ru
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закрытый канал
1 149
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1830 день
Архив постов
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የንብረት ልየታና የዲጂታል አስተዳደር ሥርዓት (AMIS) ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። 🇪🇹01/07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የያዘውን ግዙፍ ሀብትና ንብረት በዘመናዊ መንገድ ለማስተዳደርና የተቋሙን አገልግሎት ለማቀላጠፍ የሚያስችለውን የንብረት ልየታና የዲጂታል አስተዳደር ሥርዓት (Asset Management Information System - AMIS) ወደ ተግባር እያሸጋገረ ይገኛል። ይህ የንብረት ልየታ ሥራ ኮሌጁን ወደ "ስማርት ሲቲ" (Smart City) መንደርነት ለመለወጥ የሚደረገው ጥረት አካል ሲሆን፣ በተለይም አገልግሎት እየሰጡ ያሉ፣ የተጠገኑና ዳግም ወደ አገልግሎት የሚገቡ ንብረቶች መረጃ በሲስተም እንዲደራጁ ለማድረግ ያለመ ነው። ለንብረት ልየታ ሥራው የተቋቋመው ኮሚቴ እስካሁን ባከናወናቸው ተግባራት ዙሪያ ግምገማ ያደረገ ሲሆን፣ በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን የመለየትና መፍትሔ የመስጠት ሥራ ተከናውኗል። ኮሚቴው የደረሰበትን ደረጃና ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን ለሚመለከተው አካል በየጊዜው ሪፖርት እንዲያደርግ ተገልጿል። የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በጉዳዩ ላይ በሰጡት አቅጣጫ፣ በንብረት ክፍል ያልተመዘገቡ የኮሌጁ ንብረቶች በአፋጣኝ ተለይተው በሲስተም እንዲገቡ አሳስበዋል። አክለውም ሁሉም የሥራ ክፍል አመራሮች የልየታ ሥራውን በባለቤትነት እንዲያስተባብሩ፣ ያልተመዘገቡ ንብረቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተለይተው ሪፖርት እንዲደረጉ፣የተቋሙን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዲቻል ቁጥጥሩ እንዲጠናከር አቅጣጫ ሰጥተዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+4

Repost from N/a
ኮሌጆች እባካችሁ አስቸኳይ ነው ለተፈታኞቹ ይህንን ኮድ ዛሬ አድርሷቸው ዛሬም በተጨማሪ ለፈተና ሲመጡ ሞባይል ወረቀት ይዞ መምጣት አይቻልም ፡፡ መታወቂያ የኮሌጁን ይዘው መገኘት አለባቸው

የሚመዘኑ አሰልጣኞች በዚህ እንዲዘጋጁ ይላክላቸው

Document from mohamed Jemal

የትብብር ስልጠና ለሚወጡ የቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ የማርኬቲንግ ሰልጣኞች ኦረንቴሽን ተሰጠ ። 🇪🇹30/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የትብብር ስልጠና ጥራት ለማሳደግ ሰ
+6
የትብብር ስልጠና ለሚወጡ የቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ የማርኬቲንግ ሰልጣኞች ኦረንቴሽን ተሰጠ ። 🇪🇹30/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የትብብር ስልጠና ጥራት ለማሳደግ ሰልጣኞች በትብብር ስልጠና ወቅት የሚያጋጥሙአቸውን የኢንድስትሪ ነባራዊ ሁኔታ በማስገንዘብ እራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉና ያልተረድት ሀሳብ እና አሰራር ካለ ግልጽ ለማድረግና አላማውን እንዲርዱት የሚያስችል ነው ። የኮሌጅ አ/ጉ/ም/ዲ አቶ ደምበላሽ ተስፋዬ ሰልጣኞች በኮሌጁ የነበራቸውን የቆይታ ጊዜ የጨረሱ ሲሆን ወደ ትብብር ስልጠና ከመሄዳቸው በፊት በትብብር ስልጠና  ወቅት ከሰልጣኝ ምን እንደሚጠበቅ፣ማሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች እና መተግበር የሚገባቸው የስራ ስነ ምግባር ኦረንቴሽን አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል ። ትብብር ስልጠና የሚወጡ ሰልጣኞች ለአንድ ወር በካምፖኒ የስራ ላይ ስልጠና መውሰድ እንዳለባቸውና በስምንቱም የብቃት አሀዶች ውጤታቸውን አስሞልተው በተቀመጠው ጊዜ ማምጣት እንዳለባቸው የተገለፀላቸው ሲሆን ሰልጣኞች ለትብብር ስልጠና ሲሄድ መያዝ ያለባቸው የውል ደብዳቤ ፣ የብቃት አሀድ ፣ አቴንዳንስ እና የውጤት ማስሞያ ተዘጋጅቶ ተሰቷቸዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ሰማችሁ በዚህ ዝርዝር ውሰጠ የተካተተ የኮሌጃችን አሰልጣኞች በተላለፈው መለዕክት መሠረት ለፈተና እንድትቀርቡ አናሳውቃለን

