5killo Jem'a official Channel
Открыть в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Больше1 159
Подписчики
-124 часа
Нет данных7 дней
-130 дней
Архив постов
𝐷𝑈𝐵𝐵𝐴𝑇𝑇𝑂𝑂𝑇𝐴 𝐴𝐹𝐴𝐴𝑁 𝑂𝑅𝑂𝑀𝑂𝑂 𝐻𝑈𝑁𝐷𝐴𝐴𝐹🎉🎊
𝑆𝑎𝑔𝑎𝑛𝑡𝑎𝑎 '𝑜𝑛𝑙𝑖𝑛𝑒' 𝑑𝑖𝑖𝑛𝑖𝑖 𝑘𝑒𝑒𝑠𝑠𝑎𝑛 𝑖𝑡𝑡𝑖𝑖𝑛 𝑏𝑎𝑟𝑎𝑡𝑡𝑎𝑛 𝑏𝑖𝑓𝑎 '𝑐𝑜𝑢𝑟𝑠𝑒'𝑡𝑖𝑖𝑛 𝑖𝑠𝑖𝑛𝑖𝑖𝑓 𝑞𝑜𝑝ℎ𝑒𝑒𝑠𝑠𝑢𝑢 𝑘𝑒𝑒𝑛𝑦𝑎 𝑦𝑜𝑜 𝑖𝑏𝑠𝑖𝑛𝑢 𝑔𝑎𝑚𝑚𝑎𝑐ℎ𝑢𝑢 𝑔𝑢𝑑𝑑𝑎𝑎𝑑ℎ𝑎𝑎𝑛𝑖✨🎇
𝐵𝑎𝑟𝑛𝑜𝑜𝑡𝑖𝑐ℎ𝑖 𝑡𝑜𝑟𝑏𝑖𝑖 𝑘𝑒𝑒𝑠𝑠𝑎𝑡𝑡𝑖 𝑔𝑢𝑦𝑦𝑜𝑜𝑡𝑎 𝑙𝑎𝑚𝑎 𝑞𝑜𝑓𝑎, 𝑘𝑎𝑛 𝑘𝑒𝑛𝑛𝑎𝑚𝑢 𝑦𝑜𝑜 𝑡𝑎'𝑢, 𝑔𝑢𝑦𝑦𝑎𝑎 𝑗𝑢𝑚𝑢'𝑎𝑎 𝑓𝑖 𝑠𝑎𝑛𝑏𝑎𝑡𝑎 𝑥𝑖𝑞𝑞𝑎𝑎 𝑠𝑎'𝑎𝑎𝑡𝑖𝑖 𝑏𝑜𝑞𝑜𝑛𝑛𝑎𝑎 𝑘𝑒𝑒𝑠𝑠𝑎𝑛𝑖𝑖𝑡𝑖𝑖𝑛 𝑏𝑎𝑘𝑘𝑢𝑚𝑎 𝑗𝑖𝑟𝑡𝑎𝑛 𝑡𝑒𝑒𝑠𝑠𝑎𝑛𝑖𝑖 ℎ𝑜𝑟𝑑𝑜𝑓𝑢𝑢 𝑑𝑎𝑛𝑑𝑒𝑒𝑠𝑠𝑢.
💫𝐵𝑎𝑟𝑛𝑜𝑜𝑡𝑎 '𝑂𝑛𝑙𝑖𝑛𝑒' 𝐽𝑎𝑚𝑎'𝑎𝑎 6-𝑘𝑖𝑙𝑜✨✨
📚 𝐾𝑖𝑡𝑎𝑎𝑏𝑎: 𝑘ℎ𝑢𝑧-𝑎𝑞𝑖𝑖𝑑𝑎𝑡𝑎𝑘
✍️ 𝐵𝑎𝑟𝑟𝑒𝑒𝑠𝑠𝑎𝑎: 𝑀𝑢ℎ𝑎𝑚𝑚𝑎𝑑 𝐽𝑎𝑚𝑖𝑖𝑙 𝑧𝑎𝑦𝑛𝑢𝑢
👤 𝐵𝑎𝑟𝑠𝑖𝑖𝑠𝑎𝑎: 𝑈𝑠𝑡𝑎𝑎𝑧 𝐴𝑏𝑑𝑢𝑙𝑒𝑥𝑖𝑖𝑓 𝑋𝑎𝑎ℎ𝑎𝑎
💻𝐼𝑑𝑑𝑜𝑜: 𝑂𝑛𝑙𝑖𝑛𝑒'𝑑ℎ𝑎𝑎𝑛 𝑇𝑒𝑙𝑒𝑔𝑟𝑎𝑚𝑎
🗓 𝐺𝑢𝑦𝑦𝑎𝑎: 𝐽𝑢𝑚𝑢'𝑎𝑎 𝑓𝑖 𝑠𝑎𝑛𝑏𝑎𝑡𝑎 𝑥𝑖𝑞𝑞𝑎𝑎
⏰ 𝑆𝑎'𝑎𝑎𝑡𝑖𝑖: 𝐼𝑠ℎ𝑎𝑎'𝑖𝑖 𝑏𝑜𝑜𝑑𝑎 2:40 – 3:40 𝐿𝑇
♻️ 𝑁𝑎𝑚𝑛𝑖 𝑓𝑒𝑑ℎ𝑖𝑖 𝑞𝑎𝑏𝑢 ℎ𝑢𝑛𝑑𝑖 ℎ𝑎𝑎𝑙-𝑑𝑢𝑟𝑒𝑒 𝑡𝑜𝑘𝑘𝑜 𝑚𝑎𝑙𝑒𝑒 ℎ𝑜𝑟𝑑𝑜𝑓𝑢𝑢 𝑛𝑖 𝑑𝑎𝑛𝑑𝑎'𝑎
♻️𝑇𝑜𝑟𝑏𝑖𝑖 𝑡𝑜𝑟𝑏𝑖𝑖𝑑ℎ𝑎𝑎𝑛 𝑏𝑎𝑑ℎ𝑎𝑎𝑓𝑛𝑖 𝑏𝑎𝑟𝑎𝑡𝑡𝑜𝑜𝑡𝑎 ℎ𝑖𝑟𝑚𝑎𝑎𝑛𝑛𝑎𝑎 𝑔𝑎𝑎𝑟𝑖𝑖 𝑞𝑎𝑏𝑎𝑛𝑖𝑖𝑓 𝑛𝑖 𝑙𝑎𝑎𝑡𝑎𝑚𝑎.
♻️ 𝐺𝑢𝑦𝑦𝑎𝑎 𝑏𝑎𝑟𝑛𝑜𝑜𝑡𝑖𝑐ℎ𝑖 𝑖𝑡𝑡𝑖 𝑒𝑒𝑔𝑎𝑙𝑢 ℎ𝑎𝑛𝑔𝑎 𝑏𝑒𝑒𝑘𝑠𝑖𝑓𝑛𝑢𝑡𝑡𝑖, 𝑖𝑠𝑖𝑛𝑖𝑠 𝑔𝑎𝑙𝑚𝑎𝑎𝑦𝑎𝑎, 𝑛𝑎𝑚𝑜𝑜𝑡𝑎 ℎ𝑖𝑛 𝑑ℎ𝑎𝑔𝑎ℎ𝑖𝑛𝑖𝑖𝑓𝑖𝑠 𝑑ℎ𝑎𝑔𝑒𝑒𝑠𝑠𝑖𝑠𝑎𝑎!
📝𝐺𝑎𝑙𝑚𝑎𝑎'𝑢𝑢𝑑ℎ𝑎𝑎𝑓 𝑙𝑖𝑖𝑛𝑘𝑖𝑖 𝑎𝑠𝑖𝑖 𝑔𝑎𝑑𝑖𝑖 𝑓𝑎𝑦𝑦𝑎𝑑𝑎𝑚𝑎𝑎!👇
https://forms.gle/WwaUzQFgpe7DkwNz8
𝐶𝐴𝑅𝑅𝐴𝐴𝑁 𝐾𝑈𝑁 𝐴𝐾𝐾𝐴 𝐼𝑆𝐼𝑁 𝐻𝐼𝑁 𝐷𝐴𝐵𝐴𝑅𝑅𝐸!!
