ru
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Открыть в Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Больше
3 309
Подписчики
-224 часа
-97 дней
-3630 день
Архив постов
📚#ፍኖተ_እግዚአብሔር📚 ➥#በምሥጢረ_ሥላሴ ዙሪያ በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ከተጻፉ መጻሕፍት ቁጥር #፩ ምርጫዬ ነው። #ፍኖተ_እግዚአብሔር። መጋቤ ሐዲስ ልዑለ ቃል አካሉ Leulekal Alemu ም
📚#ፍኖተ_እግዚአብሔር📚 ➥#በምሥጢረ_ሥላሴ ዙሪያ በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ከተጻፉ መጻሕፍት ቁጥር #፩ ምርጫዬ ነው። #ፍኖተ_እግዚአብሔር። መጋቤ ሐዲስ ልዑለ ቃል አካሉ Leulekal Alemu ምንባባቱን ከመጻሕፍት፣ በተለይ ከሃይማኖተ አበው ያቆራኙበት መንገድና የሊቁን ታሪክ ሰፋ አድርገው ማቅረባቸው የሚያስመሰግን ተግባር ነው። በመታተሙ ደስ ብሎኛል። መጋቤ ሐዲስንም ያሳትሙልን ብዬ ደጅ የጠናሁ ይመስለኛል። ...መጽሐፉ ረዘም ላለ ጊዜ በሊቃውንቱ በቅብብል እየዳበረ መጥቶ በአለቃ ኅሩይ ፍጽምና እንዳገኘ አስባለሁ። ከምደነቅባቸውና ከአባቶቼ የማመሥጠር ጸጋ የተነሣ እግዚአብሔርን ከማመሰግንባቸው መጻሕፍት አንዱ ነው። ✍️በአማን ነጸረ [ደብተራና የሕግ ባለሙያ] 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚#የቤተክርስቲያን_ታሪክ_በኢትዮጵያ 📚 ...ረዘም ላለ ጊዜ ከገበያ ጠጠፍቶ የነበረው ይህ ተወዳጅና ተፈላጊ መጽሐፍ እነኾ በድጋሚ ታትሟል.... ስለ መጽሐፉ የተሰጠ አስተያየት የሚከተለውን ይመስላ
📚#የቤተክርስቲያን_ታሪክ_በኢትዮጵያ 📚 ...ረዘም ላለ ጊዜ ከገበያ ጠጠፍቶ የነበረው ይህ ተወዳጅና ተፈላጊ መጽሐፍ እነኾ በድጋሚ ታትሟል.... ስለ መጽሐፉ የተሰጠ አስተያየት የሚከተለውን ይመስላል ..👇 ➥ታሪክ ለአንድ ሕዝብ እና አገር የወደፊት ጉዞ መነሻ መሠረት ነው፡፡ ስለሆነም ለአንድ ሕዝብ እና አገር የወደፊት ህልውና ቀጣይነት አስፈላጊ ከሆኑት ነገሮች አንዱ ታሪክ ነው፡፡ የአንድን ሕዝብም ሆነ አገር የወደፊት ህልውና ሥልታዊ በሆነ መንገድ ማጥቃት የሚፈልጉ አካላትም ሥራቸውን የሚጀምሩት ታሪኩን ከማበላሸት ነው፡፡ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ያደረጉትና እያደረጉ ያሉትም ይህንኑ ነው፡፡#መምህር ግርማ ባቱ ያዘጋጀው ይህ መጽሐፍ በዚህ ረገድ አስፈላጊ ከሆኑ መጻሕፍት የሚመደብ ነው፡፡ ስለ ታሪክ ያለን አረዳድ እንዴት ሊሆን እንደሚገባው አቅጣጫ ከማሳየት ጀምሮ፣ በሚያነሣቸው ጉዳዮች ላይ ከብዙ ታሪካዊ ምንጮች በተጨመቀ ዕውቀት የተጻፈ ጥሩ መጽሐፍ ነው፡፡ የተለያዩ ምንጮችን በታሪካዊ ማስረጃ በመመዘን፣ እንዲሁም የተሳሳቱ ትርክቶችን ስህተትነት በማሳየት፣ በዚህ ረገድ ያሉ ክፍተቶችን የሚሞላ መጽሐፍ ነው፡፡ ይህን መጽሐፍ ስላበረከተልን መምህር ግርማ ባቱን ከልብ እያመሰገንኩ፣ ለወደፊቱም በዚሁ መንገድ በመቀጠል ሌሎች መጻሕፍትን እንደሚያበረክትልን ተስፋዬ ታላቅ ነው፡፡ ✍️ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚#ዜናሁ_ለእግዚእነ📚 የአራቱን ወንጌላት ትርጓሜ በአንድ በማንበብ ልዩ ግንዛቤና ምሥጢር እንደሚገለጥልን እርግጠኛ የሆንኩት ይህን መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ ሳለሁ ነበር፡፡ አራቱ ወንጌላት በተለመደው
