5killo Jem'a official Channel
Открыть в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Больше1 162
Подписчики
Нет данных24 часа
+37 дней
+730 день
Архив постов
ለግፍ ያላጐነበሰው ንጉሥ 👑
ክፍል 2
ቅንነት ካለ፣
ሰብአዊነት ካለ ፣
ሰላም የሆነውን እምነታችንን እና ሙስሊሞችን ለመቀበል ልቦች በሮቻቸውን ይከፍታሉ።
ነጃሺም ያደረገው ይህንን ነው። ቅን ነበር፣ለቅኖችም ልቡን ክፍት አደረገ፣አላህም በሂደት የሂዳያን መንገድ አገራለት።
የነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦች በሀበሻ የገጠማቸውን እንዲህ ሲሉ መስክረዋል:-
“ሀበሻ ገባን። መልካም ጎረቤቶችንም አገኘን። በሃይማኖታችን ምክንያት የሚደረግብን ተጽእኖ አልነበረም። አላህን በሰላም መገዛት ጀመርን። አንድም ችግርና መከራ አላጋጠመንም። የምንጠላውን ነገር አልሰማንም።”
ይህ ሰላም ፣ ሰላም የነሳቸው ቁረይሾች ሀበሻን ቀደም ሲል በንግድ የሚያውቋትን ሁለት ግለሰቦች ያቀፈ ልዑክ ለመላክ ወሰኑ::
ዐብደሏህ ቢን አቢ ረቢዓህ እና ዐምር ኢብኑል ዓስ ስጦታዎችን ይዘው ሐበሻ ደረሱ፡፡ በነጃሺ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደርም እርሱን ከማናገራቸው በፊት ለቀሳውስቱ ስጦታዎችን በማበርከት የመጡበትን ዓላማም አስረዷቸው::
ቀሳውስቱም ደገፏቸው:: ከነጃሺ ፊት በቀረቡ ጊዜም ዐምርኢብኑል ዓስ እንዲህ ሲል ተናገረ፡-
“ንጉሥ ሆይ! በአገርዎ የኛ ሕዝብ አካል የሆኑ ቂላቂል ልጆች ይገኛሉ:: የሕዝባቸውን ሃይማኖት ትተዋል:: ወደ እርስዎ ሃይማኖትም አልገቡም:: እኛም ሆንን እርስዎ የማናውቀውን አዲስና መጤ ሃይማኖት አምጥተዋል:: እኛም ከሕዝባቸው መሪዎችና ልዑላን እንዲሁም ከአባቶቻቸው፣ ከአጎቶቻቸውና ከቅርብ ዘመዶቻቸው ነው የተላክነው:: ወደነርሱ ይመልሷቸው ዘንድ እንሻለን:: እነርሱ (ሹማምንቱ) ከነርሱ የላቀ አመለካከት ያላቸው ናቸው:: በእነርሱ ላይ የፈጸሙትንም ነውር በሚገባ ያውቃሉ:: ለዚህም የሚገባቸውንም ቅጣት ይሰጧቸዋል::”
በስፍራው የነበሩት ቀሳውስትም፡-
“ንጉሥ ሆይ! እኝህ ሁለት ሰዎች የሚሉት እውነት ነው:: የራሳቸው ወገኖች ስለስደተኞቹ የሚያቀርቡት ነገር ይበልጥ ተቀባይነት አለው። በእነርሱ ላይ የፈጸሙትንም ነውር የሚያውቁት እነርሱ ናቸው። ስለዚህ አሳልፈው ይስጧቸውና ወደ ሀገራቸው ይመልሷቸው “
አሉ።
ንጉስ አስሃማ ግን ሁለቱንም ወገን ለመስማት ወሰኑ። ከሰሀቦችም መሪ የነበረው ጃዕፈር ኢብኑ አቡ ጧሊብ ከልብ የወጣ ልብ ይገባል እንዲሉ እንዲህ ሲል ተናገረ:-
“ንጉሥ ሆይ! የድንቁርና ሥርዓት ተከታይ ሕዝቦች ነበርን፡፡
ጣዖታትን እንገዛለን፤የበከተ እንበላለን፤ ዝሙት እንፈጽማለን፡፤ዝምድና እንቆርጣለን፡ በጎረቤቶቻችን ላይ እኩይ ተግባርን እንሠራለን::
ጠንካራው የደካማውን ገንዘብ ይበላል፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ላይ እያለን ነበር ….ዘሩን፣ እውነተኛነቱን፣ ታማኝነቱንና ጨዋነቱን የምናውቀው መልዕክተኛ አላህ የላከልን፡፡
