ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 071
Подписчики
+224 часа
+37 дней
+230 день
Архив постов
photo content
+1

“ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ሃሳብ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና ሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ ተካሄደ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ መድረኩ በተለያዩ ሀገራዊ እና አስተዳደራዊ የመንግስት ነባራዊ  ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በፓርቲው ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችና የተቀመጡ አቅጣጫዎች ሰነድ ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን የመንግስት ሠራተኛውን አቅም በማጎልበት ኢትዮጵያ ብሎም አስተዳደሩ ለጀመሩት የእድገትና ለውጥ ጉዞ ወሳኝ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችላቸው ግንዛቤ እንዲይዙ የሚያስችል ይሆናል ብለዋል።  በአጠቃላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረኩ ሠራተኛው ራስን ከመምራት ጀምሮ ህዝብን በሚገባ ማገልገል እንዲችልና በሠራተኛው ዘንድ የተግባርና የሀሳብ አንድነት የማምጣት ባህልን ቀጣይነቱ የተረጋገጠ ጥራት ያለውና ፍትሀዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችልና የሚያስረዳ ግንዛቤ መፍጠር ዋና አላማው መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ማጠናቀቂያ የቢሮውና የኮሌጆች አስተዳደር ሠራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን በግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቱ የቀረበው ሰነድ ላይ ግልጽነት የሚያስፈልጋቸውን ነጥቦች በማንሳትና በመጠየቅ ከመድረክ ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊቴክኔኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገነቡት የኮንስትራክሽን ስራዎች ላይ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩን በመልዕክት ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ኤች አይ ቪ ኤድስ ሴክሬተሪያት ባለሞያና የፅ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት አቶ አብዱላኪም አህመድ ሲሆኑ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ስራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙ እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አክለውም ይህ ሀይል ወጣቶችንና ሴቶችን በከፍተኛ ቁጥር ያካተተ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይህ የዛሬው መድረክ እንደተዘጋጀ ገልፀው መድረኩን አስጀምረዋል። በመቀጠል የዕለቱን ስልጠና የሰጡት አቶ ፈቲ መሀመድ የስልጠናውን ሰነድ ካቀረቡ በኋላ መድረኩን ለውይይት ክፍት አድርገዋል። ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን ምላሾችም ተሰጥተዋል። በመጨረሻም የሥራና ክህሎት ቢሮ የሴቶች ወጣቶችና ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ማርታ በዛብህ  ይህ አይነቱ መድረክ በተከታታይነት እንደሚፈጠርና ተጨማሪ ስራዎችም ቢሮው እንደሚሰራ ገልፀው መድረኩ ተጠናቋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 6/6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኔክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገነቡት የኮንስትራክሽን ስራዎች ላይ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩን በመልዕክት ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ኤች አይ ቪ ኤድስ ሴክሬተሪያት ባለሞያና የፅ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት አቶ አብዱላኪም አህመድ ሲሆኑ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ስራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙ እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አክለውም ይህ ሀይል ወጣቶችንና ሴቶችን በከፍተኛ ቁጥር ያካተተ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይህ የዛሬው መድረክ እንደተዘጋጀ ገልፀው መድረኩን አስጀምረዋል። በመቀጠል የዕለቱን ስልጠና የሰጡት አቶ ፈቲ መሀመድ የስልጠናውን ሰነድ ካቀረቡ በኋላ መድረኩን ለውይይት ክፍት አድርገዋል። ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን ምላሾችም ተሰጥተዋል። በመጨረሻም የሥራና ክህሎት ቢሮ የሴቶች ወጣቶችና ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ማርታ በዛብህ  ይህ አይነቱ መድረክ በተከታታይነት እንደሚፈጠርና ተጨማሪ ስራዎችም ቢሮው እንደሚሰራ ገልፀው መድረኩ ተጠናቋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 6/6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ከቃል እስከ ባህል በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ለሥራና ክህሎት ብልጽግና ህብረት አባላት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ ተካሄደ። በመድረኩ ለአባላቱ በፓርቲው ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎች እና የተቀመጡ አቅጣጫዎችን የያዘ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን የቢሮው ም/ኃላፊና የህብረቱን ፖለቲካ ዘርፍ የሚመሩት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ አባሉ በሚሰራበት ዘርፍ አውድ በተለይም በክህሎት ልማቱ፣ በስራ ዕድል ፈጠራው አንዲሁም በአሰሪና ሰራተኛው ዘርፎች  የውጤታማነት ባህልን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። 👇ከቀረበው ሰነድ የተመላከቱ ነጥቦች👇 ✍️ የኢኮኖሚ ልማትን ማፋጠን፤ ✍️ ማህበራዊ ብልጽግናን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ውጤታማነት ማስቀጠል፤ ✍️ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራ መስራት፤ ✍️ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ውጤታማነትን ማረጋገጥ፤ ✍️ ጠንካራ የሚዲያ እና የኮሙዩኒኬሽን ስራ መስራት፤ ✍️ የጠንካራ ፓርቲ ግንባታን አጠናክሮ መቀጠል፤ ✍️ የብሔራዊነት ገዢ ትርክት ግንባታ ማጠናከር፤ ✍️ ውጤታማ የሰላም ግንባታ መስራት፤ ✍️የፍትህ ዘርፍ ውጤታማነትን ማሳደግ፤ ✍️ የሀገር ግንባታ ማጠናከር፤ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

