1 149
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1830 день
Архив постов
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሴት ሰራተኞች የሀብት አያያዝ ስልጠና ተጀመረ
🇪🇹 ጥር 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች የሀብት አያያዝና አጠቃቀም ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
ስልጠናው በኢዝ ፕሮጀክት (Education and Skills for Employability EASE) ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ የሰው ኃይል፣ የፋይናንስና የማቴሪያል ሀብቶችን በብቃትና በውጤታማነት ማስተዳደር የሚያስችል አቅም ለመገንባት ዓላማ አድርጎ ተዘጋጅቷል።
በስልጠናው የሚሳተፉ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚሰሩ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች በስራ ቦታቸው ውስን የሆኑ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም፣ ብክነትን መቀነስ እና የተቋሙን አጠቃላይ ውጤታማነት ማሳደግ እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ኢዝ (EASE) ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሴቶችን ተሳትፎና ክህሎት ለማጠናከር የሚሰራ ሲሆን፣ ለዚህ ስልጠናም አስፈላጊውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ አድርጓል።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙ የኮሌጁ ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች ሴት ሰራተኞች በውሳኔ ሰጪነትና በሀብት አስተዳደር ያላቸውን ሚና ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመው፣ የተገኘውን እውቀት በተግባር ላይ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሴት ሰራተኞች የሀብት አያያዝ ስልጠና ተጀመረ
🇪🇹 ጥር 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች የሀብት አያያዝና አጠቃቀም ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
ስልጠናው በኢዝ ፕሮጀክት (Education and Skills for Employability EASE) ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ የሰው ኃይል፣ የፋይናንስና የማቴሪያል ሀብቶችን በብቃትና በውጤታማነት ማስተዳደር የሚያስችል አቅም ለመገንባት ዓላማ አድርጎ ተዘጋጅቷል።
በስልጠናው የሚሳተፉ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚሰሩ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች በስራ ቦታቸው ውስን የሆኑ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም፣ ብክነትን መቀነስ እና የተቋሙን አጠቃላይ ውጤታማነት ማሳደግ እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ኢዝ (EASE) ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሴቶችን ተሳትፎና ክህሎት ለማጠናከር የሚሰራ ሲሆን፣ ለዚህ ስልጠናም አስፈላጊውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ አድርጓል።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙ የኮሌጁ ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች ሴት ሰራተኞች በውሳኔ ሰጪነትና በሀብት አስተዳደር ያላቸውን ሚና ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመው፣ የተገኘውን እውቀት በተግባር ላይ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
ቀን 26/05/2018
ማስታወቂያ
በEASE ፕሮጀክት እሮብ በሚጀመረዉ የሴት አሰልጣኝ እና አስተዳደር ሰራተኞች የሰልጠና ፕሮግራም ድልድል እና የስልጠና ቦታ ( ከ 7:30__10:30)