ይህ ነብይ ወደ አላህ ጠራን፣አላህንም አንድ አድርገን እንድንገዛው፣ እኛም ሆንን አባቶቻችን ስንገዛ የነበረውን ድንጋይና ጣዖት እንድንተው አስተማረን፡፡
እውነት እንድንናገር፣ አደራ እንድንጠብቅ፣ ዝምድናን እንድንቀጥል፣ ለጎረቤቶቻቸን መልካም እንድንውል መከረን፤ እንዲሁም እርም ከሆኑ ነገሮችና ደም (ያለ አግባብ) ከማፍሰስ እንድንቆጠብ አዘዘን፡፡
(በተጨማሪም) ዝሙት ከመፈጸም፣ በሐሰት ከመመስከር፣ የየቲሞችን ገንዘብ ከመብላት፣ ጥብቅና ንጽሕት የሆኑ ሴቶችን ከማነወር እንድንቆጠብ አዘዘን፡፡
አላህን ብቻ እንድናመልክና በርሱ ላይ አንድም ነገር ላናጋራ፣ ሶላትንም ልንሰግድ፣ ዘካንም ልናወጣ፣ ጾምም ልንጾም አሳስበን፡፡
እውነት ብለን ተቀበልነው:: ከአላህ ይዞ በመጣው ነገር ተከተልነው፤ አላህን ብቻ መገዛት ጀመርን ፤ በርሱም ላይ ማጋራትን አቆምን::
አላህ ሐራም ያደረገውን ክልክል አደረግን፤ የፈቀደውን ነገርም መፈጸም ጀመርን::
በዚህ የተነሳ ነው ወገኖቻችን ጠላት አድርገው የያዙንና
ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶችን የፈጸሙብን:: መከራ ሲበዛብን፣ ከኃይማኖታችን ሊቀለብሱን ሲጫኑን ወደርስዎ አገር መጣን፡፡ ከሌሎች ንጉሶች እርስዎን መርጠን ጥገኝነት ጠየቅን፡፡ ከርስዎ ዘንድም እንደማንበደል እርግጠኞች ነን።”
ዐምር በዚህ ጊዜ ኢስላም ኢየሱስን በመጥፎ እንደሚያወሳ ለንጉሡ ተናገረ። በጃዕፈር ንግግር ልባቸው የተነካው ንጉሥ ከቁርኣን እንዲያሰማቸው ጠየቁ:: ጃዕፈርም ከቁርኣን የመርየምን ምዕራፍ አነበበላቸው፡፡
ንጉሡ እጅግ ጥልቅ በሆነ ስሜት ያደምጡ ነበር፡፡ እንባቸው ጺማቸውን እስኪያርስ ድረስ አለቀሱ
………ይቀጥላል
@aaumsu
የሙስሊም ተማሪዎችን የፍትሕ ጥያቄ አስመልክቶ የፋና ምላሽ ምን ነበር። https://vt.tiktok.com/ZSVWUFjV9/ ያዳምጡ። ሪፖስት በማድረግም ተደራሽነቱን ያስፉ።
@aaumsu
የሀገራዊ ምክክሩ ተቋቁሞ ወደ ስራ ሲገባ እንደ ሙስሊም በበቂ ሁኔታ አልተወከልንም ቅሬታችን ነበር። ያ አልፎ የአጀንዳ ማሰባሰቡ ሲጀመር ደግሞ አጀንዳዎቻችን በበቂ ሁኔታ አልተያዙምን በቅሬታ መልኩ አቅርበን ነበር። ያ ሁሉ ታልፎ ምክክሩ ከተቋጨ ሳምንት ሞላው።
እኛም 5 አመታትን ስለፈጀው የምክክር ኮሚሽኑ ሂደት እና ስለሚጠበቀው ውጤት ውይይት ልናደርግ ቀጠሮ ይዘናል። የሀገራዊ ምክክሩ አንደምታ 24 ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል። እንዲነሱ የምትፈልጓቸውን ጥያቄዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ @Niqab_issueBot ላኩልን። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድም በሁሉም መንገድ አሰራጩ። የስቶሪ እና ፕሮፋይል ቻለንጁንም ተቀላቀሉ።
ነገ እሁድ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ... በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ (@aaumsu) እንገናኝ።
@aaumsu
የሀገራዊ ምክክሩ አንደምታ ... በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ እንገናኝ !
