1 063
Подписчики
-224 часа
-77 дней
+130 день
Архив постов
በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።
መድረኩ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ከሚያዘጋጃቸው ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች አካል መሆኑ ታውቋል፡፡
ቢሮው የቀን ሰራተኛ ዜጋውን ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ አምራች ሃይል ባለሙያ በማዘጋጀት የሚሰሩበት ኢንዱስትሪ ድረስ በመሄድ ግንዛቤ እንዲፈጠር ማድረግ ችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለዩኒቨርስቲ እና ኮሌጅ ምሩቃን ስራ ፈላጊዎች የኢንተርፕርነርሺፕ እና የማይንድ ሴት ስልጠና በመሰጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ።
ስልጠናው በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ስራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ስራ እንዲፈጥሩ በሚያነሳሳ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል።
በዚህም ተሳታፊ የሆኑ የዩኒቨርስቲ እና የኮሌጅ ምሩቃን ስራ ፈላጊዎች ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ይጠብቁ የነበሩ ከስልጠናው በሚያገኙት ግንዛቤ በግልም ሆነ ተደራጅቶ ለመስራት መነሳሳት እንዲፈጠርባቸው ታሳቢ ያደረገ ሆኗል።
ቢሮው በአስተዳደሩ ትኩረት የተሰጠውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ የተለያዩ ስራዎችን በተለይም ከኢንዱስትሪዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠርና ተመራቂዎች ተደራጅተው ወደ ሰራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ላይ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ከቀበሌ አንድ ማዕከላት ባለሞያዎች ጋር የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ፡፡
በዚህም ቅድመ ሞዴል፣ ሞዴል፣ እድገት ሽግግርና ከምርጥ ተሞክሮ ቅመራ ጋር በተያያዘ ኢንተርፕራይዞችን የመለየትና ለሞዴልነት የሚበቁ ኢንተርፕራይዞችን ድጋፍና ክትትል በሰፊው ለማካሄድና በኢንተርፕራይዞች መረጃ ምዝገባ (LMIS) ዙሪያ የተሰሩትንና በቀጣይ ክፍተትን በመለየት መሰራት የሚገባቸውን ስራዎች የገመገመ ሆኗል፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ከአስተዳደሩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ከፍተኛ የማደግ አቅም ያላቸውን ኢንቸርፕራይዞች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅማቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ተሰጠ።
ይህም ስልጠና ኢንተርፕራይዞቹ ስራቸውን ዘመናዊ በሆነ መንገድ ለመስራት እንዲችሉና በገበያ ላይ ተወዳዳሪ እና ሌሎች የተሻሉ አሰራሮችን እዲያውቁና እንዲተገብሩ ያስችላቸዋል።
በዚህም ዶት ኢትዮጵያ የተሰኘ ድርጅት ከድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በኮምፒውተር የታገዘ ስልጠና ለ60 ኢንተርፕራይዞች መሰጠት ተችሏል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በምርት ማእከላችን የምናመርታቸው ምርቶች
ዘመናዊ አልጋዎች፣የምግቤት እቃዎች፣ዘመናዊ የመመገቢያ ወንበሮች፣የህጻናት አልጋዎች፣ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፣ዘመናዊ የዶሮ ቤቶች
በጣም በተመጣጣኝ ዋጋን በተሸለ ጥራት እናመርታለን
#ይምጡ ይዘዙን
አድራሻችን፡ ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው መንገድ ላይ እንገኛለን
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ኮሌጁ የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል እንደ መሆኑ መጠን የአካባቢው ወጣቶች በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም የፈጠራና የቴክኖሎጂ ባለቤት እንዲሆኑ ጥሪ ቀረበ፡፡