📚#ዜናሁ_ለእግዚእነ📚 የአራቱን ወንጌላት ትርጓሜ በአንድ በማንበብ ልዩ ግንዛቤና ምሥጢር እንደሚገለጥልን እርግጠኛ የሆንኩት ይህን መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ ሳለሁ ነበር፡፡ አራቱ ወንጌላት በተለመደውና በጥንታዊው የአንድምታ ትርጓሜ ላይ የአቀራረብ ለውጥ ብቻ ተደርጎበት የአንድምታ ትርጓሜ ተማሪዎችን ወደ ዘመናዊ ስልቶች ዘመናዊ ተማሪዎችን ወደጥንቱ መንገድ ይህ መጽሐፍ ብዙዎችን እንደሚጠቅም ከዚህ በፊት ኤቫንጌልዮን በሚል ርእስ በ2003 ዓ.ም የማቴዎስን ወንጌል በከፊል አዘጋጅቼ ባቀረብኩት መጽሐፍ አረጋግጫለሁ።ስለዚህ ይህ መጽሐፍ ደግሞ ኤቫንጌልዮን ክፍል አንድ እስከ ክፍል ስድስት ተብሎ ተከፋፍሎ ሊቀርብ የነበረውን በአንድ በማጠቃለል ያቀረብኩት መሆኔን አንባቢ እንዲረዳልኝ በትህትናና በአክብሮት እየጠየቅሁ መልካም የንባብ፣ የምርምር፣ የጥናትና የጸሎት መጽሐፍ እንዲሆንልዎ መልካም ምኞቴ ነው ። ✍️ከአዘጋጁ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧እነኾ በድጋሚ ታትሟል ..! #የመምህር_በትረ_ማርያም_አበባው የመጀመሪያው ዕትም በ15 ቀናት ውስጥ ከገበያ ያለቀ ኹሉም የተሻማበት መጽሐፍ ... 📚#ኦርቶዶክሳዊ_ተዋስኦ [መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተ
💧እነኾ በድጋሚ ታትሟል ..! #የመምህር_በትረ_ማርያም_አበባው የመጀመሪያው ዕትም በ15 ቀናት ውስጥ ከገበያ ያለቀ ኹሉም የተሻማበት መጽሐፍ ...       📚#ኦርቶዶክሳዊ_ተዋስኦ [መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠየቁ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው] #በዚህ መጽሐፍ በምዕመናን መካከል ለሚመላለሱ ጥያቄዎች አስቦ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ከርሠ መጻሕፍትን በርብሮ መልስ አዘጋጅቶ ማቅረቡ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ሥራ ሆኖ ስላገኘሁት ጥያቄ ቢኖርብንም ባይኖርብንም የሚያነሣቸው ጥያቄዎችና የሚመልሳቸው መልሶች የዕውቀት ዳርቻችንን ስለሚያሰፉልን እንድታነቡ እጋብዛለሁ። ✍️ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚#ተንከተም📚 👉ይህ መጽሐፍ፥ ጸሎተ ሃይማኖትን እየጸለዩ የይዘቱን ጥልቀት የማያወቁትን ሁሉ ከአምስት ደቂቃ ላልበለጠ ጊዜ የሚጸልዩት ጸሎት ምን ያህል ሰፊ እንደሆነ የሚያመላክት ግሩም መጽሐፍ ነ
