1 148
Подписчики
-124 часа
-27 дней
-1830 день
Архив постов
1 148
" በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን።" ሮሜ ፲፬ ፥ ፰
የትምህርት ክፍላችን ተማሪ የሆነችው ቅዳሜ በሚኖረው የምርቃት መርሐግብር ላይ ለመመረቅ ዝግጅት ላይ የነበረችው የማርኬቲንግ ተማሪ የሆነችው ወጣት ብሩክታዊት አሸናፊ ባልተጠበቀና ባልተገመተ ሁኔታ ጋውን ለመውሰድ እንደወጣች በመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፏን በመስማታችን የተሰማንን ሀዘን እገልጻለን። የመጽናናት አምላክ ቤተሰቦቿን ፣ ያስተማሯት መምህሮቿንና ጓደኞቿን ብሎም ለትምህርት ክፍሉና በአጠቃላይ ለኮሌጃችን ማኅበረሰብ መጽናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን።
የቀብር ስነ ሥርዓቷም ነገ ይፈጸማል 😭
እግዚአብሔር ነፍሷን ከደጋግ ቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን
የተፈሪ መኮንን ፖለቲካ ኮሌጅ
1 148
መስከረም 05/2018ዓ/ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያው የወርቃማው ሰኞ የልምድ ልውውጥ መድረክ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህር ቀሲስ ትጉህ መሃሪ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያውን ወርቃማው ሰኞ የልምድ ልውውጥ አደረጉ ። ትምህርት የሚገኘው በመደበኛ የትምህርት አሰጣጥ ብቻ ሳይሆን ብዙ መጸሀፍቶችን በማንበብ የሚገኝ ሲሆን አብዛኛዎቹ መጸሀፎች የተፃፉት የሰዎች የህይወት ልምዶች ላይ ጥናት በማድረግ ነዉ በማለት የሰዎች የግል ተሞክሮ በጣም ጠቃሚና አስተማሪ መሆኑን የገለፁት መምህር ቀሲስ ትጉህ መሃሪ ለልምድ ልውውጥ ስለተጋበዙ ምስጋና አቅርበዋል።በአምቦ ወረዳ ሶስት በ1975 ዓ/ም የተወለድት መምህር ቀሲስ ትጉህ መሃሪ የመንፈሳዊ እና አለማዊ ትምህርታቸውን ጎን ለጓን እንደተማሩ ገልፀው ።የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአንቦ ቼሪ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአንቦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን በ1994 ዓ/ም 12ኛ ክፍል አጠናቀዋል ።የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በቲዎሎጂ የሰሩ ሲሆን በመንፈሳዊ ትምህርት።፣በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግብርና ደረጃ አንድ እና ሁለትን ፣በቲያትርሪካል አርት ተምረው ኮሌጁ በመምህርነት እንደቀጠራቸው እና በህይወታቸው ደስተኛ የሆኑበት አጋጣሚ እንደሆነ እና በመንፈሳዊ አገልግሎት እና በበጎ አድራጎት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።
መምህር ቀሲስ ትጉህ መሃሪ በባቡር መንገድ ካቦነት እና የተለያዩ ሀሳቦችን በማፍለቅ በተለያዩ ስራዎችን ማለትም በመዝሙር ካሴትና ሲዲ ሽያጭ እና በከተማ ግብርና ዘርፍ የራሳቸውን ስራ ይሰሩ እንደነበር ጭምር ተሞክሮአቸውን ሲያጋጥሟቸው የነበሩትን ተግዳሮቶች በማንሳት ለኮሌጁ ማህበረሰብ አካፍለዋል።
ኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
ጳግሜ 5/2017 ዓ/ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዋና በር መግቢያ ርክክብ እና የማእድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሄደ።
በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ለኮሌጁ የተሰራው የዋና በር መግቢያ ማህበሩ አሰርቶ ስለጨረሰ የርክክብ ኘሮግራም እና የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳቹ ልዩ ስጦታ በማህበሩና በኮሎጁ በጥምርት ለኮሌጁ ሰራተኞች፣ኮሌጁ ለሚያሳድገው ልጆች የተበረከተ ሲሆን ወ/ሮ ዳግማዊት የስራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ናየተቋማት ልማት ዘርፍ ሀላፊ ፣ክብርት ወ/ሮ ቆንጅት ተድላ የማህበሩ የሀገር ውስጥ ተጠሪና የቦርድ ፀሀፊ፣ ወ/ሮ የምስራች ፈለቀ የማህበሩ የኢትዮጲያ ቻፕተር ሰብሳቢ፣ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር አባላት እና የቦርድ አባላት፣አቶ አብዱልበር መሀመድ የኮሌጁ ዋና ዲን እና የኮሌጁ አመራሮችና የኮሌጁ ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል ።
1 148
ጳግሜ 3/2017 ዓ/ም
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለአራተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት የኮሌጁ ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ ትውልድን በጋራ መገንባት የወላጆች ተሳትፎ በልጆች ሕይወት ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰጥተዋል ።ልጆች ካላማቋረጥ በዙሪያቸው ካላቸው መስተጋብሮች ማለትም ከማህበራዊ ሚዲያ፣ከአቻዎቻቸው ፣ከትምህርት ቤት ትምህርቶችን ይወስዳሉ በመሆኑም ልጆችን የማሳደግ ሂደት እንደ ወቅቱ የሚለዋወጥ ስለሆነ በልጆች አስተዳደግ ዙሪያ የሚታወቁትን አራት የወላጅ አይነቶች አብራርተዋል ።በልጆች አስተዳደግ ዙሪያ የራሳቸውን ተሞክሮ አካፍለው ሁሉም የግቢው ማህበረሰብ እኔ በየትኛው የልጆች አስተዳደግ ውስጥ ነኝ የሚለውን እንዲያጤኑበት መልክት አስተላልፏል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድ
1 148
26/12/2017ዓ/ም
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሶስተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አሰልጣኝ ወ/ሮ ማህሌት ሰለሞን ለየት ባለ አቀራረብ በቀዳማዊ ልጅነት ላይ አጠር ያለ ፕረዘንቴሽን አቅርበዋል ።የ23 አመት የስራ ላይ ቆይታቸው እጅግ ብዙ ስራዎችን እንደሰሩ እና ልምድም ሲባል እነዚህን ስራዎች ስንሰራ ያጋጠሙንና ያሳለፍናቸውን ውጣውረዶች ማለትም እንደሆነ ገልፀው ጠንክረን መስራት ዋጋ መክፈል እንዳለብን ከልምዳቸዉ አካፍለዋል ።እንደ ተሞክሮ ለሌሎች ዲፓርትመንቶች ይጠቅማል ያሉትን ትምህርትና ስልጠና ከመጀመሩ በፊት አጠር ያለ ከሰልጣኞች ጋር የሚደረግ ዉይይት የሰልጣኞችን የመረዳትና የመቀበል አቅም ዉጤታማ እንደሚያደርግው ገልፀዋል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ ለቀረበዉ አስተማሪ የልምድ ልውውጥ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም ይህን ተሞክሮ በመውሰድ ከግቢው ማህበረሰብ ጋር እንዲሰሩ መልክት አስተላልፈዋል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
ነሐሴ 20/2017 ዓ/ም
ከባለ ድርሻ አካላት እና ከተገልጋዮች ጋር የጋራ መድረክ ተካሄደ
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀተ ዓመት ዕቅድ ውይይት ከባለ ድርሻ አካላት እና ከተገልጋዮች ጋር የጋራ መድረክ ያካሄደ ሲሆን ከመድረኩ ለመረዳት እንደቻለው ኮሌጁ ባቀረበው የ2018 በጀተ ዓመት ዕቅድ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።በዕቅድ ዙሪያ የጋራ ስምምነት ላይ በመደረሱ ከሚመለከታቸው አካላት ማለትም ከሆቴል ባለቤቶች ማህበር፣ከመከላከያ፣ከፖሊስ፣ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ከትምህርትና ስልጠና ዘርፍ እና ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅታዊ አሰራር እና ትብብር የሚሰሩ ተግባራት የተዘጋጀ ትስስር ሰነድ ኮሌጁ ተፈራርሟል።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
