ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 064
Подписчики
-124 часа
-47 дней
+530 день
Архив постов
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰሩ ስራዎችን ጉብኝት ቀጥሎ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ። ቡድኑ በዛሬው ዕለት በጠዋቱ መርሃግብር በዋናነት በአሰሪና ሰራተኛው ዘርፍ  በኢንዱስትሪዎች እና በኤጀንሲዎች ያለውን አጠቃላይ የስራ ሁኔታ የጎበኘ ሲሆን በተለይም በፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ እና የመንግስት የልማት ድርጅት በሆነው ኤሌክትሪክ አገልግሎት  የሰራተኛ ማህበራት ከድርጅቶቹ ጋር ያላቸው ግንኙነት እና የሙያ ደህንነትና ጤንነት ስርዓት ያለበትን ደረጃ ምልከታ አድርጓል። ከኢንተርፕራይዝ ልማት አኳያ በድሬዳዋ የመጀመሪያ የሆነው በዲጂታል ማርኬቲንግ እና የበቃ የሰው ሃይል ለኢንዱስትሪዎች አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ የተተገበሩና የስራ ዕድል ፈጠራ ተግባራት ያስገኛቸው ውጤቶችና ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎችን ተመልክቷል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ ሁለተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩ ኢንዱስት
+8
በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ ሁለተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ከሚያዘጋጃቸው ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች አካል መሆኑ ታውቋል፡፡ ቢሮው የቀን ሰራተኛ ዜጋውን ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ አምራች ሃይል ባለሙያ በማዘጋጀት የሚሰሩበት ኢንዱስትሪ ድረስ በመሄድ ግንዛቤ እንዲፈጠር ማድረግ ችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ ባለመውና በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራው ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ድጋፋዊ ጉብኝት ማካሄድ ጀመረ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የመግቢያ ውይይቱ ላይ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት በአስተዳደሩ በሥራ እና ክህሎት ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የክህሎት ልማት፣  የአሰሪና ሰራተኛ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን  ተመልክቶ ድጋፍ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ የስራ ጉብኝት መሆኑ ለቀጣይ የስራ ዕንቅስቃሴ መነቃቃት የሚፈጥር ነው ብለዋል። የመስክ ምልከታው ዓላማ በዋናነት መልካም አፈፃፀሞችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የኢንዱስትሪ ሰላማዊ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት መሆኑን የልዑኩ ቡድን መሪ አቶ ጥኡመዝጊ በርሔ አስታውቀዋል፡፡ በዚህም የልዑክ ቡድኑ በዛሬው ዕለት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ልህቀት ማዕከል፣ በአስተዳደሩ የሚገኙ የግልና የመንግስት ኮሌጆች፣ የወረዳ አንድ ማዕከላት እና ከፍተኛ የማደግ አቅም ያላቸው ኢንተርፕራይዞችን ተዟዙሮ የተመለከተ ሲሆን በተጨማሪ በአስተዳደሩ የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች፣ ኢንተርፕራይዞች ያሉበትን ሁኔታ እና የኢንዱስትሪ ሰላም ጋር ተያይዞ የተከናወኑ ሥራዎችን ጉብኝት በቀጣይ ቀን ያካሂዳል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+1

የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ፡፡ የኮሌጁን መደበኛ የ2018 በጀት ዓመት የ6ወር የንብረት፣የወጪ አስተዳደር እንዲሁም የካይዘን ትግበራ ሂደት ለመገምገም በኮሌጁ ለተገኘው የምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት አጠቃላይ በኮሌጁ ውስጥ የተሰሩትን ስራዎች በተለይም ከዲጂታላይዜሽን፣ኮሌጁን ለስራ ምቹ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር የተሰሩ ስራዎችን በበቂ ሁኔታ የተብራራ ሲሆን በተለይ ኮሌጁ ከካይዘን ትግበራ አንጻር ያለውን ልምድና የትግበራ ሁኔታ ለኮሚቴው አባላት የተገለጸ ሲሆን እቅዱ ተፈጻሚ እንዲሆንና ስራዎች ዘላቂ እንዲሆኑ ሁሉም የኮሌጁ ሰራተኞች ከኮሌጁ ማኔጅመንት ጋር በከፍተኛ ትጋትና የሁሉም ተሳትፎ በጋራ በማካተት እየሰራ እንዳለ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም ኮሌጁ በአስተዳደሩ የተጣለበትን