የሀገራዊ ምክክሩ በዘርፈ ብዙ ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ምክክር አድርጎ ምክረ ሀሳቦችን ካጠናቀረ ቀናቶች አልፈዋል። ሕዝበ ሙስሊሙም አጀንዳዎቹን አቅርቦ የመድረኩ አካል እንዲሆኑ አድርጎ ነበር። ለመሆኑ ሀገራዊ ምክክር ምንድን ነው? በምክክር መድረኩ የሕዝበ ሙስሊሙ አጀንዳዎችስ ምን ምን ነበሩ? ምክክሩ ስኬታማ ይሆን ዘንድ መደረግ ያለባቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? ከሀገራዊ ምክክሩስ ልንወስዳቸው የሚገቡ ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?
እነዚህ እና ሌሎች ጥያቄዎች መልስ የሚያገኙበት ልዩ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ (@aaumsu) የሚዘጋጅ ይሆናል።
ቀን፦ እለተ እሁድ ነሐሴ 24 / 2018 ዓ.ል
ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
ቀጠሯችንን ቀጠሯችሁ አድርጉ። በሰዓቱ እንገኝ፤ ለሌሎችም እናሰራጭ።
@aaumsu
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በስኮላርሺፕ ለመግባት አስባችሁ ለUAT ፈተና ክፍያ፤ የትራንስፖርት ወጪ አቅማችሁ የማይችል ሙስሊም ተማሪዎች፦
ጀመዓችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዚህ ችግር ምክንያት ተማሪዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ከመቀላቀል ወደሗላ እንዳይሉና የሙስሊም ተማሪዎችን ተሳትፎ ለማበረታት በማሰብ የጥቂት ተማሪዎችን የUAT ክፍያ፤ የመመዝገቢያ ወጪ እና የትራንስፖርት ክፍያ ለመሸፈን አስቧል። ስለሆነም አቅሙ የሌላችሁና ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተማሪዎች https://forms.gle/Bap5GQQZMigtBKES6 አመልክቱ።
ለማመልከት ዛሬ የመጨረሻ ቀን ሲሆን በቅርቡም ወጭ የሚሸፈንላቸው ተማሪዎችን ይፋ የምናደርግ ይሆናል።
ማስታዎሻ፦ ወጪው የሚሸፈነው አቅሙ ለሌላቸው ተማሪዎች ብቻ ነው። የሚሸፈነውም ለጥቂት ተማሪዎች ብቻ ነው። አላህ ኡማውን የምትጠቅሙ ያድርጋችሁ።
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የኢንስታግራም ገፅን https://www.instagram.com/aaumuslimstudents?igsi=MWZyMHZjNW1paWo4Mg== ፤ የቲክቶክ ገፅን ደግሞ https://vt.tiktok.com/ZSVggku7N/ Follow አድርጉ። ለሌሎችም Share ያድርጉ።
@aaumsu
ከሒጃቡ ጀርባ !
በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVG8tMAY/ በመግባት አዳምጡት፤ ሪፖስትም አድርጉ።
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የኢንስታግራም ገፅን https://www.instagram.com/aaumuslimstudents?igsi=MWZyMHZjNW1paWo4Mg== ፤ የቲክቶክ ገፅን ደግሞ https://vt.tiktok.com/ZSVggku7N/ Follow አድርጉ። ለሌሎችም Share ያድርጉ።
@aaumsu
የቀድመው የጅግጂጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሳይኮሎጂ ዲፕርትመንት ሌክቸር ድጋፋችንን ይሻሉ !