📚#ተንከተም📚 👉ይህ መጽሐፍ፥ ጸሎተ ሃይማኖትን እየጸለዩ የይዘቱን ጥልቀት የማያወቁትን ሁሉ ከአምስት ደቂቃ ላልበለጠ ጊዜ የሚጸልዩት ጸሎት ምን ያህል ሰፊ እንደሆነ የሚያመላክት ግሩም መጽሐፍ ነው። እንግዲያውስ ከ፲፪ቱ አበው የተቀበሉትን፣ ሊቃውንት በ፲፪ አንቀጾች የቀመሙትንና ፲፪ በሮች ወዳሏት መንግሥተ ስማያት የሚያስገባንን ጸሎተ ሃይማኖት በ፲፪ ምዕራፎች ላቀረቡልን ሊቀ ሊቃውንት፥ ዕድሜ፣ ጤና እንዲሰጥልኝ እየተመኘሁ፡ ባለ፲፪ የሆናችሁት እንድታነቡት በ፲፪ቱ ሐዋርያት ስም እጋብዛለሁ፡፡ ሊቀ ሊቃውንትን ስምዐኮነን እና ሌሎች ሊቃውንትንም ልክ እንደዚህ የተቋጠሩትን እንድታፍታቱልን በዚሁ አጋጣሚ አሳስባለሁ፡፡ ✍️ከዲ/ን ብርሃኑ አድማስ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📔#መድሎተ_ጽድቅ [በመምህር ያረጋል አበጋዝ] #መንፈስ_ቅዱስ በነቢይ ዳዊት አድሮ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላኪየ ዘመሀሮን ጸብአ ለእደውየ ወቀትለ ለአጻብእየ - ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ለእጆቼ ሰልፍ
📔#መድሎተ_ጽድቅ [በመምህር ያረጋል አበጋዝ] #መንፈስ_ቅዱስ በነቢይ ዳዊት አድሮ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላኪየ ዘመሀሮን ጸብአ ለእደውየ ወቀትለ ለአጻብእየ - ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ለእጆቼ ሰልፍን፣ ግራ ቀኝ ማማተብን፣ ለአእምሮዬ እቀውትን ለአንደበቴ መልስን የሰጠኝ ይክር ይመስገን ብሏል መዝ. 143፡1 “መድሎተ ጽድቅ - የእውነት ሚዛን በእጅህ አስጨብጦ፤ ቀዳሚውን፣ ማእከላዊውን፣ ደኃራዊውን፤ አማኒ፣ መናፍቅ፣ ተርጓሚ፣ ተቃዋሚ፣ አስተማሪ፣ ተከራካሪ የሚገናኝበት የምሥጢር ሜዳ ስለ ጻፍህ መንፈስ ቅዱስ በጥበቡ አሠርቶሃል፡፡ በተለይም ዛሬ በልቡናው ሳይሆን በሆዱ የሚያስብ አስተማሪ (ሰባኪ) ነኝ ባይ እንደ ተምች በወረደበት ጊዜ፣ በትረ ኖሎት ያዝን ባዮችም ከሜዳው ሸሽተው ከበጐች ተለይተው በትራቸውን በበትረ መንግሥት በቀየሩበት ጊዜ ይህን መጽሐፍ ማውጣትህ የተኙትን ያነቃል፣ እምነታቸው የዛገባቸውን ይወለውላል፣ መምሰል የማረካቸውና መሆን ያቃታቸውን ከቻሉ እንዲያስቡ ያደርጋል እላለሁ፡፡ ✍#የንታ_መምህር_ደጉ_ዓለም_ካሳ [የመጻሕፍት እና የቅኔ መምህር] #የንታ ያለምክንያት ይህን እንዳላሉ ልብ ልትል ይገባል!!ጊዜውን የሚዋጅ ይህን ምርጥ የጦር እቃ እነኾ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧ዜና_መጽሐፍ 📚ምድራዊ መልአክ ቅዱስ_ያሬድ #የቅዱስ_ያሬድን ድርሰቶች አብዝተን የምንጠቀምበት ዐውድ ምሥጋና (Doxology)ነው።አዘጋጁን ከዚህ ቀደም በማውቅበት ሥራው ቅዱስ ያሬድን “የቤተ ክር
💧ዜና_መጽሐፍ 📚ምድራዊ መልአክ ቅዱስ_ያሬድ #የቅዱስ_ያሬድን ድርሰቶች አብዝተን የምንጠቀምበት ዐውድ ምሥጋና (Doxology)ነው።አዘጋጁን ከዚህ ቀደም በማውቅበት ሥራው ቅዱስ ያሬድን “የቤተ ክርስቲያ ብርሃን ቅዱስ ያሬድ” በሚል ገልጦት ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በስፋትና በምልዓት ልቆ በመጣው ሥራው “ምድራዊው መልአክ ቅዱስ ያሬድ” ብሎታል፡፡ እውነትም በምድር እንደሰው ኖሮ እንደመላእክት በንጽሕና እና ሕይወታቸው በሆነ ምስጋና የተለየ ቅዱስ አባት ነውና መጠሪያው እና የመጽሐፉ ርእስ ተገቢ ነው እላለሁ፡፡ ይህን ለማስረዳት የሄደበትም ርቀት እጅግ የሚያስመሰግን ነው፡፡ እንዲሁም ስለ ቅዱስ ያሬድ ሕይወት፣ የሥራዎቹን ሥርዓተ አምልኳዊ መሠረታዊነት ከይዘት ትንተና፣ ከታሪክ ምስክሮችና ትውፊታዊ ዋቢዎች ጋር ያሰናዳበት መንገድ ድንቅ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊውን ኦርቶዶክሳዊነት የማወቂያ መንገድ ነው፡፡ ወደዚህ መንገድ ኑ ይህን መጽሐፍ አንብቡ፣ ምስክሮቻቸን ድንቅ እንደሆኑም ዕወቁ፡፡ በሕይወት ትጠቀሙበታላችሁ፡፡ ወንድማችን ታደሰ ዓለማየሁም እጅህን ይባርከው፣ ለበለጠው ሥራም ያትጋህ!! ✍[ረዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ግርማ ባቱ]፦በቅድሥት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና የሥነ መለኮት መምህር 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደ
#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ታሪኮች_ለልጆች #የልጆች የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች በመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር የታተመ ውስጡ ከለርድ ልጆችን በሚማርክ መልኩ የተዘጋጀ ነው። ልጆቻችንን የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንደመኾናቸው በሃይማኖትና በወንጌል ኮትኩተን   በማሳደግ ኃላፊነታችን እንወጣ ዘንድ እንዲያስፈልግ ልብ ይሏል ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚#መዋዕያን #በዚህ መጽሐፍ፦ጽሑፎቹ በምንጭ አጠቃቀም ረገድ የሀገር ውስጥም የውጪም ምንጮችን ግብዓት አድርገዋል። የውጮቹን ምንጮች ተጠቅመን በውስጣዊ እይታ ለማንጠርና ዳግም ታሪኩን በብሔራውያን ሊ
📚#መዋዕያን #በዚህ መጽሐፍ፦ጽሑፎቹ በምንጭ አጠቃቀም ረገድ የሀገር ውስጥም የውጪም ምንጮችን ግብዓት አድርገዋል። የውጮቹን ምንጮች ተጠቅመን በውስጣዊ እይታ ለማንጠርና ዳግም ታሪኩን በብሔራውያን ሊቃውንት ኅሊና ተገብቶ አማናዊውን ምስል ለማግኘት ጥረት ተደርጓል - በተለይ የሚሲዮናውያኑን ጉዳይ በሚዳስሰው ምዕራፍ አራት። በተፋላሚ ሜዳም ብቅ እያሉ የቅድመ መከላከል ተግባር መከወን የዘመኑ ፈሊጥ ስለሆነ፡፡ ቤቱ በቂ መልስ ያለበት ነውና ሐሳብ አይፈራም። የ19ኛው ክፍለ ዘመን ሊቃውንት ተዋሥኦ ያንን ያሳያል። በዚህች ንዕስት መጽሐፍ በክብር አርፈው የድል አድራጊነት አክሊል የደፉትን ቅዱሳን የአሸናፊነት ታሪክ በያዘው ቅዱስ ጽሕፈት (ገድል) ሁለንተናዊ ይዘት ጀምረን በዘመናዊት ኢትዮጵያ ዋዜማ ቤተ ክርስቲያናቸውን በክብር ለማቆየት ተገቢውንና ዘመኑ የሚጠይቀውን ተጋድሎ ቢፈጽሙም በቅጡ ባልተዘከሩት፣ ታሪካቸው በተጻራሪዎቻቸው ተለባብሶ ተጽፎ በተዳፈነው ሊቃውንት የተጋድለ ሒደት እንቋጫለን፡፡ መልካም የንባብ ጉዞ ከመዋዕያኑ ጋራ! ✍️በአማን ነጸረ ➯ይህንና መሰል ጥዑምና ብስለት ያላቸው መጻሕፍት ለማግኘት #ጎራ_በሉ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧እነኾ ይህ ዕንቊ -የምዕመናን ምርኩዝ -የጉባኤ ቤትና የሊቃውንት ስንቅ - የመነኮሳት አለኝታና መካሪ የኾነ መጽሐፍ ገበያ ላይ እንደሌለ ይነገራል እርግጥምም የለም...እኛም በሰማን ጊዜ ልንጽፍላች