ትልቅ ሀላፊነት ለመወጣት ወጪዎችን በመቀነስና በራስ አቅም በመስራትና ምርቶችን በማምረት ሌሎች ተቋማትም ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰራ እንዳለ ለኮሚቴው አብራርቷል፡፡ የመስክ ምልከታውና ግምገማውን ለማድረግ የተገኘውን ኮሚቴ የመሩት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ አንድነት ሀይሉ እንዳሉት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚሰራቸው ስራዎች በሙሉ በአስተዳደሩ እንደ ሞዴል የሚወሰድ ተቋም ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ኮሌጁ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ የሚሰራቸው ስራዎች ለራሱ አልፎ ለሌሎችም እንደ ተሞክሮ ሊወሰድ ይገባዋል ብለዋል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ አክለውም ስራዎችን ለማዘመን እየተሰራ ያለው የዲጂታላይዜሸን ስራዎች፣ትምህርትና ስልጠናው የተቀላጠፈ እንዲሆን እየሰራ ያለው ስራ እንዲሁም የስራ ቦታው ለሰራተኛውና ለሰልጣኞች ምቹ እንዲሆን ከካይዘን አተገባበር አንጻር እየሰራ ያለው ስራ እጅግ አርኪ በመሆናቸው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ይህንንም የስራ አፈጻጸም ሌሎች ተቋማት እንደ ልምድ ሊወስዱት ይገባል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ቋሚ ኮሚቴው በኮሌጁ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የመስክ ምልከታውንና ሪፖርቱን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከአራቱ የድጋፍ ማዕቀፍ አንዱ የሆነውን የኢንተርፕሩነርሽፕ ስልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ። በተያዘው የበጀት አመት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ ለአሰልጣኝ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ሲሆን ይህን መሰረት በማድረግ የመንግስት ፖሊ ቴክኒክና የግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኖች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ አዲስ በተዘጋጁ እና ከተከለሱ የስልጠና ሰነዶች አንዱ የሆነውን  Entrepreneurship (Discover yourself and develop an entrepreneurial mind set and design and lunch your vencher) ላይ ስልጠና ወስደዋል፡፡ ስልጠናው ከEDI በመጡ አሰልጣኝ የተሰጠ ሲሆን በመርሃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ውልታ ትልቅሰው ለመንግስት ፖሊ ቴክኒክና ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኖች የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና መሰጠቱ ስራዎችን በተለይም የሚሰጡ ድጋፎችን በዕውቀትና በክህሎት ለመስራት  የሚያስችል እንደሆነ ገልጸዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

በየጊዜው የሚዘረጉ ዲጂታል የአሰራር ሲስተሞችን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥን ማቀላጠፍ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አጠቃላይ አሰራር በዲጂታል ሲስትም ለመቀየር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል:: ኮሌጁ የአገልግሎት አሰጣጡን ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን አሰራር በDigital System ለመተካት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለአመራር አባላትና ለክፍል ተጠሪዎች የግንዛቤ መድረክ አካሂዷል:: አሁን ባለንበት ዘመን ቴክኖሎጂን መጠቀም ምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም እንደ ተቋም ቀጣይነትን ለማረጋገጥ በዲጂታል ሲስተም ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግና ምንሰጣቸውን አገልግሎቶች ማዘመን ይጠበቅብናልም ብለዋል:: የግንዛቤ ስልጠናው ከኢትዮ ቴሌኮም በመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም አሁን ያለው አሰራር በዲጂታል ሲስተም ሲቀየር በምን መልኩ ይሰራል የሚለውና የስራ ክፍሎች ሲስተሙን የሚያንቀሳቅሱበትን ሂደት በዝርዝር ግንዛቤ መስጠት ችለዋል:: በመድረኩ በተሰጠውን ግንዛቤ ላይ ከተሳታፊዎች በሲስተሙ አተገባር ዙሪያ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ማብራሪያም ተሰጥቶባቸዋል:: በእለቱ ግንዛቤውን የሰጡት የኢትዮ ቴሌኮም ባለሙያዎች በቀጣይ ቀናትም ሲስተሙ የሚተገበርባቸው በሁሉም ስራ ክፍሎች ላይ በመገኘት የሲስተሙን አጠቃላይ አተገባበርና አጠቃቀምን በተመለከተ የተግባር ስልጠና እንደሚሰጡም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን መደበኛ ፣ በኮሌጁ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ
+9
የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን መደበኛ ፣ በኮሌጁ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ፡፡ የኮሌጁን መደበኛ ፣በኮሌጁ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የ2018 በጀት ዓመት የ6ወር የእቅድ አፈጻጸም ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ እስከ ግማሽ በጀት አመቱ ማጠቃለያ ድረስ በከፍተኛ ትጋትና የሁሉም ተሳትፎ በጋራ በማካተት እየሰራ እንዳለ የተገለጸ ሲሆን ፡፡ በተጨማሪም ኮሌጁ በ ቴክኒክና ሙያ አዲሱ እሳቤ አንጻር ከእቅዱ ጋር በማስተሳሰር እየሠራ እንደሚገኝ ለቋሚ ኮሚቴው ገለጻ ተደርጓል።የከተማው አስተዳደር ለኮሌጁ የሰጠውን ሃላፊነት ኮሌጁ ተቀብሎ ከእቅዱ ጋር በማስተሳሰር ያለምንም እንከን እየሰራንም እንዳለ የተብራራ ሲሆን። የቋሚ ኮሚቴው አባላት እንዳሉት ኮሌጁ በመደበኛ እንዲሁም በኮሌጁ ባሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከእቅዱ አንጻር አመርቂ ውጤት የታየበት ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ተቋሙን ሞዴል እንዲሆን የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት የተገኙ ልምዶችና ውጤቶች ለሌሎች ተቋማት የማካፈል ስራዎች ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡በተለይ የገጠሩን ማህበረሰብ ለመጥቀም እየተሰራ ያለው ቴኖሎጂዎችን የማፍራትና የማሸጋገሩ ስራ እንዲሁም ትምህርትና ስልጠናዎችን ፕሮጀክት ተኮር እንዲሆኑ በተጨማሪም የኮሪደር ልማቱ ላይ ያለው አመርቂ ውጤት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የመስክ ምልከታውንና ሪፖርቱን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በክቡር ዳንኤል ተሬሳ የተመራው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በጅግጅጋ የመግቢያ ውይይት ማድረግ ጀመረ፡፡ መድረኩ በቀጣይ በዘርፉ ታቅደው እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት የሚገኙበትን
+8
በክቡር ዳንኤል ተሬሳ የተመራው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በጅግጅጋ የመግቢያ ውይይት ማድረግ ጀመረ፡፡ መድረኩ በቀጣይ በዘርፉ ታቅደው እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት የሚገኙበትን ሁኔታ በአካል በማየት ጠንካራ ሥራዎች በመለየት ወደሁሉም እንዲሰፉ የማድረግ እና ክፍተቶች ካሉ ደግሞ የማገዝ ሥራ ለመስራት መግባባት የሚፈጠርበት ይሆናል፡፡ ድጋፍና ክትትሉ ዛሬ በይፋ ሲጀመር  በጅግጅጋ ከተማ የሶማሌ ክልልን ጨምሮ የሀረሪ ክልል እና የድሬዳዋ አስተዳደር የዘርፉ አመራሮች በተገኙበት የአፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ የመግቢያ ውይይት በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡

ኢንዱስትሪዎች ጥራቱን የጠበቀ ምርት እንዲያመርቱ የስራ ቦታቸው ምቹ ሊሆኑ ይገባል ተባለ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሲሰጥ የነበረውን የአራቱን ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የድ
+3
ኢንዱስትሪዎች ጥራቱን የጠበቀ ምርት እንዲያመርቱ የስራ ቦታቸው ምቹ ሊሆኑ ይገባል ተባለ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሲሰጥ የነበረውን የአራቱን ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የድጋፍ ማእቀፎች ስልጠናና ትግበራ ስራ በማስቀጠል ኡሚ ዱቄት ፋብሪካ ለሚገኙ ሰራተኞች በካይዘን አተገባበር ላይና የካይዘን ክህሎት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና ሰጠ፡፡ ኮሌጁ በተያዘው በጀት አመት ሊሰራቸው ካቀዳቸው ስራዎች መካከል አንዱና ዋንኛው ኢንዱስትሪዎች የተሸለ ምርት እንዲያመርቱ የሚያስችላቸውን አቅም የመገንባትና የካይዘን ፍልስፍና አተገባበር ላይ በቂ ግንዛቤ በመፍጠር ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ያለምንም ብክነት ለገበያ እንዲያቀርቡ ማስቻል ነው፡፡ በዛሬው እለት የተጀመረው የካይዘን ትግበራ የመጀመሪያ ምእራፍ ስራ ከዚህ ቀደም በተለያዩ አነስተኛ፣መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ላይ ተከታታይነት ያለው የካይዘንና ሂሰብ መዝገብ አያያዝ ስልጠናዎች የተሰሩ ሲሆን በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎቹ ያለባቸውን ክፍተት ለመሙላት