ዶክተር አብዱናሲር አሕመድ በአንድ ወቅት ጂግጂጋ ዩኒቨርስቲን በፕሬዚዳንትነት ያገለገሉ አንጋፋ ምሁር ናቸው። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሳይኮሎጂ ዲፓርትመንት መምህር ሲሆን ባደረበት ፅኑ ሕመም ምክንያት በውጭ ሀገር እንዲታከም ስለተወሰነና ከሕክምና እና ከአንዳንድ ወጪዎች ጋር ተያይዞ የገንዘብ እጥረት ስላጋጠመው እርዳታ ይደረግለት ዘንድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርት እና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ጠይቋል።
ነብያችን ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንድ ሙስሊም ከሌላኛው ሙስሊም ልክ እንደ አንድ አካል ነው ብለዋልና የዶክተርን ችግር ችግራችን አድርገን እንተባበራቸው ዘንድ ጥሪያችን ነው። የአንድን ሙዕሚን ጭንቀት በዱንያ ላይ ያቃለለ አላህ ከአኼራ ጭንቀቱ ያቃልልለታልና በቻልነው አቅም ከዶክተር ጎን በመቆም ጭንቀታቸውን እናቃል። መልዕክቱን ለሌሎችም በማዳረስ በኸይር ስራው ላይ ተሳታፊ እንሁን።
የንግድ ባንክ አካውንት፦ 1000003646096 (Abdenasir Ahmed Ibrahim). የላካችሁበትን screenshot በማድረግ @Niqab_issueBot ላኩልን።
አላህ ሙሉ አፊያቸውን ይመልስ፤ የመጨረሻም ያድርገው።
@aaumsu
ፕሮግራማችን ባምረ ሁኔታ ተጠናቋል። ሁላችሁም ጥሩ መረጃዎችን እንዳገኛችሁበት ባለሙሉ ተስፋ ነን።
ከጥያቄዎች ብዛት አንጻርና ከመዘናጋትም ያልተመለሰ ጥያቄ ካለ፤ ከላይ በሪከርዱ ላይ ያልተዳሰሰ ጥያቄ ካላችሁ በማንኛውም ሰዓት በ @Aaumuslimstudentsunion1 አናግሩን!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!
@aaumsu
የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ አስመልክቶ የአአዩ ሰብዓዊ መብቶች ማዕከል ምላሽ ምን ነበር?
በ https://vt.tiktok.com/ZSVggku7N/ በመግባት አዳምጡ፤ ለሌሎችም አሰራጩ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ፕሮግራማችን ተጀምሯል። https://t.me/aaumsu?livestream=df89bd4b44cd79a9cc ተቀላቀሉ። ለሌሎችም share አድርጉ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን መቀላቀል ለምትፈልጉ በሙሉ!
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስገዝ መሆኑን ተከትሎ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከመግቢያ ፈተና እና ከአጠቃላይ የካምፓስ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ማወቅ የሚገቧችሁን ወሳኝ መረጃዎች የምንዳስስበት ልዩ መድረክ አዘጋጅቶላችኋል።
በዚህ ፕሮግራም ላይ ከሚነሱ ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የኢንትራንስ ውጤቴ ስንት መሆን አለበት?
- የዩኒቨርሲቲው የትምህርት እድሎች (Self-sponsored, Government-sponsored/Cost-sharing, Presidential Scholarship, Teaching Scholarship) ልዩነታቸው ምንድን ነው?
- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና (UAT) ምን ይመስላል? ምን ዓይነት ጥያቄዎችስ ይካተታሉ? ለመፈተን ምን ማሟላት ያስፈልገኛል?
- እንደ Medicine, Software Engineering እና Law ያሉ ከፍተኛ ውድድር የሚታይባቸውን ትምህርት ክፍሎች ለመቀላቀል ምን ያህል እድል አለኝ?
- ኒቃብ ለብሼ በነጻነት መማር እችላለሁን? ከትምህርቴስ እስተጓጎላለሁን?
- በካምፓስ ቆይታዬ የሃይማኖት ግዴታዎቼን (ሶላት፣ ጾም፣ ዒድ እና ሌሎች የዲን ተግባራትን) ለመፈጸም አመቺ ሁኔታዎች አሉ ወይ?