💧እነኾ ይህ ዕንቊ -የምዕመናን ምርኩዝ -የጉባኤ ቤትና የሊቃውንት ስንቅ - የመነኮሳት አለኝታና መካሪ የኾነ መጽሐፍ ገበያ ላይ እንደሌለ ይነገራል እርግጥምም የለም...እኛም በሰማን ጊዜ ልንጽፍላችኹ ወደድን ..! የተወሰኑ ቅጂዎች እኛ ዘንድ የሚገኙ ሲኾን ስለመጽሐፉ ደግሞ የዲያቆን ያረጋልን ክታብ እየጋበዝን በኋላ ካለቀ እንዳትቆጩ እናሳስባለን ..!👇 ❝ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡❞            ✍️ ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ሳታቋርጡ_ጸልዩ "ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተጠምዶ መዋል አይችልም" አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው ድምፅ ሳይሆን ሀሳብ ነው ፤ እጅ ሳይሆን እደ ልቦናን ማንሣት  ነው፤   አፍአዊ ሳይሆን ውስጣዊ አኳኋን ነው ።ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፤ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከሆነ ጸሎትህ ሥልጡን ነው ።     #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

#ሳታቋርጡ_ጸልዩ "ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተጠምዶ መዋል አይችልም" አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው ድምፅ ሳይሆን ሀሳብ ነው ፤ እጅ ሳይሆን እደ ልቦናን ማንሣት  ነው፤   አፍአዊ ሳይሆን ውስጣዊ አኳኋን ነው ።ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፤ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከሆነ ጸሎትህ ሥልጡን ነው ።     #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

📖"ነገረ ማርያም" [በሶርያ አባቶች እና ሌሎች ] ☞ መነሻው #የመንፈስ_ቅዱስ_ዋሽንት በተሰኘው በተወዳጁ #ቅዱስ_ኤፍሬም ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጻፋቸው ድርሳናት ነው ፥ ከዚም መለ
📖"ነገረ ማርያም" [በሶርያ አባቶች እና ሌሎች ] መነሻው #የመንፈስ_ቅዱስ_ዋሽንት በተሰኘው በተወዳጁ #ቅዱስ_ኤፍሬም ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጻፋቸው ድርሳናት ነው ፥ ከዚም መለስ ሲባል እያንዳንዱ ገጽ ሕይወት ያለው ነው!-መምህር ዲያቆን ሽመልስ መርጊያ በርካታ የትርጉም ሥራ አበርክተውልናል... ግን እመኑኝ ይኽኛው እጅግ ልዩ ነው ልዩ ስለኾነችዋ ስለ #ድንግሏ_እመቤት -ከጽንሰቷ እስከ እርገቷ ጥፍጥ ባለ መልኩ ስለጌታም አስተዳደግ በመጠኑ የሚያትት ስለሐዋርያቱና -እመቤታችን የጠበቀ ወዳጅነት በተለይ በሶርያ ቤተክርስቲያን እዴት እንደምትከበር ሲተነትን አንዳንድ የእመቤታችን ክብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፈጠረችው እንጂ በሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ-ክርስያናት የማትከበር ለሚመስላቸው መናፍቃን የማያዳግም ምላሽ የሚሰጥ የሚሉትም ኹሉ የእነርሱ ተረት እና እሳቤ እንደኾነ የሚያስረዳ..