𝐴𝐴𝑈-𝑀𝑆𝑈 6-𝑘𝑖𝑙𝑜 𝐽𝑒𝑚𝑒𝑎!
ℎ𝑡𝑡𝑝𝑠://𝑡.𝑚𝑒/𝐴𝐴𝑈6𝑘𝑖𝑙𝑜𝑗𝑒𝑚𝑒𝑎
ልዩ የእህቶች የቅዳሜ ሙሐደራ ፕሮግራም 🥀
የዚህ ሴሚስተር የመጀመሪያ ደዕዋ ፕሮግራማችንን እነሆ በአላህ ፍቃድ መጪው ቅዳሜ ሚያዚያ 10 ቀን በተወዳጁ መስጂዳችን አል አቅሷ የምናካሒድ መሆኑ ይታወቃል:: ታዲያ እህቶችዬ በእለቱ በዲንም ሆነ በዱንያ እውቀታቸው የታወቁና ጥሩ ልምድ ያካበቱ ኡስታዛዎችን ጋብዘን እየተጨዋወትን ቁም ነገር የምንይዝበት ፕሮግራም ነው!!
✨ ምን ምን ርእሶች ይዳሰሳሉ?
■ Hijab፡ የላቀው ጌታችን ሴትን ልጅ ከኢስልምናዋ በኋላ በሂጃብ ያከበራትን ያክል በምንም ነገር አላከበራትም። ሂጃብ ለሴት ልጅ ነጻነቷ፣ ማንነቷ፣ ክብሯ፣ የቁጥብነት መገለጫዋ ነው። ዓሊሞች "የሴት ልጅ ኢማን የሚጨምረው ሃያእዋ በጨመረው ልክ ነው፤ ሃያእዋ የሚጨምረው ደግሞ ራሷን በሰተረችበት ልክ (በሒጃብ) ነው" ይላሉ። እና አያጓጓም እህቶችዬ? ቅዳሜ ኢንሻአላህ ስለሂጃባችን ስለአለባበሳችን የምንተዋወስ ይሆናል።
■ Haram RelationShip፡
በማንኛውም ዘርፍ ላይ ያለ ወጣት ሊፈተንባቸው ከሚችላቸው ነገሮች ውስጥ ቀዳሚው ጾታዊ ፊትና ነው። እኛ ደግሞ ወጣት ከመሆናችንም አልፎ የግቢ ተማሪዎች መሆናችን (ከቤተሰብም የራቀን ስለሆንን) ለንደዚህ አይነት ሁኔታዎች ተጋላጭነታችን የበዛ ነው። ታድያ በስብስባችን የኡስታዛን ዳዕዋ፣ እናታዊ የሆነ ምክር፣ በዲን ጥላ የተሳሰሩ ሰዎችን ነሲሃ የምንሰጣጥ ይሆናል ኢንሻአላህ!!
■ Personal Experience Sharing: እንደአጠቃላይ ተጋባዥ እንግዶቻችን ከግቢ ቆይታቸው፣ ከግቢ ውጪም ባለው፣ ከትዳር ህይወታቸው ተንተርሰው ለኛ ጠቃሚ የሚሉትን ምክሮቻቸውን ያካፍሉናል።
ውዷ እህቴ ለዚህ የተከበረ ስብስብ ተጋብዘሻልና እንዳያመልጥሽ እያልን ለሁሉም ግቢ እህቶች ክፍት የሆነን ጥሪ ለማቅረብ እንወዳለን 😊!
☕️ የሻይ ቡና ጊዜም ይኖረናል ኢንሻአላህ
⏳ ቅዳሜ ሚያዝያ 10፤ከጠዋቱ 3፡00 ላይ
📍 አል አቅሷ መስጂድ
©የ6 ኪሎ ጀምዓ ዳእዋና ቂርዓት ሴክተር
📚 KITAB REMINDER – LAMIYYAH
📍 Those who have not yet received the Lamiyyah kitab can take it today at 4 Kilo Mosque (available for both brothers and sisters).