#ከቃልእስከባህል 2ኛውን የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ መጠናቀቅ ተከትሎ፥ ለድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት አባላት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

photo content
+3

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ። በመድረኩም ከተለያዩ ተቋማት ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል። በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የስራ አካባቢያቸውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነት እና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳደግ እንዲሁም የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

#ዜና| በኮሌጅ ውስጥ የሚገኙ ሴት ሰራተኞችን ቀጣይነት ባለው ስልጠና አቅማቸውን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት በስርዓተ-ፆታ ላይ የተመሰረተ ጥ
+7
#ዜና| በኮሌጅ ውስጥ የሚገኙ ሴት ሰራተኞችን ቀጣይነት ባለው ስልጠና አቅማቸውን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት በስርዓተ-ፆታ ላይ የተመሰረተ ጥቃትን እንዲሁም የህይወት ክህሎት እና ስራ ፈጠራ በተመለከተ የአቅም ግንባታ ስልጠና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከኮሌጁ እና ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተጋበዙ አሰልጣኞች ለሴቶች የአስተዳደር ሰራተኞች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡ በስልጠናው ላይ በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ እንደ ገለጹት እንደሚታወቀው ሃገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላለችብት እድገት እንዲሁም ቀጣይ ለምትደርስበት የእድገት ደረጃ ለመድረስ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነዉ። ስለዚህ ሴቶችን በህይወት ክህሎት እንዲሁም በስራ ፈጠራ ላይ ማብቃት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ምክትል ዲኗ አያይዘውም በስርአተ-ፆታ ላይ የተመሰረቱ ጥቃቶችን አብዛኛው ጊዜ ሴቶች እንዲሁም ህጻናት ላይ የሚደርስ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም አካላት ሊቃወሙትና ሊታገሉት እንደሚገባ በስልጠናው ላይ ለተሳተፉ አካላት አስገንዝበዋል፡፡ በስልጠናው ላይ በኮሌጁ የሚገኙ ሴት አመራሮች፣ሴት ኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እንዲሁም ሁሉም ሴት ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው ለ5 ቀን የሚቆይ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና | የፀሀይ ታዳሸ ሀይልን ለወጣቶች የስራ አድል ፈጠራ ያለው አበርክቶት ከፍተኛ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተባለ። ADRA ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጅት 5.2 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የፀሀይ ሀይል ኤሌትሪክ መሳሪያ ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለገሠ። በ2001 ወደ ስራ የገባው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከደረጃ 1-5 በማንፋክቸሪንግ ኤሌክትሪክ አውቶ እና ሰርቬይንግን ጨምሮ በ9 የትምህርትና የስልጠና ዲፓርትመንቶች እያሰለጠነ ይገኛል። ኮሌጁ ADRA ኢትዮጵያ ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጀት ጋር በመተባበርና በፀሀይ የኤሌትሪከ ሀይል ማምረቻ ተከላ እና ጥገና ዙሪያ ወጣቶችን እያሰለጠነ ይገኛል። ለሁነቱ የተግባር መማሪያ የሚያስፈልግ 5.2 ኪሎ ዋት የሚያመነጨ የፀሀይ ሀይል ማመንጫ መሳርያ ለኮሌጁ ለግሶል። በኩነቱ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ስራ ከህሎት አና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል አና የቴክኒክ ሞያ ኤጀንሲ ሀላፊ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ ስራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥርት ወጣቶችን ስልጠናውን እንዲወስዱ እየተደረገ ይገኛሉ ብለዋል።በተለይም የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ከማድረግ ጎን ለጎን ወጣቶችን በማደራጀት የስራ እድል ተጠቃሚ አንዲሆኑ ያደርጋል ሲሉ ገልፀዋል። የADRA ኢትዮጵያ የፕሮጀከት ዳይሬክተር ዶክተር ዘሪሁን ሀዋኖ በበኩላቸው ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ባለፉት 2 አመታት 90 ወጣቶችን በዘርፉ ማሰልጠናቸውን ገልፀው እርዳታው ሰልጣኞች በዘረፉ በቂ እውቀት እንዲጨብጡ እንዲሁም የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ ያደረጋል ብለዋል። #DireTv አማርኛ የካቲት 4/2017

