ru
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закрытый канал
1 149
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1830 день
Архив постов
የEASE ፕሮጀክት ስራ አፈፃፀም ፣የእቅድ ውይይት እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 15/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት ስራ አፈፃፀም እና የእቅድ ውይይት መድረክ ተካሄደ ።የEASE ፕሮጀክት የአንድ አመት ስራ አፈፃፀም በዝርዝር ለኮሌጁ ማህበረሰብ EASE ፕሮጀክት አባል አቶ መንክር ግርማ ቀርቧል ። አያይዞም በቀጣይ የሚተገበረው የEASE ፕሮጀክት እቅድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ከመድረክ ለተነሱም ሀሳቦች በኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ደምበላሽ ተስፋዬ እና በEASE ፕሮጀክት መሪ ወ/ት ቤተልሄም አሰፋ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።በአጠቃላይ የEASE ፕሮጀክት በስልጠና አሰጣጥ ፣ ስራ ፈጠራና ኢኖቬሽን ልእቀት ለማምጣት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የበቁና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን ለማፍራት የሚያግዝ ፤ ለሴቶች እና ስደተኞች ልዪ ድጋፍ በማድረግ ያበቃል ፤ በሊደርሽፕ እና ማኔጅመንት ስልጠና ለእስታፎች በማመቻቸትና ማብቃት ፤ ስልጠና አሰጣጡን ምቹና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ሰልጣኞች ሳይጉላሉ ባሉበት አካባቢ ስልጠና በማመቻቸት እና ሌሎችም ተግባራቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ይሰራል ። እንደ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት አተገባበሩ ላይ ሰፊ ግንዛቤ ለኮሌጅ ማህበረሰብ ተፈጥሯል ። በመድረኩም ላይ በኮሌጅ ምክትል ዲን ዶ/ር ከበደ አዲስ ኮሌጅን ለተቀላቀሉ አሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣቹ መልእክት አስተላልፈዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

photo content
+9

photo content

photo content

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለአስራ ዘጠነኛ ሳምንት ተካሄደ። በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አሰልጣኝ አቶ አለማየሁ ፈንታ "የኢኮኖሚን ጫና እንዴት መቋቋም እንችላለን " በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ለኮሌጅ ማህበረሰብ ግንዛቤ ፈጥረዋል ። የ21ኛውን ክፍለ ዘመን የኢኮኖሚ ጫና በተለይም በማደግ ላይ ያሉ ባሉ ሀገራት የዋጋ ግሽፈት ፣ የገንዘብ የመግዛት አቅም መቀነስ ፣ የስራ አጥነት መሰረታዊ ችግሮች ናቸው በማለት የኢኮኖሚ ጫናን ለመቋቋም የሚረድ አምስት ዋና ዋና መንገዶችን በጥልቀት አብራርተዋል ። የኢኮኖሚ ጫናን ለመቋቋም የመጀመሪያው እርምጃ ያለንን ሀብት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን በመለየት በአግባቡ ማስተዳደር እንዳለብንና ወጪዎቻችንን መመዝገብና የአደጋ ጊዜ ፈንድ ማስቀመጥ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

photo content

Video from Getenesh

ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ጋር በመተባበር ከስደት ተመላሽ ሴቶችን ለአንድ ወር በኩሊነሪ አርት እና በፀጉር ስራ ያሰለጠናቸውን ሴት ሰልጣኞች አስመረቀ ።

photo content

ተፈሪ መኮኮንን ፖ /ቴ /ኮ  ከዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ጋር  በመተባበር በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች አስመረቀ ። 🇪🇹ታህሳስ 08 /2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ከዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር  ጋር በመተባበር ከስደት ተመላሽ ሴቶችን ለአንድ ወር በኩሊነሪ አርት እና በፀጉር ስራ ያሰለጠናቸውን ሴት ሰልጣኞች አስመረቀ ። በእለቱም  የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የዴክ  ዴቨሎፕመንት እስኪል ፕሮግራም ዳሬክተር አቶ ተመስገን ታደለ ያደረጉ ሲሆን ለስልጠናው መሳካት ኮሌጅ ላበረከተው አስተዋጽዎ አመስግነዋል  ። በምረቃ ፕሮግራም ላይ ለተገኙ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ፣ የንፋስ ስልክ  ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣የስራና ክህሎት ሚኒስቴር እና ተመራቂዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልክት አስተላልፈዋል ።       የዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ለተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ለንፋስ ስልክ  ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለእያንዳንዳቸው የስድስት መቶ ሺህ ብር የስልጠና እቃዎችን በስጦታ አበርክተዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ተፈሪ መኮኮንን ፖ /ቴ /ኮ ከዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ጋር በመተባበር በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች አስመረቀ ። 🇪🇹ታህሳስ 08 /2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ጋር በመተባበር ከስደት ተመላሽ ሴቶችን ለአንድ ወር በኩሊነሪ አርት እና በፀጉር ስራ ያሰለጠናቸውን ሴት ሰልጣኞች አስመረቀ ። በእለቱም የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የዴክ ዴቨሎፕመንት እስኪል ፕሮግራም ዳሬክተር አቶ ተመስገን ታደለ ያደረጉ ሲሆን ለስልጠናው መሳካት ኮሌጅ ላበረከተው አስተዋጽዎ አመስግነዋል ። በምረቃ ፕሮግራም ላይ ለተገኙ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣የስራና ክህሎት ሚኒስቴር እና ተመራቂዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልክት አስተላልፈዋል ። የዴቨሎፕመንት ኤክስፐርታይዝ ሴንተር ለተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ለንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለእያንዳንዳቸው የስድስት መቶ ብር የስልጠና እቃዎችን በስጦታ አበርክተዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

photo content

photo content

ሰላም ዋላችሁ በአንደኛ እና በሁለተኛ ዙር ስልጠና ያልተሳተፋችሁ አሰልጣኞችና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ አርብ 3:00 ሰአት ስልጠና ስለሚሰጥ በሰዓቱ ቴክኖሎጅ አዳራሽ እንድትገኙ። የሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት

በተፈሪ መኮንን ፖ/ ቴ/ኮ ለአመራሮችና ሰራተኞች የግብረገብ ስልጠና ተሰጠ ። 🇪🇹ታህሳስ 08 /2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፀረ ሙስና ዳሬክቶሬት የተዘጋጀ የግብረገብ ስልጠና ለኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ ። በስልጠናው መግቢያ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሽሮሜዳ ካምፓስ ዲን አቶ ተስፋጺኦን እንደገለፁት ግብረገብ ሲባል ሁላችንም እንደምናውቀው ሳይሆን በተግባር የምንሆነው እሴታችን ነው ስለሆነም ይህ ስልጠና የምንማማርበት መድረክ የሚፈጥረር ነው በማለት መልክት አስተላልፈዋል ።ስልጠናው ግብረገብ ምንነትና ምንጭ ፣ግብረገባዊ ግዴታዎች ፣ግብረገብ እሴት ማዳበር ዓላማዎች ፣ የግብረገብ እሴትቶች ማሽቆልቆል ፣የአመራርና ሰራተኛው ግብረገብ ላይ ከአ.አ ፀረ-ሙስና የመጣ ባለሙያ ተሰቷል ።ስልጠናውም አአላማ በሰራተኝው እና በአመራር ዘንድ የሚስተዋለውን የስነ ምግባርና ግብረገብ እሴቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መሄድ ከዚህ ጋር በተያያዘ ሰራተኛውና አመራሩን በማንቃት ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ስላስፈለገ እንደሆነ ተገልጿል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን ቡድን

photo content
+5