💻 Online participants can follow using the softcopy PDF.
⎙ Kitab PDF soft copy 👇🏻
https://t.me/qirat_channel_5k/181
🤝 Make sure to come prepared and benefit fully from the dars.
🌙 DAY 3 REMINDER – COURSE EXTENDED
As-salamu ‘alaykum dear students,
Alhamdulillah, the sessions have been very beneficial so far, and due to the importance of the remaining content, the course has been extended by one more day.
📢 Today is Day 3, and the dars will continue:
⏰ Time: 11:00 - 12:30 LT
📍 Venue: 4 Kilo Mosque
💻 Online: via 5 Kilo Qira’ah Channel
⚠️ Make sure to be on time and continue benefiting from the remaining sessions.
🤝 Stay consistent and make the most of these final days, in sha’ Allah.
❇️በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋት የማውረድ ጥቅሞች፦
🔵የምስራች ምክንያት መሆኗ፦ አንድ ባሪያ ከመሞቱ በፊት በጀነት እንዲበሰር ሰበብ ትሆናለች።
🔵ለጭንቀት መወገጃ መሆኗ፦ አላህ ለባሪያው የሚያስጨንቀውን ነገር ሁሉ እንዲበቃው (እንዲያስወግድለት) ሰበብ ትሆናለች።
🔵ፍላጎቶች እንዲሟሉ ማድረጓ፦ ጉዳዮችና ፍላጎቶች እንዲፈጸሙ ሰበብ ትሆናለች።
🔵የተረሳን ነገር ለማስታወስ መርዳቷ፦ አንድ ባሪያ የረሳውን ነገር እንዲያስታውስ ሰበብ ትሆናለች።
🔵በረካን ማስገኘቷ፦ በሶለዋት አውራጁ አካል፣ በሥራውና በዕድሜው ላይ በረካ እንዲወርድ ሰበብ ትሆናለች።
📚 ምንጭ: ኢብኑ አል-ቀዪም | ጀላእ አል-አፍሃም ገጽ (522-523)
©
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉
إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﷺ
🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
"ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።"
ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው።
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ-ለዲን ሲሉ እየታገሉ ላሉም እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!!
በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️
اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
+1
"በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ብቻ ሳይሆን ክብራቸውንም የሚነካ ድርጊት ስለሆነ በቶሎ እንዲቆም እንጠይቃለን።" - የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ
እየደረሰ ስላለው በደል ያወጣው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ጥያቄው የጥቂቶች ነው ላሉት አድርሱላቸው።ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ጥያቄ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እንፈልጋለን ! ! !
©aaumsu
"ዩኒቨርሲቲው ጥቂት ስለሆኑ መመሪያውን አላሻሽልም ብሏል። የፌደራል መጅሊስን ሄደን ስንጠይቅ ደግሞ ኒቃብ ሱና ስለሆነ ተውት ብሎናል። እንደተባለውም እናንተ ጥቂቶች ናችሁና ዘገባ ልንሰራላችሁ አንችልም።" - ፋና