እነዚህን እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎቻችሁን ይዛችሁ በመምጣት በቂ ምላሽ እንድታገኙ ሁላችሁንም በክብር ጋብዘናል።
📅 ቀን፦ ነገ ሐሙስ
⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ፦ በህብረቱ የቴሌግራም ቻናል በቀጥታ ስርጭት (Live) 👉 [@aaumsu]
መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ ለምታውቋቸው ሁሉ ሼር በማድረግ ያካፍሉ!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በስኮላርሺፕ ለመግባት አስባችሁ ለUAT ፈተና ክፍያ፤ የትራንስፖርት ወጪ አቅማችሁ የማይችል ሙስሊም ተማሪዎች፦
ጀመዓችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዚህ ችግር ምክንያት ተማሪዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ከመቀላቀል ወደሗላ እንዳይሉና የሙስሊም ተማሪዎችን ተሳትፎ ለማበረታት በማሰብ የጥቂት ተማሪዎችን የUAT ክፍያ፤ የመመዝገቢያ ወጪ እና የትራንስፖርት ክፍያ ለመሸፈን አስቧል። ስለሆነም አቅሙ የሌላችሁና ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተማሪዎች https://forms.gle/Bap5GQQZMigtBKES6 አመልክቱ።
ማስታዎሻ፦ ወጪው የሚሸፈነው አቅሙ ለሌላቸው ተማሪዎች ብቻ ነው። የሚሸፈነውም ለጥቂት ተማሪዎች ብቻ ነው። አላህ ኡማውን የምትጠቅሙ ያድርጋችሁ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
የኒቃቢስቷ መልዕክት
በአስኮ በድር መስጂድ የሴቶች ፕሮግራም ላይ የተላለፈ፦
"ኒቃብ ለብሼ መንቀሳቀስ፤ መማር፤ መስራት መብቴ ነው። መብታችን ሊከበር ይገባል።"
ሙሉ መልዕክቱን https://vt.tiktok.com/ZSVVMbPqD/ በመግባት አዳምጡ። ለሌሎች ይደርስ ዘንድም ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
በዘንድሮው አመት የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተናን ለወሰዳችሁና አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን መቀላቀል ለምትፈልጉ ተማሪዎች፦
ለዚህ ስኬት እንድትበቁ ላደረሳችሁ ጌታችን አላህ ምስጋና ይድረስ። የአመታት ጥረት እና ልፋታችሁን ለትልቅ ስኬት መሠረት የሚሆን ያድርግላችሁ። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስገዝ መሆኑን ተከትሎ ከመግቢያ ፈተና እና አጠቃላይ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ማወቅ ያሉባችሁ ነገሮች ስለሚኖሩ ጀመዓችን ነገ ማለትም ሐሙስ ነሐሴ 21 / 2018 ዓ.ል ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ በሕብረቱ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ (@aaumsu) የኦረንቴሽን ፕሮግራም አዘጋጅቷል። ስለሆነም ቀጠሯችንን ቀጠሯችሁ በማድረግ፤ መልዕክቱንም ለሌሎች በማሰራጨት በሰዓቱ እንገኝ። አላህ ከተሻሉ ስኬቶች ያድርሳችሁ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ሒጃቧ ታሪኳ !
በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVXjj6CP/ በመግባት ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ሪፖስት ያድርጉ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ የሶማሌ ክልል ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው ሒጃብን በመከልከል ያወጣው መመሪያ ከልጅነት ጀምሮ ያደጉበትን ባህል እውቅና እንደሚነፍግ ፤ የሐይማኖት ነፃነታቸውን እንደሚፃረር ፤ የክልሉ ተወላጆች በትምህርት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚቀንስ እንደሆነ በመጥቀስ መመሪያው ይሻሻልና ሁሉንም አቃፊ የሆነ የትምህርት ስርዓት ይዘረጋ ዘንድ የክልሉ መንግስት እንዲሰራ ጠይቀዋል።
መመሪያው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በትምህርት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ወደሗላ የሚያስቀር ስለሆነ ይስተካከል ዘንድ ሁሉም አካል ሊረባረብ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
ከወሎ ደሴ ነው ---
ስለ ሒጃብ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ስለደረሰው የመብት ጥሰት፤ ስለሙስሊም ተማሪዎች መብት፤ ስለሕዝበ ሙስሊሙ አጀንዳዎች ጥያቄ አለን ብለዋል። ለሁሉም ጥያቄዎችም ፍትሐዊ መልስ ሊሰጥ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፍትሕ፤ እኩልነት እና ነፃነት እስኪሰፍን ጥያቄ አለን!
ሒጃብ ለብሶ መማር መብት ነው!!
በሀገር ውስጥ በእኩልነት መተዳደር፤ የሚገባንን በፍትሕ ማግኘት መብት ነው!!!
@aaumsu
