1 068
Подписчики
+224 часа
Нет данных7 дней
+230 день
Архив постов
ለ4ኛው አገር ዓቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ለተሳተፉና ላለፉ ተወዳዳሪዎች የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራ ክህሎት ቢሮ የውድድርና የተነሳሽነት ስሜትን በመፍጠር በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማቱ ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን እና አሰልጣኞችን ባለሙያዎችን ለማፍራት በማለም የ2017 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች ማካሄዱ ይታወሳል፤
በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ የዕውቅና ፕሮግራም ላይም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት በዋናነት በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር በሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በተለይም ከኢንዱስተሪዎችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍን የላቀ ሚና ለማጎልበት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ እና በዚህም አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንና ይህም መርሃግብር አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ከተጣለበት ከፍተኛ ኃላፊነት አንዱ በሙያ ክህሎቱ የበለጸገ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን የመቅዳት፣ የማሻሻል እና የማሸጋገር ስራ ዋነኛው መሆኑን ገልጸው፡፡ በሙያ ክህሎታቸው የበቁ ቴክኖሎጂስቶችና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ለሚሰሩ አሰልጣኞች፤ ሰልጣኞች፤ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች እንዲሁም ለ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ መምህራንና ተማሪዎች ውድድሮችን በማዘጋጀት ማትጋቱ አስፈላጊነቱ ስለታመነበት ቢሮው ይህን ኃላፊነት በመውሰድ ውድድሮችን በማዘጋጀት ዕውቅናና ሽልማት መርሃግብር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
በአጠቃላይ በዚህ መርሃ ግብር በሁሉም ውድድሮች ለተሳተፉና ውጤት ላስመዘገቡ የሰርተፍኬትና የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በቀጣይ ድሬዳዋን ወክለው በፌደራል ደረጃ የሚወዳደሩ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአምራች ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ በሚል መሪ ሀሳብ 136 ኛው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን በዛሬው እለት በድሬዳዋ ደረጃ በድምቀት ተከብሯል ።
#ዜና /አለምአቀፉ የሰራተኞች ቀን በናሽናል ስሚንቶ ፋብሪካ በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች በድምቀት ተከበረ
#DGC ሚያዚያ 22/2017
የናሽናል ስሚንቶ አ/ማ ከድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር "በአምራች ኢንዱስትሪው እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የስራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ" በሚል መሪ ሀሳብ አለምአቀፉ የሰራተኞች ቀን በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች በድምቀት ተከብሯል።
በመርሀ ግብሩም ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አለም አቀፉ የሰራተኞች ቀን ስናከብር ኢንደስትሪዎችን የሚገነቡ አገልግሎቶችን የሚያቀርቡ ኢኮኖሚያችንን የሚያንጹ እጆችን እናከብራለን ብለዋል።
በአለም ለ136ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን የሰራተኞች ቀን ሲከበር ያለፈውን ትግሎች ለማስታወስ ብቻ ሳይሆን ዘመናዊ የስራ ቦታዎችን ለሰራተኞች ክብር እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ላይ ግልጽ አላማ ይዘን በአንድነት እንድንቆም የሚያደርገን ሊሆን ይገባልም ነው ያሉት።
የናሽናል ሲሚንቶ አ/ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ሚስተር ሊዮ የሰራተኞች ቀን ሲከበርም የናሽናል ሲሚንቶ አ/ማ ድርጅትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምርት ና ምርታማነትን በማሳደግ በቁርጠኝነት ስራቸውን እየፈጸሙ ለሚገኙት ሰራተኞች ምስጋና እና የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
በዓሉ በተቋሙ ሲከበርም የኢትዮጵያ እና የቻይና ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብርን ይበልጥ በማቀራረብ በኩል ጎልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።
በመርሀ ግቡሩም በተቋሙ ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ ቆይተው በጡረታ ለተሰናበቱ እና ጥሩ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ሰራተኞች የስጦታ ና የእውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
በመርሀ ግብሩም የናሽናል ሲሚንቶ አ/ማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድሬዳዋ አስተዳደር ተጠሪ ክብርት ወ/ሮ ቢፍቱ መሀመድ፣የናሽናል ሲሚንቶ አ/ማ ከፍተኛ አመራሮች እና በርካታ ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
©️ DDGC
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአጠቃላይ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ https://lmis.gov.et የሚከናወነው ምዝገባ እንቅስቃሴን አስመልክቶ ከወረዳ የአንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