Repost from N/a
ሰላም እንደምን አላችሁ የኮሌጅ የሰው ሀብት ዳይሬክተሮች እነዚህን አሰልጣኞች ለመጋቢት 4/2018 አስቱ ዩንቨርስቲ ፈተና ስለሚሰጥ ጠዋት 2፡00 ከላይ በተጠቀሰው ቀን እንዲገኙ ጥሪ አስተላልፉላቸው

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "ለውጥን መቃወም" በሚል ርዕስ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ። 🇪🇹30/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ የሚካሄደው "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለ26ኛ ሳምንት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። በዕለቱ የብረታ ብረት የስልጠና ዘርፍ አሰልጣኝ የሆኑት አቶ መኮንን ጣሰው "ለውጥን መቃወም" በሚል ርዕስ ሰፊና ትምህርታዊ ገለጻ ለኮሌጁ ማህበረሰብ አቅርበዋል። አቶ መኮንን በአቀራረባቸው ለውጥን መቃወም ማለት ሰዎች አዳዲስ ሀሳቦችን፣ ቴክኖሎጂዎችን ወይም አሰራሮችን ለመቀበል የሚያሳዩት የመከላከያ ባህሪ መሆኑን አስረድተዋል። መቃወም በግል፣ በቡድንና በተቋም ደረጃ ሊከሰት እንደሚችል የገለጹት አሰልጣኙ፣ ይህም በስራ ፍጥነት፣ በምርታማነትና በእድገት ላይ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተጽዕኖ በዝርዝር አብራርተዋል። ይህን ችግር ለመፍታትም የሚከተሉት የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተጠቁመዋል ስለ ለውጡ አስቀድሞ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር፤ ግልጽ የሆነ የኮሙኒኬሽን ወይም የመግባቢያ ስርአት መዘርጋት ፤ ሰራተኞችን በለውጥ ሂደቱ ላይ በንቃት ማሳተፍና ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ፤ ለውጡን ለተቀበሉ አካላት ማበረታቻዎችን መስጠት። አሰልጣኙ አክለውም የቴክኖሎጂ፣ የድርጅት አወቃቀር፣ የባህሪ እና የስትራቴጂ ለውጦችን በበጎ መልኩ በመቀበል ራስን፣ ተቋምንና ሀገርን ብቁ ማድረግ እንደሚገባ የራሳቸውን የህይወት ተሞክሮ በማጣቀስ አስገንዝበዋል። የኮሌጁ የተቋማት ልማት አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ በአሰልጣኙ የቀረበውን ገለጻ አድንቀው፣ ተቋሙ ካለበት የለውጥ ጉዞ አንጻር ግንዛቤው ወቅታዊና ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ሌሎች የኮሌጁ ሰራተኞች መሰል የልምድ ልውውጦችን በማቅረብ የጋራ እውቀትን እንዲያሳድጉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

"የምርጫዬ" መተግበሪያ የአጠቃቀም ቅደም ተከተል 1.“ምርጫዬ” የተሰኘውን የመራጮች መመዝገቢያ መተግበሪያ ከPlay Store / APP Store በማውረድ በስልክዎ ላይ ይጫኑ፣ 2.በስልክዎ ላይ ከተጫኑ ዝርዝር መተግበሪያዎች ውስጥ “ምርጫዬ” የሚለውን መተግበሪያ ይክፈቱ፣ 3.በመቀጠልም ከተከፈተው የ“ምርጫዬ” መተግበሪያ ላይ የሚጠቀሙበትን ቋንቋ ይምረጡ፣ 4.ቋንቋ መርጠው ከገቡ በኋላ ከሚያገኟቸው ዝርዝሮች ውስጥ “የእርስዎን መገለጫ ይፍጠሩ” የሚለውን ይጫኑ፣ 5.በመቀጠል “በፋይዳ አማካኝነት ወደ መለያ” የሚለውን አማራጭ ይጫኑ፣ 6.የፋይዳ ገጹ ሲመጣልዎ ከፋይዳ መታወቂያዎት ላይ 16 አኅዝ ያለውን ቁጥር (FAN) ካስገቡ በኋላ በስልክዎ የሚላክልዎን ባለስድስት አኅዝ የአንድ ጊዜ ማረጋገጫ ቁጥር (OTP) ይሙሉ