ሙስሊም ተማሪዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየፈፀመባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ዘገባ ይሰራ ዘንድ ወደ ፋና ባመሩበት ወቅት ከተቋሙ የምርመራ ዘገባ ክፍል ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ጌታሁን ዳዲ ጋር ተወያይተው ነበር። በውይይቱ ወቅት የሚመለከታቸውን ሁሉ አናግረው ፍትሕ እስኪመጣ ድረስ ከጎናቸው በመቆም ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡም አፅንዖት በመስጠት ገልፀው ነበር።
ሆኖም ግን ውጤት ለመጠየቅ ዳግም ሲሄዱ የሙያ ስነ-ምግባርን ባልተላበሰ እና ከፍትሕ ፅንሰ ሀሳብ በራቀ መልኩ ምላሽ ሰጥተዋል። በምላሻቸው የፌደራል መጅሊስ ሄደው ሲጠይቁ ኒቃብ ለትርፍ ፅድቅ የሚሰራ እንደሆነ እንደገለፁላቸው፤ ዩኒቨርስቲውም ይህንን እየጠየቁ ያሉት ተማሪዎች ጥቂቶች ስለሆነ መመሪያውን ሊያሻሽል እንደማይችል እንደገለፀላቸው፤ እርሳቸውም ጠያቂዎቹ ጥቂት ስለሆኑና ከመጅሊስ እና ከዩኒቨርስቲው የተሰጣቸው መልስ አመርቂ ስለሆነ ዘገባውን ሊሰሩ እንደማይችሉ ገልፀዋል።
ጥያቄው ዩኒቨርስቲውን የገነባው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል። መጅሊስ ያነሳነውን የመብት ጥያቄ ሱና ነውና ተውት ብሎ ከሆነም ይፋዊ ማብራሪያ እንዲሰጠን እንፈልጋለን። የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ ጥቂቶች ስለሆናችሁ አንዘግብም ስላለው ጋዜጠኛ ጌታሁን ዳዲ ሚዲያው አቋሙ ምን እንደሆነ ይፋ ሊያደርግ ግድ ነው።
ጥያቄያችን ፍትሕ ተነፍጎ እየደረሰብን ያለው በደል ይቆም ዘንድ የወጣው ጨቋኝ መመሪያ ይቁም ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው።
መልስ እንፈልጋለን!
©aaumsu
@fivekjemaa
🌙 DAY 2 REMINDER – 3-DAY SHORT COURSE
As-salamu ‘alaykum dear students,
Alhamdulillah, yesterday’s session was truly beneficial and engaging, with both in-person and online participants taking part. It was a great start!
📢 Today is Day 2 — and you still have a valuable opportunity to join and benefit.
📚 Kitab: Lamiyyah
👤 Instructor: Ustadh Zenjebil
📍 Venue: 4 Kilo Mosque
💻 Online: via 5 Kilo Qira’ah Channel
⏰ Time: 11:00 – 12:30 LT
⚠️ Try your best to be on time and not miss out on these remaining sessions.
⎙ kitab PDF soft copy 👇🏻
https://t.me/qirat_channel_5k/181
🤝 Don’t let this opportunity pass come, benefit, and be part of the gathering of knowledge.
@fivekjemaa
ቢላል ኢብኑ ሰዕድ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፦
ወንጀል ስትሰራ የወንጀሉን ትንሽነት ሳይሆን ያመፅከውን ጌታ ትልቅነት ተመልከት!!
ሲየሩ አእላመ-ኑበላእ (5:91)
ዶክተር ሽብሩ ተመስገን (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ዲን) ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄያቸውን ለማቅረብ ይምጡ ማለታቸውን ተከትሎ ቅሬታቸውን ለማቅረብ የሄዱ ተማሪዎች እሳቸው ስለሌሉ ተመለሱ ተባሉ ! ! !