ነው። በጥቅሉ እጅግ ተወዳጅ መጽሐፍ ነው! -ስታነቡት እንደምትጋሩኝ አልጠራጠርም ...! 💧ሱባኤውን በንባብ ለማሳለጥ ደግሞ አይነተኛ ምርጫም ነው!መጽሐፉን ለማግኘት ደግሞ ምንም መጨነቅ አይጠበቅም #በግዮን_መጻሕፍት በተለመዱት የሥራ ቀናት እና እኹድ ደግሞ ከቅዳሴ ሰዓት በኋላ ተሰናድቶ ይቆያችኋል! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✤ #በአታ_ለእግዝእትነ_ወእምነ_ብጽዕት_እም_ብጹዓን_ቅድስተ_ቅዱሳን_ወላዲተ_ቃል_ድንግል_ማርያም፤ ✤ በዓለ ሢመቱ ለቅዱስ ፋኑኤል ሊቀ መላእክት፤ ዕረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ እመቤታችን በአባት በእና
#በአታ_ለእግዝእትነ_ወእምነ_ብጽዕት_እም_ብጹዓን_ቅድስተ_ቅዱሳን_ወላዲተ_ቃል_ድንግል_ማርያም፤ ✤ በዓለ ሢመቱ ለቅዱስ ፋኑኤል ሊቀ መላእክት፤ ዕረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ እመቤታችን በአባት በእናቷ ቤትም ፫ ዓመት ተቀመጠች፤ ከእንግዲህ ወዲያማ ወስደን እንስጥ ብለው ይዘዋት ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ ከዚያውም ደርሰው እነሆ ተቀበሉን አሏቸው * ይኸውም የተደረገው ታኅሣሥ ፫ ዕለት ነው፤ በአታ የሚለው ስያሜም የተሰጠው በዚሁ ነው፡፡ ‹‹አመ ፫ ለታኅሣሥ በኣታ›› እንዳለ መቅድመ ተአምር፡፡ በዚህም፤ #መቅደሲቱ_ወደ መቅደስ ገባች፤ #ቅድስቲቱ_ወደ ቅድስት ገባች፤ #ክብርቲቱ_ወደ ክብርት ቤቷ ገባች፤ #ልዩ_የሆነችው_ወደ ልዩ ሥፍራ ገባች፤ #ቅድስተ_ቅዱሳኗ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ገባች፤ #ንጽሕተ_ንጹሐኗ ወደ ንጽሕ አዳራሽ ገባች፤ #ቤተ_መቅደሷ ወደ ቤተ መቅደስ ገባች፡፡ #በዓለ_ሢመቱ_ለቅዱስ_ፋኑኤል_ሊቀ_መላእክት፤ #ሰዳዴ አጋንንት ነው፤ /ሄኖክ 10፥8፣ ድርሳን ዘፋኑኤል/ #መጋቤ ድንግል ነው፡፡/ተአምረ ማርያም/ #ማኅሌታዊ ነው፤ #በመንበረ መንግሥቱ ዙሪያ ከሚቆሙት ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው፡፡ /ሄኖክ 20፥39/ #ለመልካም ነገሮች ከሚራዱ መላእክት አንዱ ነው /መዝ. 33፥7/ #ካህነ ንስሐ ነው /ሄኖክ 10፥5/ #ዐቃቤ ጻድቃን ነው፡፡ /2ኛ ነገ. 6፥14/ ✤#ኢትዮጵያዊው_አቡነ_ዜና_ማርቆስ_በዓለ_ዕረፍታቸው ነው፡፡ እኒህ ታላቅ አባት በምድረ ጉራጌ በሚገኘው በምሁር ኢየሱስ ገዳም 40 ዓመታትን ሱባኤ የገቡ፤ እንዲሁም በርካታ ሊቃውንትን /አባ ጽጌ ድንልንና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታን ጨምሮ ሌሎችን ሊቃውንትም/ ያፈሩ ፈርጥ ሲኾኑ፤ በስተመጨረሻ በተአምራት የተሞላውን ታላቁን ገዳም #ደብረ_ብሥራትን (ጅሩ) መሥረተው በክብር አርፈዋል #ከቅዱሳኑ_በረከት_የክፈለን!!🙏

#እንኳን_ለቅዱስ_ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል (የልደት ቀን) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ ይባላል፡፡ በነቢ