ማሳሰቢያ ስም ዝርዝር ላይ ያልተካተታቹ ሴት አሰልጣኝ እና የአስተዳደር ሰራተኞች ካላቹ የእናንተ የስራ ዘርፍ የተመደቡ ተሳታፊዎች የስልጠና ቦታ በመገኘት ለአስተባባራዎች ስማቹሁ እንደሌለ በማሳወቅ እና በመመዝገብ ስልጠናዉን መከታተል እንዳለባቹሁ እናሳዉቃለን የ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎችቀን 26/05/2018
ማስታወቂያ
በEASE ፕሮጀክት እሮብ በሚጀመረዉ የሴት አሰልጣኝ እና አስተዳደር ሰራተኞች የሰልጠና ፕሮግራም ድልድል እና የስልጠና ቦታ ( ከ 7:30__10:30)
ማሳሰቢያ ስም ዝርዝር ላይ ያልተካተታቹ ሴት አሰልጣኝ እና የአስተዳደር ሰራተኞች ካላቹ የእናንተ የስራ ዘርፍ የተመደቡ ተሳታፊዎች የስልጠና ቦታ በመገኘት ለአስተባባሪዎች ስማቹሁ እንደሌለ በማሳወቅ እና በመመዝገብ ስልጠናዉን መከታተል እንዳለባቹሁ እናሳዉቃለን የ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች
1 149
ማስታወቂያ
በEASE ፕሮጀክት ለሴት አሰልጣኞች እና ለሴት የአስተዳደር ሰራተኞች ከዕሮብ እስከ ዓርብ (ከ 27/05/2018_ 29/2018ዓ.ም/) ለ 3 ተከታታይ ቀናቶች ስልጠና ሰለሚሰጥ ስልጠና ላይ እንድትገኙ ስንል እናሳዉቃለን ።
የስልጠና ሳዓት ከ 7:30_ 10:30 ነዉ ::
የEASE ፓሮጀክት አስተባባሪ
1 149
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
🇪🇹25/05/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሃያ አራተኛ ሳምንት ተካሄደ ። በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አሰልጣኝ አቶ ከድር አብደላ ለየት ባለ አቀራረብ ያላቸውን የህይወት ፍልስፍና አቅርበዋል ።በ17 አመት የስራ ላይ ቆይታቸው እጅግ ብዙ ስራዎችን እንደሰሩ እና ልምድም ሲባል ስራዎችን ስንሰራ ያካበትነው አቅም እንደሆነ ገልፀው ጠንክረን በመስራት ዋጋ መክፈል ፣ በስራ ቦታችን ላይ ሰአት አክብረን በመገኘት ተገቢውን ስራ ሀላፊነት ወስደን መስራት እንዳለብን ከልምዳቸዉ አካፍለዋል ። በስራ ቆይታቸውም ብዙ የሙያ ልጆች ያፈሩ ሲሆን በኮሌጅ እየሰሩ ያሉ የስራ ባልደረቦቻቸው የበመድረኩ ላይ ትሁት እና ጠንካራ አሰልጣኝ እንደሆኑ በመግለፅ ምስጋና አቅርበዋል ። በመጨረሻም ለኮሌጅ ማህበረሰብ ይጠቅማል ያሉትን የስራ ሰአት ማክበር እና ስራን በጥራት መስራትና ሀላፊነትን መወጣት እንዳለበት በማስገንዘብ ሰራተኛው ከስራ ሰአት ውጪ በመስራት ገቢውን ማሳደግ እንዳለበት አብራርተዋል ።
የኮሌጅ የተቋማት ልማት አስ/ጉ/ም ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ አሰልጠኝ አቶ ከድር አብደላ ሞዴል አሰልጣኝ እንደሚሆኑ ገልፀው የኮሌጅ ማህበረሰብ ስራን በሀላፊነት በመወጣት ለተሻለ ውጤት እንዲሰራ መልክት አስተላልፈዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
🇪🇹25/05/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሃያ አራተኛ ሳምንት ተካሄደ ። በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አሰልጣኝ አቶ ከድር አብደላ ለየት ባለ አቀራረብ ያላቸውን የህይወት ፍልስፍና አቅርበዋል ።በ17 አመት የስራ ላይ ቆይታቸው እጅግ ብዙ ስራዎችን እንደሰሩ እና ልምድም ሲባል ስራዎችን ስንሰራ ያካበትነው አቅም እንደሆነ ገልፀው ጠንክረን በመስራት ዋጋ መክፈል ፣ በስራ ቦታችን ላይ ሰአት አክብረን በመገኘት ተገቢውን ስራ ሀላፊነት ወስደን መስራት እንዳለብን ከልምዳቸዉ አካፍለዋል ። በስራ ቆይታቸውም ብዙ የሙያ ልጆች ያፈሩ ሲሆን በኮሌጅ እየሰሩ ያሉ የስራ ባልደረቦቻቸው የበመድረኩ ላይ ትሁት እና ጠንካራ አሰልጣኝ እንደሆኑ በመግለፅ ምስጋና አቅርበዋል ። በመጨረሻም ለኮሌጅ ማህበረሰብ ይጠቅማል ያሉትን የስራ ሰአት ማክበር እና ስራን በጥራት መስራትና ሀላፊነትን መወጣት እንዳለበት በማስገንዘብ ሰራተኛው ከስራ ሰአት ውጪ በመስራት ገቢውን ማሳደግ እንዳለበት አብራርተዋል ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ ለቀረበዉ አስተማሪ የልምድ ልውውጥ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም ይህን ተሞክሮ በመውሰድ ከግቢው ማህበረሰብ ጋር እንዲሰሩ መልክት አስተላልፈዋል ። የኮሌጅ የተቋማት ልማት አስ/ጉ/ም ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ አሰልጠኝ አቶ ከድር አብደላ ሞዴል አሰልጣኝ እንደሚሆኑ ገልፀው የኮሌጅ ማህበረሰብ ስራን በሀላፊነት በመወጣት ለተሻለ ውጤት እንዲሰራ መልክት አስተላልፈዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