ተከታታይነት ያለው የዳሰሳ ጥናት የተደረገ ሲሆን በተገኘው ግብአት መሰረት ኮሌጁ በተረከባቸው ኢንዱስትሪዎች ላይ አራቱን የድጋፍ ማእቀፎች የሚተገብር ይሆናል፡፡በዚህም ስራ ላይ የኮሌጁ መምህራን ከኢንዱስትሪው ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን የሚተገበር ሲሆን በቀጣይም በኢንዱስትሪው ውስጥ የሚኖሩ የቴክኖሎጂ ችግሮችን፣የስፔርፓር ችግሮችን እንዲሁም የክህሎት ችግሮችን ተከታታይነት ያለው ስራዎችን በመስራት የሚፈታ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 1/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በኢንተርፕራይዝ ልማት ስራዎች የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈጻጸም ✍️   በግማሽ ዓመቱ ውስጥ አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን እንዲደራጁ በማድረግ ሂደት በሦስቱም ዘርፎች ማለትም በግብርና 1113 አባላት ያላቸው 118 ኢንተርፕራይዞች፣ በኢንድስትሪ 791 አባላት ያላቸው 107 ኢንተርፕራየዞች እንዲሁም በአገልግሎት ዘርፍ 2069 አባላት ያሏቸው 190 ኢንተርፕራይዞችን በአጠቃላይ በሦስቱም ዘርፎች 3973 አባላትን ያቀፉ 415 ኢንተርፕራይዞችን ማደራጀት ተችሏል፡፡ ይህም በዕቅድ ከተያዘው 750 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን ከማደራጀት አንፃር የ55.3 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ✍️   ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጡ መንግስታዊ ድጋፎችን በማጠናከር ከአንዱ የእድገት ደረጃ ወደ ቀጣይ የእድገት ደረጃ እንዲሸጋገሩ የማድረግ ስራም ሲከናወን የቆየ ሲሆን በዚህም መሰረት 312 ኢንተርፕራይዞች ሽግግር እንዲያደርጉ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም በዕቅድ ተይዞ ከነበረው የ320 ኢንተርፕራይዞች የደረጃ እድገት ሽግግር አንፃር የ97.5 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም 77 ኢንተርፕራይዞች ቅድመ ሞዴል ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም በግማሽ ዓመቱ 87 ኢንተርፕራይዞችን ቅድመ ሞዴል ለማድረግ ከተያዘው ዕቀድ አንፃር የ88.5 በመቶ የተመዘገበበት ነው፡፡ ✍️   377 ኢንተርፕራይዞች የ72,807,737 ብር የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም የገበያ ትስስር ተጠቃሚ ለማድረግ ከታቀደው 218 የኢንተርፕራይዞች መጠን እንዲሁም ከትስስሩ የገንዘብ መጠን አንፃር በሁለቱም ከ100 ፐርሰንት በላይ አፈፃፀም የተመዘገበበት ነው፡፡ ✍️   ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅማቸውን እንዲያጠናክሩ በማድረግ ሂደት 180 ሚሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ለማድረግ ታቅዶ 324.61 ሚሊዮን ብር ማስቆጠብ ተችሏል ይሕም ከ100 ፐርሰንት በላይ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሆኗል፡፡ ✍️   ኢንተርፕራይዞችን የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንፃር 2750 አባላት ያሏቸውን 2000 ኢንተርፕራይዞች የ205 ሚሊዮን ብር ብድር ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ 2749 አባላት ላሏቸው 1943 ኢንተርፕራይዞች የ310,532,293 ብር ብድር ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም ለማሰራጨት ከታቀደው የብድር ገንዘብ መጠን አንፃር ከ100 ፐርሰንት በላይ፣ ከብድር ተጠቃሚ አንቀሳቃሾች አንፃር የ100 ፐርሰንት እንዲሁም የብድር ተጠቃሚ ለማድረግ ከታቀደው የኢንተርፕራይዞች ቁጥር አንፃር ደግሞ የ97 በመቶ አፈፃፀም ሊመዘገብ ችሏል፡፡ ✍️   ለኢንተርፕራይዞች ከተሰራጨ ብድር ውስጥ ከዘመኑ እና ከውዝፍ ብድሮች ከ150.5 ሚሊዮን ብር በላይ ለማስመለስ ታቅዶ ከውዝፍ ብድር 4,968,929 ብር እንዲሁም ከዘመኑ ብድር 175,292,009 በድምሩ 180,260,938 ብር ተመላሽ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል፡፡ ይምህ ከዕቅድ አንፃር ከ100 ፐርሰንት አፈፃፀም የተመዘገበበት ነው፡፡  ✍️   ለኢንተርፕራይዞች ከሚሰጥ የኦዲትና የሂሳብ አያያዝ ዝርጋታ አገልግሎቶች አንፃር ለ532 ኢንተርፕራይዞች የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ስርዓት የመዘርጋት እና ለ446 ኢንተርፕራይዞች ደግሞ የኦዲት አገልግሎቶችን የመስጠት ስራ ተከናውኗል፡፡ በአጠቃላይ ከሂሳብ መዝገብ አያያዝ ስርዓት ዝርጋታ አንፃር በዕቅድ ተይዞ ከነበረው 475 አንፃር ከ100 ፐርሰንት በላይ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሲሆን  የኦዲት አገልግሎትን ለኢንተርፕራይዞች ከመስጠት አንፃር በዕቅድ ከተያዘው የ500 ኢንተርፕራይዞች መጠን የ89.2 በመቶ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ለማድረግ ተችሏል፡፡