------------------------------------------
ሚያዚያ 07 / 2018 ዓ.ል
------------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎቹን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያን ካወጣበት 2017 ዓ.ል ጥቅምት ወር ጀምሮ ተማሪዎች ለተለያየ የመብት ጥሰት ተጋላጭ ስለሆኑ የመብት ጥሰቱ ቆሞ መብታቸውን የሚያከብር መመሪያ ይወጣ ዘንድ ሲጠይቁ እንደነበር ይታወቃል። ለ19 ወራት ያክል ባደረጉት እንቅስቃሴ ውስጥም የተማሪዎች ሕብረት ከአቅሜ በላይ ነው ስላለ ከተማሪዎች ዲን ጀምሮ እስከ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ድረስ ተደጋጋሚ ውይይቶችን እያደረጉ፤ ደብዳቤዎችን እያስገቡ፤ የሚመለከታቸውን አካላት ሁሉ እየጠየቁ ዘልቀዋል።
ሆኖም ግን መፍትሔ መስጠት ያልፈለጉት የዩኒቨርስቲው አመራሮች ተማሪዎቹን አናውቃችሁም በማለት ያስገቡት ደብዳቤ ላይ ጭምር ስርዝ ድልዝ አድርገው እየመለሱ፤ ውይይት አናደርግም እያሉም እየተናገሩ ዘልቀዋል። በዚህ መሐል ስለጉዳዩ ማብራሪያ የተጠየቁት የተማሪዎች ዲን ዶክተር ሽብሩ ተመስገን "እኛ ጀመዓ አናውቅም። ተማሪዎች ጥያቄ ካላቸው በተናጠል መጥተው ይጠይቁ።" - ማለታቸውን ተከትሎ ተማሪዎች ለመጠየቅ የሄዱ ቢሆንም "እርሳቸው ዛሬ ቢሮ አልገቡም። ነገ ኑ!" - ተብለው ተመልሰዋል።
ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ አቅርበው መፍትሔን በውይይት ለመሻት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም ዩኒቨርስቲው እየመለሰበት ያለው መንገድ ግን ትክክለኛ ያልሆነ ነው። ተማሪው እየጠየቀ ያለው የተጣሱት መብቶቹ ይከበሩ ዘንድ ነው። ተማሪን በመናቅ ጥያቄዎችን ችላ ብሎ በማድበስበስ ለማለፍ እየተደረገ ያለው አካሄድ ሊስተካከል ይገባል። ጥያቄያችንን ላለፉት 19 ወራት በሁሉም መንገድ አቅርበናል። ከዶክተር ሳሙኤል ጀምሮ ዶክተር ሽብሩንም ጨምሮ ጥያቄዎቻችንን አቅርበን በተገኙበት ውይይት ላይ መፍትሔ የማይሆኑ ምላሾች ተሰጥተው ነበር። አሁን እየተከሄደ ያለው አካሄድ ደግሞ የውይይትንም በር የዘጋ ነው።
ነገሮች መስመር ይዘው መፍትሔ በቶሎ ይመጣ ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲረባረቡ ዳግም ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
ألسلام عليكم ورحمة الله وبركاته✨✨
ምን ያህል ስለ እምነታችን መሰረታዊ ነገሮች እናውቃለን ፣ ምን ያህል አቂዳችን ላይ እምነት አለን
ያለንበትን መለስ ብለን ምንገመግምበት ፣ የጠፋንን ማስታወሻ ፣ ያላወቅነውን ማወቂያ መድረክ አዘጋጅተን ተጋበዙልን እያልናቹ ነው
ወጣቱ ኡስታዛችን ዘንጀቢል ስለ እምነታችን ሊነግረን 4ኪሎ መስጅድ ይጠብቀናል ፣ ታድያ መቅረት አይቻልም ፣ የራቅን እንደሆነ 5 kilo Qirat Channel ላይ live ስለሚተላለፍ እዛ ላይ እንኳ ቢሆን ከመከታተል ወደኋላ አንበል።
📚ኪታብ ፡ ላሚያ በ ኢብን ተይሚያ (لامية)
👤አስተማሪ ፡ ዘንጀቢል
🗓ቀን ፡ እሮብ (ዛሬ) - አርብ ( 3 ቀን )
⏰ሰዓት ፡ 11:00 - 12:30 (ከአስር እስከ መግሪብ)
📍ቦታ ፡ 4ኪሎ መስጅድ እና Online 5 kilo Qirat Channel
አስተውሉ ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል ፣ ዲን ላይ አውቄዋለው ጨርሻለው ሚባል ነገር የለም ፣ ኢማናችንን ለመጠበቅ ግዴታ ሁሌ መተዋወስ አለብን።
⚠️ ስለዚህ ከሚቀሩት አንሁን !