ለህጋዊና  ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን ምን ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ✅ ካሉበት ሆነው የእጅ ስልዎን በመጠቀም በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (www. lmis.gov.et ) ላይ አስፈላጊውን ምዝገባ ያከናውኑ፣ ✅ የባለሙያ ድጋፍ ከፈለጉ አቅራቢያዎ በሚገኝ አንድ ማዕከል በመሄድ ምዝገባውን ማካሄድ ይችላሉ፣ ✅በግለሰቡ እንዲሞሉ የቀረቡ መረጃዎችን ሞልተው ሲያጠናቅቁ  8 ዲጅት ያለው ቁጥር መልዕክት በስልክዎ ይደርስዎታል፡፡ ✅ ቀጥሎ  የተላከልዎትን የባዮሜትሪክ ቁጥር ይዘው በአቅራቢያዎ ወደ ሚገኝ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመሄድ አሻራ መስጠት ይኖርብዎታል፣ ✅መረጃዎቹን ሰጥተው ሲያጠናቅቁ በስልክዎት አስር ዲጂት ያለው የሰራተኛ መለያ መታወቂያ ቁጥር የያዘ መልዕክት ይደርስዎታል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ምዝገባው ተጠናቀቀ ማለት ነው። ቀጣይ ሂደቶቹን ለማወቅና ተከታታይ ወቅታዊ መረጃ እንዲደርስዎ ገፃችንን ይከታተሉ። 📢ልብ ይበሉ ✅ ለእነዚህ አገልግሎቶች ምንም አይነት ክፍያ አይጠየቁም! ✅ተጨማሪ መረጃዎችን በአቅራቢያዎ ከሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ማግኘት ይችላሉ! #LegalOverseasEmployment #OverseasOpportunities  #ህጋዊአማራጭ  #ደህንነቱየተጠበቀሥራስምሪት  ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ የካቲት 4፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols

#Oduu gammachiisaa!!! Warra barnota fi leenjii digrii barbaaddan hundaaf! Inistiitiyuutii Leenjii Teeknikaa fi Ogummaa Federaalaa Rippabiliika Dimookiraatawaa Itiyoophiyaa, Mooraa Saatalaayitii Kolleejjii Pooliteeknikii Dire dawaa bara barnootaa 2017tti dabalataan leenjii idilee digrii tokkoffaa sagantaa galgalaa (extension) fi sagantaa dhuma torbee (weekend) Leenjiiwwan Idilee: 1. Automotive Teeknooloojii 2. Construction Teeknooloojii 3. Electrical Electronics Teeknooloojii 4. Garment Teeknooloojii 5. Manufacturing Teeknooloojiidhaan. Qophii leenjii fi galmee iyyattoota ulaagaa galmee guutan xumuruu isaa, gammachuu guddaadhaan isin beeksifna