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና መው
+1
‼️ከህመም ጋር እየታገለ ፈተናውን የወሰደው ተማሪ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥቷል የበደሌ ኢፈ ቦሩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አሉዲን ሁሴን፤ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና መውሰድ እንደጀመረ የትርፍ አንጀት ህመም ያጋጥመዋል፡፡ ይሁን እንጂ፣ ህመሙ ፈተናውን መጨረስ የሚያስችልበት ደረጃ ላይ በመሆኑ፥ ትምህርት ቤቱ ከሐኪሞቹ ጋር በመነጋገር መድኃኒት እየወሰደ ፈተናውን እንዲወስድ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ህክምና እየተደረገለት ለሶስት ቀናት የማኅበራዊ ሳይንስ ፈተናውን ወስዶ ያጠናቀቀው ተማሪ አሉዲን፤ 472 ማምጣቱን ጅማ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል፡፡

❗️መንትዮች ከፍተኛ ውጤት አስመዘገቡ ያብጸጋ አስቻለው እና ያብተስፋ አስቻለው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን የሚገኘው ሶዶ ቡኢ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው። መን
+1
❗️መንትዮች ከፍተኛ ውጤት አስመዘገቡ ያብጸጋ አስቻለው እና ያብተስፋ አስቻለው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን የሚገኘው ሶዶ ቡኢ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው። መንትዮቹ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ሳይነጣጠሉ በተመሳሳይ ክፍል ነው የተማሩት፡፡ የደረጃ ተማሪዎች የነበሩት መንትዮቹ፤ በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት አምጥተዋል። ያብጸጋ 548 እና ያብተስፋ 543 ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ መንትዮቹ ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሠራር መሰረት በአንድ ዩኒቨርሲቲ በአንድ ዶርም ውስጥ ተመድበው ትምህርታቸውን ለመከታተል ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ #FMC https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

‼️የፊዚክስ ውጤት ተስተካክሏል የ 2ኛ ዙር ተፈታኞች የሆናችሁ እና የፊዚክስ ውጤት ወደ 100 ያልተቀየረላችሁ አሁን ተስተካክሏል። እንደገና እየገባችሁ የተስተካከለውን ማየት ትችላላችሁ። Website
‼️የፊዚክስ ውጤት ተስተካክሏል የ 2ኛ ዙር ተፈታኞች የሆናችሁ እና የፊዚክስ ውጤት ወደ 100 ያልተቀየረላችሁ አሁን ተስተካክሏል። እንደገና እየገባችሁ የተስተካከለውን ማየት ትችላላችሁ። Website፡ https://result.eaes.et Telegram፡ https://t.me/EAESbot

‼️ከፍተኛ ውጤት ተማሪ ገነት መርጋ👏 ተማሪ ገነት መርጋ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። የዶዶላ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ስትሆን በተፈጥሮ ሳይንስ
+1
‼️ከፍተኛ ውጤት ተማሪ ገነት መርጋ👏 ተማሪ ገነት መርጋ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። የዶዶላ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ስትሆን በተፈጥሮ ሳይንስ #579/600 አምጥታለች። የሒሳብ እና ፊዚክስ ውጤቶቿም 100/100 ናቸው። https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk