The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Открыть в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Больше3 291
Подписчики
+224 часа
+127 дней
+10030 день
Архив постов
የክረምት የወጣቶች የትምህርት፣ ስልጠና እና ምክክር ጊዜ በአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ ሻኪሶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
* * * * * * * * *
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ፣ አዶላ ገናሌ ሲኖዶስ፣ በኦዶ ሻኪሶ ሰበካ አዘጋጅነት የሁለተኛ ዙር የክረምት የወጣቶች የትምህርት፤ ስልጠና እና ምክክር ጊዜ በሻኪሶ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ከሁሉም የሰበካው ማኀበራነ ምዕመናን እና በአቅራቢያው ካሉ ሰበካዎች የመጡ ወጣቶች በሻኪሶ ከተማ ተገኝተው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለንተናዊ የአገልግሎት ፖኬጅ ማዕቀፍ መሰረት ስልጠናቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ።
ስልጠናውን ባሳለፍነው ሰኞ በኦፊሴል የከፈቱት የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ለወጣቶቹ ሰፊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የመልዕክታቸውንም መነሻ በኤፌ 1፥9-11 በማድረግ ወጣቶች የሚሻለውን ፈትነው ማወቅ እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ያለንበትም ዘመን ብዙ ምርጫዎች ያሉበት ዘመን መሆኑን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ በዙሪያችን ያሉ የሚያታልሉ ነገሮች ጥቂት እውነት ያለባቸው የሚመስሉ ነገር ግን ሀሰቶች ናቸው፤ እኛ ግን የሚያስፈልገን ሙሉ እውነት ነው ብለዋል።
ለወጣቶቹም ባስተላለፉት መልዕክት የመምረጥ አቅም የሚመጣው ከእግዚአብሔር ቃል እና እንደ ቤተ ክርስቲያን የራሳችን የሆኑ ትምህቶች፣ ልምምዶችና የእምነት መግለጫዎቻችንን በአግባቡ በማወቅ ነው ብለዋል።
በመክፈቻ መርሃግብሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌልና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል ለወጣቶች የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል። በአገልግሎት ዘመናቸውም ወርቃማ ጊዜ አድርገው የሚቆጥሩት ከወጣቶች ጋር በአገልግሎት ያሳለፏቸውን ዓመታት መሆኑ ገልጸዋል።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የሲኖዶሱ መሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ለወጣቶቹ መልዕክት አስተላልፈዋል: ምክርም ለግሰዋል።
ስልጠናው በቤተክርስቲያኒቱ ሁለንተናዊ የወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ መሰረት 'በሁለንተናዊ መልኩ ማደግ' በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሲሆን: የቤተክርስቲያኒቱ ተባባሪ ጠቅላይ ጸሐፊ በሆኑት ቄስ ፈቃዱ ቤኛ እና የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር በሆኑት ወንድማገኝ ኡዴሣ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ለወጣቶቹ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ።
ስልጠናው ለአንድ ሳምንት ያክል በሻኪሶ ከተማ እየተካሄደ ሲሆን ከ1,200 በላይ ወጣቶች እየተካፈሉት ይገኛል።
- - - - - - - - -
Leenjiin Gannaa Dargaggootaa Sinoodoosii Adoolaa Gannaalee, Magaalaa Shaakkisootti kennamaa jira.
* * * * * * * * *
Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaa, Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti, Sabakaa Oddoo Shaakkisootiin kan qophaa'e leenjiin gannaa dargaggootaa magaalaa Shaakkisootti adeemsifamaa jira.
Leenjichi marsaa 2ffaadhaaf adeemsifamaa kan jiru yoo ta'u, waldaa amantootaa sabakaa Oddoo Shaakkisoorraa, akkasumas sabakoota ollaa irraa dargaggootni argamuun, akkaataa Paakeejii Hundagaleessaa Dargaggootiin leenjii fudhachaa jiru.
Leenjicha Wiixata darbe ofiiseelaan kan banan Pirezidaantiin WKWWMYI Lubni Dr. Yoonaas Yiggazuu dargaggootaaf ergaa dabarsaniiru. Ka'umsa ergaa isaanii Efesoon 1:9-11 godhachuudhaan, dargaggootni isa caalu qoratanii hubachuun akka irraa eegamu dubbataniiru.
Barri keessa jirru kun bara filannoo baay'ee qabu ta'uu kan kaasan pirezidaantichi, wantoota dargaggoota dogongorsiisan dhugaa muraasa kan qaban, garuummoo soba kan ta'an ta'uu hubachuun dargaggootni dhugaa guutuu irratti akka xiyyeeffatan hubachiisaniiru.
Ergaa dargaggootaaf dabarsaniin, dandeettiin waa filachuu dargaggootaaf kan dhufu Sagalee Waaqayyoo fi bu'uura barsiisa Waldaa Kiristaanaa sirriitti hubachuudhaan akka ta'e ergaa dabarsaniiru.