ከድሬዳዋ አጠቃላይ እና ከአዲሱ ሁለተኛ ትምህርት ቤት የተውጣጡ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መጋቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትምህርት ቤት ቆይታቸው ሊማሯቸው የሚችሉ የተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች በምን አይነት መንገድ እንደሚሰጡና ሰልጣኞች በኮሌጁ የሚገኙ እምቅ እውቀቶችን መጠቀም የሚችሉበትን መልካም አጋጣሚ ለመፍጠር ታልሞ በተዘጋጀው ትምህርታዊ ጉብኝት ላይ መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሀሚድ እንዳሉት ኮሌጁ የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል እንደ መሆኑ መጠን የአካባቢው ወጣቶች በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም የፈጠራና የቴክኖሎጂ ባለቤት መሆን የሚያስችላቸውን ክህሎት ማግኘት ትችላላችሁ ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን አያይዘውም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በአእምሯቸው እያሰቡ በእጃቸው እየሰሩ ሃገርና የሚገነቡ ስልጡን ዜጎች የሚፈሩበት ተቋም እንደመሆናቸው መጠን በዚህ ጉብኝት የተሳተፋችሁ እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች ይህንን ዘርፍ በመቀላቀል ስኬታማ ህይወት እንዲመሩ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት ለተማሪዎቹ ገለጻ ያደረጉት ደግሞ የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም ኮሌጁ በርካታ ስልጠናዎችን እንደመስጠቱ መጠን ለሰልጣኞች የሚሰጣቸው ስልጠናዎች በሙሉ የ21ኛውን ክፍለዘም የስልጠና ሂደት የተከተሉ ናቸው፡፡በተለይ ደግሞ ለ1ኛን 2ተኛ ደረጃ ተማሪዎች ደግሞ የSTEM እና የቴክኖሎጂ ፈጠራን ማጎልበት በሚያስችሉ ወርክሾፖችን በማዘጋጀት ስልጠናዎችን እንዲወስዱ በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዛሬ በተደረገው ትምህርታዊ ጉብኝት ላይ የተሳተፉ የድሬዳዋ አጠቃላይ እና የአዲሱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ባዩት ነገር እጅግ እንደተደሰቱና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ምርጥ ባለሙያዎችን የሚያፈሩ ተቋማ እንደሆኑ ተረድተናል ያሉ ሲሆን በቀጣይም ከሚማሩት ትምህርት ጎን ለጎን በኮሌጁ በሚሰጡ የተለያዩ ስልጠናዎች በመሳተፍ እራሳቸውን የሙያና ክህሎት ባለቤት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 16/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
መልካም ስብዕና ያለው ትውልድን በመገንባት ሙስናን በዘላቂነት መከላከል እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ "ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር " በሚል መሪ ቃል የዓለም የፀረ-ሙስና ቀንን በፖናል ውይይት አክብረዋል::
በክብረ በዓሉን ላይ ለሰራተኛው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው ሙስና በባህሪው በግልፅ የማይታይና ውስብስብ የሆነ መገልጫ ያለው በመሆኑ በመንግስት አቅም ብቻ ተቆጣጥሮ ችግሩን መቅረፍ አይቻልም ያሉ ሲሆን አስተሳሰቡ የዳበረና ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ በመቅረፁ ረገድ እንደ ተቋም የድርሻችንን ማበርከት ይጠበቅብናልም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ሙስና ያልተገባ ጥቅም ማግኘት ብቻ ሳይሆን እንደ ተቋም የአገልግሎት አሰጣጥን በእስታንዳርዱ መሰረት ለዜጎች አለመስጠትንም ይጨምራል ያሉ ሲሆን በዚህም የምንሰጣቸውን አገልግሎቶ ከማዘመን ጀምሮ ሁላችንም ባለንበት የስራ ዘርፍ የድርሻችንን መወጣት ስንችል ሀገር በማሻገር ሂደት ውስጥ አሻይራችንን ማሳረፍ እንችላለንም ብለዋል::
በመድረኩ ክብረ-በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀው ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለሰራተኛው ቀርቦ ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይም በተሳፊዎች ውይይት ተደርጎበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የወጣቶች ክንፍ የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ።
የጥያቄና መልሱ መርሃግብር አላማም የብልፅግና ፓርቲ ወጣት አባላትን ለማብቃት ሲሆን በዚህም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የፓርቲውን ዕሳቤ የተከተለ ተሳታፊነትን ማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶታል።
የጥያቄና መልስ ውድድሩ ጥያቄዎች በዋነኝነት በብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ወጣቶች ክንፍ መተዳደሪያ ደንብ ዙሪያ ላይ ሲሆን ሰፊ ሀገራዊ ጉዳዮችንም የዳሰሰ ሆኗል።
ለጥያቄና መልስ ውድድሩ አሸናፊዎች ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደተር ስራና ክህሎት ቢሮ ከጤግሮስ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ለአስተዳደራችን ስራ ፈላጊዎች ምርጥ አማራጭ የስራ እድል ይዞ ቀርቧል፡፡
በተመረጡ 4 የንግድ ዘርፎች ባለ ሱቅ ሊያደርጋችሁ ነው
#እንዴት?