photo content

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ምን አከናወነ? ✍️   54 ኢንተርፕራይዞች በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ አስተዳደር ስርዓት (ELMIS) ፕላትፎርም ላይ ተመዝግበዋል፣ ✍️   ስራ ፈላጊ ዜጎችን በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት መተግበሪያ (Ethiopia Labor Market Information System) ላይ ከመመዝገብ አኳያ ወንድ 3218 ሴት 4208 በድምሩ 7436 ለመመዝገብ ተችሏል፡፡ ይህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ለመመዝገብ ከታቀደው 11,227 የስራ አጥ ምዝገባ መጠን አንፃር የ66.14 በመቶ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሆኗል፡፡ ✍️   በጠቅላላው ስድስት ወራት ውስጥ በከተማ በነበረ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሦስቱም ዘርፎች ማለትም በግብርና ለ172 ዜጎች (2.3%)፤ በኢንድስትሪ ለ3183 ዜጎች (42%) እንዲሁም በአገልግሎት ለ4223 ዜጎች (55.7%) በድምሩ 7,578 ዜጎች (ወንድ 4380፤ ሴት 3198) የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ይህም ሦስቱም ዘርፎች በዕቅድ ተይዞ ከነበረው 8241 የስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር የ92 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️   በጠቅላላው በስድስት ወራት ውስጥ በገጠር በነበረ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሦስቱም ዘርፎች ማለትም በግብርና ለ1010 ዜጎች (59.23%)፤ በኢንድስትሪ ለ155 ዜጎች (9.1%) እንዲሁም በአገልግሎት ለ540 ዜጎች (31.7%) በድምሩ 1705 ዜጎች (ወንድ 915፤ ሴት 790) የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ይህም በሦስቱም ዘርፎች በዕቅድ ተይዞ ከነበረው 2707 የስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር የ63 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️   ከ9283 የሥራ ዕድል ውስጥ የሴቶች ድርሻ 3988 ሲሆን ይህም የ43 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ከዕቅድ አንፃር ደግሞ የ73 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ✍️   ከ9283 የሥራ ዕድል ውስጥ አጠቃላይ የወጣቶች መጠን 6366 ሲሆን ይሕም ከጠቅላላው የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች ውስጥ የ68.6 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ከዕቅድ አንፃር የ72.7 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ✍️   ለ41 አካል ጉዳተኛ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው ተደርጓል፡፡ ይህም በዕቅድ ከተያዘው የ77 አካል ጉዳተኞች የስራ ዕድል ተጠቃሚነት አንፃር የ53 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️ ከ973 ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ካደረጉት ውስጥ ወንድ 245 ሴት 631 በድምሩ 876 ተጨማሪ የኮምፒውተር ክህሎት ስልጠና የወሰዱ ናቸው፡፡ ✍️ በብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ከ973 ሰልጣኞች ውስጥ ከ27 ሰልጣኞች ማቋረጥ በስተቀር ቀሪዎቹ 946 ወጣቶች የስራ ትስስር ተፈጥሮላቸዋል፡፡ ✍️ ቢሮው ከቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት(LLRP) ጋር በመተባበር ለ15 በአስተዳደሩ ገጠር ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ወንድ 46 ሴት 146 በድምሩ ለ192 ዜጎች ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ 500,000 ሺህ ብር በድምሩ 7.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጎ ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል። ✍️ ቢሮው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር የሚሰራ ግራንድ ግሩፕ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመቀናጀት በኢ-መኒ ዲጂታል ፋይናንስ በሁሉም ወረዳዎች 40 ኢንተርፕራይዞች በአጠቃላይ 200 ዜጎችን ወደ ስራ ለመግባት ዝግጁ ሆነው ተደራጅተዋል።