Sagantaa baniinsaa kana irratti, Daarektara Qajeelcha Wangeelaa fi Ti'ooloojii kan ta'an Lubni Dr. Lalisaa Daani'eel dargaggootaaf Sagalee Waaqayyoorraa barumsa kennaniiru. Bara tajaajila isaaniitti yeroo addaa jedhanii kan fudhatan yeroo dargaggoota waliin dabarsan ta'uus ibsaniiru.
Baniinsa sagantichaa irratti geggeessitoota sinoodoosii dabalatee keessummootni affeeraman dargaggootaaf ergaa dabarsaniiru, gorsas kennaniiru.
Leenjichi paakeejii hundagaleessa tajaajilaa dargaggootaa waldattii ka'umsa tolfachuudhaan mata duree 'Guddinna Hundagaleessa Dargaggootaaf' jedhuun kan qophaa'e yoo ta'u, Itti Aanaa Muummicha Barreessaa WKWWMYI kan ta'an Luba Feqaaduu Beenyaa fi Daarektara Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa kan ta'an Wondmagegn Uddeessaatiin mata dureewwan garagaraa irratti leenjiin dargaggootaaf kennamaa jira.
Leenjichi torbaan tokkoof magaalaa Shaakkisootti adeemsifamaa kan jiru yoo ta'u, dargaggootni 1,200 hirmaachaa jiru.
#EECMY #AdolaGenaleSynod #YouthSummerCamp #Shakiso #Guji
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ 7ተኛ መደበኛ ጉባኤ ለቀጣይ አራት ዓመታት ሲኖዶሱን የሚመሩ መሪዎችን በመምረጥ በስኬት ተጠናቋል።
በዚህም መሠረት፥
1. ቄስ ጋምቤላ ሉአል ፕሬዚዳንት
2. ቄስ ሞሰስ ኦዝ ምክትል ፕሬዚዳንትና
3. አቶ ጴጥሮስ ቾርኮል አቃቤ እንዋይ በመሆን ተመርጠዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የተመረጠቱትን አዳዲስ የሲኖዶሱ መሪዎች ቃለ መሃላ አስገብተዋል። የአገልግሎት ጊዜውን የጨረሰውን አመራር በማመስገን በቅርብ ሆኖ አዲሱን የአመራር ቡድን እንዲግፍ አሳስበዋል።
ጉባኤውንም የምስራቅ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ ኚግዎ ኦሞድና የሲኖዶሱ አመራሮች፣ በጋምቤላ የአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው አንግዶች ተገኝተው ተካፍለዋል።
A Jithɛth cɛ jɛ lar ɛ thuɔ̱k bä lätdɛ lät a thil pek...!
የ7ኛው የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ጉባኤ ማጠቃለያ የህብረት ዝማሬ በኑኤር ቋንቋ።
"ኦ ኢየሱስ ፈቃድህን ልፈጽም ቃል ገብቻለሁ..."
The 7th West Gambela Betel Synod Convention closing song in Nuer Language.
"Oh, Jesus, I have promised to do your wills..."
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ 7ተኛውን የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ጉባኤን ለመካፈል ጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ገብተዋል።
የጋምቤላ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የሲኖዶሱ ኘሬዚዳንት ቄስ ጀምስ ጋዴት፣ የሲኖዶሱ ማኔጅመንት፣ ምዕመናንና የመንግሥት ተወካዮች ተቀብለዋቸዋል።
ከእርሳቸውም ጋር የቤተ ክርስቲያኒቱ የቤቴል ሲኖዶሶች ህብረት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪ ቄስ ዶ/ር ተፈሪ በርኬሳ በጋምቤላ የተገኙ ሲሆን መሪዎቹም ከምዕመናንም ጋር በጋራ የጌታን ዕራት ተካፍለው ለምዕመናን ሰላምታ አቅርበዋል።
ሐምሌ 23 ቀን 2017
ጋምቤላ
የቤተ ክርስቲያን አንድነት ሥነ-መለኮት (The Theology of Church Unity) በሚል ርዕስ ሥልጠና በአዶላ ከተማ ተሰጠ
* * * * * *
በአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ ከበርካታ ሰበኮችና ማኀበራነ ምዕመናን ለተወጣጡ ቁጥራቸው ከ1,300 በላይ ለሚሆኑ ወንጌላዊያን፣ ቄሶችና የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ሥልጠናው ተሰጥቷል። አንድ ሙሉ ቀን የወሰደውን ይህንን ሥልጠና የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌልና ቲኦሎጂ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል ሰጥተውታል።
በሲኖዶሱም ባሳለፍነው ዕሁድ የቅስና ሃላፊነት ለተቀበሉት አገልጋዮች የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶለሳ ባሳለፍነው ሳምንት የቅድመ ቅስና ስልጠና ለእጩ ቀሳውስቱና ለትዳር አጋሮቻቸው ሰጥተዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በሁለቱም ሥልጠናዎች ላይ ተገኝተው ለአገልጋዮቹ ጠቃሚ መልዕቶችን አስተላልፈዋል።
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