በሸቀጣ ሸቀጥ በአልበሳት በኮስሞቲክስ እና በስቴሽነሪ ለተደራጁ ሦስት ሦስት ወጣቶች ሙሉ የሱቅ እቃ በነጻ ያቀርባል በመጀመሪያ የተረከቡትን ሸጠው ሲጨርሱ እና ዋናውን ሲመልሱ ሌላ ዙር ሙሉ የሱቅ እቃ ያቀርባል አሁን ሲጨርሱ ዋናውን መልሰው ሌላ ዙር ይመጣሎታል
#ይህንን አስገራሚ እድል ተጠቃሚ ለመሆን ምን ማድረግ አለብን?
3 ሆኖ መደራጀት ለስልጠና እያንዳንዱ የማህበር አባል 4500 ብር መክፈል (የአሰልጣኞች ወጪና የመመዝገቢያ ) በመጨረሻም ንግድ ፍቃድ አውጥቶ ሱቁን ብቻ ማዘጋጀት፡፡
#ከዛስ?
ከዛማ ምን ጥያቄ አለው የሱቅ ባለቤት በመሆን አስተማማኝ የስራ እድል ይፈጠርላችኋል በአምስት አመት ውስጥ ትልቅ ሱፐር ማርኬት እንዲከፍቱ ድጋፍ ይደረግላችኋል፡፡
ተጨማሪ መረጃ በሁሉም ወረዳዎች (ቀበሌ) የስራ እና ክህሎት ማስተባባሪያ ጎራ እያላችሁ መረጃውን መውሰድ ትችላላችሁ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የሳቢያን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጉብኝት አካሄዱ::
ኮሌጁ ከ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር ባለው ቅንጅትና ተማሪዎች ላይ እየፈጠረ የሚገኘውን ግንዛቤ መነሻ በማድረግ ተማሪዎች ስለዘርፉ ይበልጥ እውቀት እንዲኖራቸው እንዲሁም ኮሌጁ ስልጠናዎችን የሚሰጥበት አጠቃላይ እንቅስቃሴ እንዲመለከቱ ለማድረግ በአካል ተገኝተው እንዲጎበኙ ማድረግ ተችሏል::
ከጉብኝቱ አስቀድሞ ለተማሪዎቹ ኦረንቴሽን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ በቀጣይ የክህሎት ባለቤት ወደሚያደርጋችሁ ኮሌጃችሁ እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን አክለውም እዚህ በኮሌጃችን ላይ የሚሰጡ ስልጠናዎች ከመደበኛው ትምህርት የሚለይባቸው ዋነኛ ምክንያት ሰልጣኞች አምስቱንም የስሜት ህዋሶችን ተጠቅመው የሚሰለጥኑበት በመሆኑ 100% ውጤታማና ብቁ የክህሎት ባለቤት የሆነ ዜጋ የሚፈራበት ዘርፍ በመሆኑ ነውም ብለዋል::
ም/ል ዲኑ አክለውም ኮሌጁ በቀጣይ ተማሪዎቹ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአጫጭር ስልጠናዎች በመረጡት የሙያ መስክ በማሰልጠን የሙያ ባለቤት ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልፀው ተማሪዎች በቀጣይ በኮሌጁ የሚኖራቸውን ቆይታ ራሳቸውን ለማብቃት ሊጠቀሙበት እንደሚገባም አሳስበዋል::
የሳቢያን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በጉብኝቱ ኮሌጁ ያለውን የማሰልጠን አቅምና STEMን መሰረት ያረጉ የማሰልጠኛ ወክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይም በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ በFinishing እንዲሁም በFurniture Making ሙያ ስልጠናዎችን በተከታታይ የሚሰለጥኑ መሆኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