+1
#እንኳን_ለቅዱስ_ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል (የልደት ቀን) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ ✤  የሰማርያው ነቢይ ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ ይባላል፡፡ በነቢይነትም ሆነ በብቃት ኤልያስን የሚያክል፤ በሥራው የሚወክል ከእሱ በፊትም ኾነ በኋላ በተአምራት የተሞላ እሳት ለበስ ነቢይ እሱ ከመረጠው ከደቀ መዝሙሩ ከኤልሳዕ በቀር አልተነሳም፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ከኢዮርብዓም እስከ እርሱ ድረስ ለአያሌ ዓመታት በሰይጣን ግፊት በሰው ሠራሽ ጣዖት የተመረዘ በኃጢአትም ረዘረዘ፣ የግፈኛው አክአብና የዘማዊቷ ኤልዛቤልን መንግሥት በሦስት ዓመት ከመንፈቅ በከባድ ድርቅ በመናጥ፣ እንዲሁም አፈር እንደበላው ብረት የዛገ አስተሳሰባቸውን በሰው ደምና በቅሚያ ገንዘብ የተሞላ ሰውነታቸውን በማን አለብኝነት ያበጠ ልባቸውን እንደሰም  በማቅለጥ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ያሳጣ በፈጣሪው ለዚህ ሥራ የተመረጠ ሰመ ጥር ነቢይ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ነውና፡፡ ኤልያስ የከተማ ነቢይ ብቻ አይደለም ባሕታውያን ተብለው ከሚጠሩት ነቢያተ ጽድቅም አንዱ እንደነበር ሕልውናው ምስክር ነው፡፡ ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡

#ራእየ_ኒፎን የይቅርታ ፏፏቴ የርኅራኄ ባለጠጋ የሆንክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፊትህን ከእኔ አትመልስ፤ ማረኝ፤ ይቅርም በለኝ፡፡ ጌታ ሆይ “አላውቅህም አትበለኝ!' ጌታ ሆይ እስከዛሬ የት ነበር
#ራእየ_ኒፎን የይቅርታ ፏፏቴ የርኅራኄ ባለጠጋ የሆንክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፊትህን ከእኔ አትመልስ፤ ማረኝ፤ ይቅርም በለኝ፡፡ ጌታ ሆይ “አላውቅህም አትበለኝ!' ጌታ ሆይ እስከዛሬ የት ነበርክ?' ብለህም አትቆጣብኝ፡፡ በኃጢአት የቆሸሽሁ፧ በበደል እንደ ጢስ የጠቆርሁ፤ ሕግህን በመተላለፍ የበሰበስሁ፤ ፍቅርህን በመርሳት የተዋረድሁ፤ በርኵሰት የሽተትሁ፤ በዲያብሎስ ምክር የጠፋሁ፤ ሰዎች በሚሠሩት አስነዋሪ ሥራም ዋነኛ የሆንኩ የማልጠቅም ትቢያና ጉድፍ ልጅህን አትናቀኝ፤ ከፊትህም አፍሬ አልመለስ፡፡ መምህሬ ሆይ! ከእኔ አትራቅ፤ ራራልኝ፤ አድነኝም፡፡ ሰው ወዳጅ ሆይ “አንተ የኃጢአተኛን በንስሐ ከክፉ መንገዱ መመለሱን እንጂ መጥፋቱን እንደማትሻ' አውቃለሁና ተመልሰህ እስክትረዳኝና ምሕረትህን እስካገኝ አላርፍም፡፡" (ራእየ ኒፎን ገጽ 59) 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📚መጻሕፍትን ለመጻሕፍት ተማሪዎች📚 📚አንድ መጽሐፍ - ለአንድ ተማሪ📚 ➲የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ“ፈለገ ጥበብ የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ መታሰቢያ የ፬ቱ ጉባኤያት ትርጓሜ አዳሪ ትምህርት ቤት” ሰሞኑን ከምእመናን መጻሕፍትን በማሰባሰብ ላይ ይገኛል!! ➠ለምን መጻሕፍትን ማሰባሰብ አስፈለገ!? 