በዋናነት ምዝገባ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እሰከ አሁን የተመዝጋቢዎች ቁጥር የደረሰበት ደረጃ ተገምግሟል፤ በተለይም ስራ ፈላጊ፣ ስራ ያላቸው እና ኢንተርፕራይዞችን ምዝገባ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የታየ ሲሆን በዚህም ሂደት የተመላከቱ ክፍተቶችን ለማስተካከልና በቀጣይ በሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት ደረጃ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ያለውን አፈጻጸም ለማሻሻል እንዲሁም ቁጥሩንም ከፍ ለማድረግ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራር አባላትን የያዘ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ እያሳየ በሚገኘው ከፍተኛ አፈፃፀም ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለትም በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚገኘው የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማችን የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጏል::
ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከተ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ የለውጥ ስራዎችም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል::
ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረገው ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃ መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ሞዴል ተደርጎ መወሰድ የሚችልበት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ሀሳባቸውን ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡበት ኮሌጅ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሚያዚያ 20/2017 ዓ.ም
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሰራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
በአስተዳደሩ የተጀመረው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ እየተካሄደ መሆኑ ተገለጸ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ በሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አዲስ በተከለሰው የሙያ ደረጃና የሆልስቲክ ምዘና አሰጣጥ ስርዓት የሙያ ምዘና በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል በዚህም በአስተዳደሩ 232 የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና በ12 ዘርፎች በ23 ሙያዎች(Occupation) ይመዘናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመሆኑም ከሚያዚያ 7/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት አስር ቀናት በ5 ሙያዎች/occupations/ 38አሰልጣኞች በደረጃ 4 እና 5 Practical እና Knowledge Test የወሰዱ ሲሆን በቀጣይም ያልተመዘኑ አሰልጣኝ መምህራን በተመሳሳይ የሚመዘኑ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ለኢትዮ-ጣልያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሆቴልና ቱሪዝም ዲፓርትመንት አሰልጣኝ መምህራን ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም ስልጠናው በትምህርት ክፍሉ ትምህርትና ስልጠናን በተሻለ መልኩ ለመስጠት እንዲያስችል አሰልጣኝ መምህራኑን በሼፍነት ሙያ እውቀትና ልምድ ባላቸው ተጋባዥ አሰልጣኞች አማካይነት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር በተፈጠረው መልካም አጋጣሚ አሰልጣኞች የእውቀት እና ክህሎት ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው ሆኗል፡፡
በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና በመዘጋጀቱ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ዘንድ ያለውን የክህሎት ክፍተት መሙላት ከመቻሉ ባሻገር በቀጣይ በ2018 ዓ.ም ትምህርትና ስልጠና ዘመን እንዲሁም ለምዘና ዝግጁ የሚያደርጋቸው እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ለኢትዮ-ጣልያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሆቴልና ቱሪዝም ዲፓርትመንት አሰልጣኝ መምህራን ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም ስልጠናው በትምህርት ክፍሉ ትምህርትና ስልጠናን በተሻለ መልኩ ለመስጠት እንዲያስችል አሰልጣኝ መምህራኑን በሼፍነት ሙያ እውቀትና ልምድ ባላቸው ተጋባዥ አሰልጣኞች አማካይነት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር በተፈጠረው መልካም አጋጣሚ አሰልጣኞች የእውቀት እና ክህሎት ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው ሆኗል፡፡
በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና በመዘጋጀቱ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ዘንድ ያለውን የክህሎት ክፍተት መሙላት ከመቻሉ ባሻገር በቀጣይ በ2018 ዓ.ም ትምህርትና ስልጠና ዘመን እንዲሁም ለምዘና ዝግጁ የሚያደርጋቸው እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የአፈጻጸም ደረጃና ውጤታማነት ላይ የዳሰሳ ጥናት ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በኮሌጆች በኩል ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሲሰጥ የነበረውን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የአፈጻጸም ደረጃና ውጤታማነት የዳሰሳ ጥናት ለማድረግና ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ለመለየት፣ የተገኙ ትምህርቶችን ለመቀመርና በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል የሚያስችሉ የመፍትሄ ሀሳቦችን የሚቀርቡበት ይሆናል፡፡
በዚህም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚያደርጉ የቢሮው ባለሙያዎችና ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን በክህሎት፡ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፡ በጥራትና ምርታማነት፡ በገበያ ትስስር የሚታዩ ክፍተቶችንና ውስንነቶችን ለመለየትና ለመረዳት እንዲሁም የተሰጠው ድጋፍ ምን ያህል ውጤታማ እንደነበር ለማወቅ ይህ የዳሰሳ ጥናት የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