✍️ በዚህ እንመዝገብ: https://forms.gle/58hpV6yW6n2sdzZV6
Repost from AAU - Muslim Students Union
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ተከትሎ ሚንበር ቲቪ ያዘጋጀው ዘገባ ነው። በዘገባው፦
፨ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ፦ ዩኒቨርስቲው ያወጣው የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥሰው እና በተግባርም ለሙስሊም ተማሪዎች ከእምነታቸው እና ትምህርታቸው ይመርጡ ዘንድ የሚያስገድደውን መመሪያ ሕገ-መንግስታዊ ነው እንዳሉ ተገልጿል።
፨ የዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ዲን ዶክተር ሽብሩ ተመስገን፦ ተማሪዎች ፍትሕን ፍለጋ ለ19 ወራት በየቢሮው ያደረጉትን እንቅስቃሴ እንዳልነበር ቆጥረው የመብት ጥሰት ካለ በተናጠል ይምጡ፤ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል አናውቅም ብለዋል።
፨ በፌደራል መጅሊስ የማህበራዊ እና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት፦ ለሚዲያው ተገቢውን ምላሽ መስጠት ባለመቻላቸው በዘገባው ውስጥ ማካተት እንዳልተቻለ ተገልጿል።
፦ ሙሉ ዘገባው https://youtu.be/JgTDcltz1NU?si=ETM-ZAdmAGguR3pe ላይ አለ። በዩቲዩብ ገብታችሁ አስተያየት ስጡ። ያልሰሙት ይሰሙም ዘንድ ቪድዮውን Share አድርጉ።
@aaumsu
"እኛ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል ነገር አናውቅም። ተማሪዎች ተሰባስበው ሳይሆን በተናጠል ሆነው ተማሪዎች ሕብረት ቢሮ በመምጣት የደረሰባቸውን በደል ያስረዱ።" - ዶክተር ሽብሩ ተመስገን (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ዲን) ለሚንበር ቲቪ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለውን በደል አስመልክቶ ሚንበር ቲቪ በሰራው ዘገባ ላይ ማብራሪያ ይሰጡ ዘንድ የተጠየቁት የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ዲን ሀላፊ ዶክተር ሽብሩ "እኛ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል አናውቅም። ተማሪዎች የደረሰባቸው በደል ካለ ተሰባስበው ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ወደ ተማሪዎች ሕብረት በመሄድ ያመልክቱ።" - የሚልን የተድበሰበሰ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ መልስ የተቋሙን አንጋፋነት፤ ታማኝነት የማይመጥን እንዲሁም ከተማሪዎች ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ምላሽ ነው።
መመሪያው ይሻሻል ዘንድ እና እየደረሰ ያለው በደል ለ18 ወራት ያክል ለተማሪዎች ሕብረት ሲቀርብለት እንደነበርና ሕብረቱም "ከአቅሜ በላይ ነው!" - በማለት ወደ ተማሪዎች ዲን መርቶ እርሳቸው ባሉበት ውይይት ከተደረገ ቡሃላ "ይህ ከእኔ አቅም በላይ ነው። ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ጋር ተመካክሬ ውጤቱን አሳውቃለሁ።" - የሚል ምላሽን በመስጠት በያዙት ቀጣይ ቀጠሮ ላይ ሳይገኙ ቀርተው ተማሪዎችን እንዳስቀየሙ የሚታወቅ ነው።
በደሉ የደረሰባቸው ሙስሊም ሴቶች እንደ ግል ስለሚመለከታቸው ደጋግመው ጠይቀዋል። በደሉ የተፈፀመው እንደ ወል በሙስሊሙ ላይ ስለሆነ እንደ ሙስሊም ጠይቀናል። በግልም በወልም ውይይት የጀመሩ ቢሆንም መፍትሔ ይሰጡ ዘንድ ጫና ሲደረግባቸው ጀመዓ የሚባልን ነገር አናውቅም ብለዋል። ሊስተካከል ይገባል።
በዘገባው እንደተጠቀሰውም በፌደራል መጅሊስ የማህበራዊ ጉዳይ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት አግባብነት የሌለው መልስ ስለሰጡ ቃላቸውን ማካተት አልተቻለም ብሏል። እንደ መጅሊስ በሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የተያዘው አቋም ግልፅ እንዲሆንና መፍትሔ ይመጣ ዘንድ አስቸኳይ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ጥሪያችን ነው።
©aaumsu
@fivekjemaa
💥 ደርስ ማስታወሻ :::::::::::::::::::::::
🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋
✅ ኢንሻአላህ ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል ::
📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ
⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ
🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ማክሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ። 6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል ቡዙ እናተርፍለን።
قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ﷺ:
"የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው"
ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ
ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/durus_at_aqsa
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934
@fivekjemaa