🖊📚 መጻሕፍት ለሰው ኹሉ አስፈላጊዎች መኾናቸው ምንም አያጠያይቅም ፥ ጉባኤያችን ደግሞ የመጻሕፍት ጉባኤ ቤት መኾኑ ፥ ደቀመዛሙርትም ወደ አገልግሎት ሊሰማሩ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ከመገኘታቸው አንጻር ፥ ከትርጓሜ ትምህርታቸው በተጓዳኝ ኹሉንም የሐሳብ ዘውጎች በንባብ የማየት ዕድሉ ሊመቻችላቸው የሚገባ በመኾኑ ነው። ይኽም ለነገ አገልግሎታቸው ስንቅ ከመኾኑም ባሻገር - ለእንግዳ አስተሳሰቦች አዲስ ካለመኾናቸውም በተጨማሪ .. መረዳት የታከለበት ርቱዓዊ የኾነውን ኦርቶዶክሳዊ እሳቤ ከሐሳባት ኹሉ ከፍ አድርገው በልዕልና ለማንበር [ለማስቀመጥ/ለመግለጥ] ይጠቅማቸዋል። ለዚኽም “የመጻሕፍት ክምችቱ” አስፈልጓል። ➠ሌላስ ምክንያት ይኖሮ ይኾን!? 🖊📚 እንደ ጉባኤ ቤታችን የምንከተላቸው ልዩ ልዩ መርሖዎች አሉን ፤ ከእነሱ መካከል አንዱ ፥ ደቀመዛሙርት ከወንበራቸው ማካከል አንዱን መጽሐፍ [ለምሳሌ የማቴዎስን ወንጌል] ሲዘልቁ ፥ ወደ ቀጣይ ወንበር ከማለፋቸው በፊት ፥ በዘለቁት መጽሐፍ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ፥ በዚኽ ጊዜ የማ’ይ’ወ’ጣ የመጽሐፍ ዳገት ፣ የማይወረድ የንባብ ቁልቁለት ፣ የማይሮጥ የተብሰልስሎት ሜዳ አይኖርም። በዚኽ መካከል የመጽሐፍ እጥረት ቢከሰት ተነሣሽነትን ያሳጣል ፤ የእይታ አድማስን ያሳጥራል ፤ የምርምር መጠንን ይገድባል ፤ ይኽ እንዳይከሰት ፥ ደቀ መዛሙርት ዋኝተው የማያቋርጡት ፥ ዝቀው የማይጨርሱት የመጽሐፍ ክምችት መኖሩ እጅግ አስፈላጊ በመኾኑ “የመጻሕፍት ስብስቡ” አስፈልጓል። ➠ሌላ ተጨማሪ ምክንያት ይኖር!? 🖊📚 አንባቢ በብዙ ጉዳዮች ላይ መረዳት ይኖረዋል ፥ መረዳቱንም ለሌሎች በተለያየ ቅርጽ ያጋራል። አሳቢነትም ደራሲነትም ከንባብ ማሕፀን ይወለዳሉ። የጉባኤያችን ደቀመዛሙርት ደግሞ አንደኛ የመጻሕፍት ተማሪዎች ናቸው ፥ ሲቀጥል በንባብ ልምድ የዳበረ ሰብእናን ከፈጠሩ - ደራሲ በመኾን በድርሰት ቤተክርስቲያንን የማገልገል ዕድላቸው ሰፊ ነው ፤ በመኾኑም ጉባኤ ቤታችን ከደቀመዛሙርት መካከል ደራሲያንንም የመፍጠር ዓላማ አለው። የአባቶችን በሳል የድርሰት ወርቃማ ዘመን ለመድገም - ደቀመዛሙርት የንባብ ልምድን እንዲያዳብሩ ማገዝ ፥ የንባብ አማራጮችን በማስፋት መፍቀርያነ መጻሕፍት እንዲኾኑ መርዳት ስለሚኖርብን “የመጻሕፍት ስብስቡ” አስፈልጓል!! 📚የማያስቆጭ ፥ ሰጪውንም እንደ ዕድለኛ የሚያስቆጠር ስጦታ ቢኖር “የመጻሕፍት ስጦታ” ነው ፤ ይኽ ደግሞ ጉባኤ ቤት ላይ ሲኾን ፥ ለቤተክርስቲያን ትልቅ ውለታን መዋል ነው!! በተጨማሪም ምእመናን አገልጋዮች ላይ ያላቸውን ቅሬታ ከማሰማት የበለጠ ፥ በመሠራት ላይ ባሉ አገልጋዮች የድርሻቸውን መወጣት ቢችሉ ፥ ወደፊት የሚመኟቸውን ዓይነት አገልጋዮች ማየት ይችላሉ!! ስለኹሉም ነገር እግዚአብሔር ይርዳን!! 📚ምእመናን፦ “መጻሕፍትን ለመጻሕፍት ተማሪዎች” ፥ በማገዝ #አገልጋያችኹን_ፍጠሩ!! በሥጦታውም እየተሳተፋችኹ ያላችኹ ፥ “የሥጦታችኹ ብድራቶች በመድኃኔዓለም ዓይኖች ሥር ይጠ’በ’ቁ’ላችኹ” ዘንድ ምኞታችን ነው📚 +ጸልዩ ለነ..!