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የECDD ፕሮጀክት የአካቶ ስልጠና ውጤታማነት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ቀጠለ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የECDD ፕ
+9
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የECDD ፕሮጀክት የአካቶ ስልጠና ውጤታማነት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ቀጠለ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የECDD ፕሮጀክት የአካቶ ስልጠናን በኮሌጅ  ውጤታማ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ቀጥሏል ። ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም የኮሌጅን ምድረ ግቢ ለአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞች ምቹ የማድረግ ስራ ከተቋሙ ጋር እየሰራ ይገኛል ። በመሆኑም በቀን 27/06/2018 ዓ.ም ECDD በኢጣሊያን በራይዝ ፕሮጀክት ድጋፍ በአርባ አምስት ቀናት  ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲውል የታቀደው የአካል ጉዳተኞች ምቹ መፀዳጃ ቤት እና ሁለት የአካል ጉዳተኛ ራምፕ በአርት ጋለሪ እና በኮሪያ ህንፃ ላይ ለመስራት ከስራ ተቋራጮች፣ከኢሲዲዲ እና ከኮሌጁ ጋር ውል ተፈራርመዋል። የኮሌጁ አመራሮችም  ለአካቶ ትምህርትና ስልጠና የኮሌጅን ምድረ ግቢ ምቹ ከማድረግና ስልጠና አሰጣጡን ለአካል ጉዳተኞች እኩል ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልፀው የECDD ፕሮጀክት እያደርገ ላለው  ድጋፍ በኮለጁ ስም ምስጋና አቅርበዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ጥብቅ ማሳሰቢያ                   ምደባ ያላገኙ  አሰልጣኞች  በፐብሊክ ሰርቪስና የሰውሃብት ቢሮ የተላለፈ  መልዕክት   መጋቢት 04/2018 ከጠዋቱ 2:00 ሰአት አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (aastu) የብቃት ምዘና ሰለሚኖር ሁሉም እንዲገኙ ይደረግ። በዚህ ምዘና ያላለፈ ምደባ የማያገኝ መሆኑን በግልፅ እንዲያውቁት ይደረግ። ማስታወሻ:- (1)ሲመጡ ሞባይል እና ኤሌክትሮኒክስ ነክ ነገሮች ይዞ መግባት አይቻልም።(2) ማንነትን የሚገልፅ የኮሌጅ መታወቂያ ይዞ እንዲገኙ

ለኮሌጁ  ውድ  የተከበራቹ   የሴት  አሰልጣኞች  እና  የአስተዳደር  ሰራተኞች  በሙሉ  እንኳን  ለ አለም  አቀፍ  የሴቶች  ቀን  ማርች 8  አደረሳቹ!!!!! የሰዓት ለውጥ ተደርጓል!!!! ሰኞ  የካቲት  30/2018 ዓ.ም   ስራና  ክህሎት  ቢሮ  አለም   ዓቀፍ የሴቶች  ቀን  ማርች  8   በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለማክበር  ዝግጅቱን  አጠናቋል ስለዚህ  በዕለቱ  ሁላቹሁም  ነጭ ልብስ ለብሳቹ   ከሰዓት 7:00   ሰዓት   በኮሌጅ  በመገኘት  በተዘጋጀው  መኪና     በጋራ  የሚኬድ  መሆኑን  ከወዲሁ     እናሳውቃለን። የኮሌጁ አዲስ የተቋቋመው የሴት  ፎረም  አባላት  በሙሉ  እንድታስተባብሩ  መረጃ  እንዲያዝ  እናሳውቃለን   !!! ኮሌጁ!!!

በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሳንፎርድ ት/ቤት ተማሪዎች ጉብኝት አደረጉ ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የእስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ ጉብኝት ያደረጉት የ
+9
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሳንፎርድ ት/ቤት ተማሪዎች ጉብኝት አደረጉ ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የእስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ ጉብኝት ያደረጉት የሳንፎርድ ት/ቤት የ10 እና 11 ክፍል ተማሪዎች ለስልጠና የሚውል አላቂ እቃዎችን ለኮሌጁ አ/ጉ/ም/ዲ አቶ ደምበላሽ ተስፋዬ በኩል አስረክበዋል ።ተማሪዎቹም እንደገለፁት አላማ አድርገው የተነሱ የአርት ሰዎችን በሀገራችን የሚሰጣቸውን ትኩረት ለመጨመር መሆኑን ገልፀው ። በኮሌጅ የነበራቸው ጉብኝት ለተቋሙ ድጋፍ ለማድረግ እንዳነሳሳቸውና በቀጣይ ባላቸው የተማሪዎች ድረገፅ ኮሌጁን የማስተዋወቅ ስራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል ። የኮሌጅ አ/ጉ/ም/ዲ አቶ ደምበላሽ ተስፋዬ ድጋፍ ያደረጉትን የሳንፎርድ ት/ቤት ተማሪዎች አመስግነው አገር ተረካቢ ዜጎች በዚህ ልክ አስበው ባደረጉት አስተዋፅዎ ኮሌጁ ስልጠና ለሚፈልጉ ተማሪዎች በእስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ ስልጠና እንደሚመቻችላቸው ገልፀዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ለኮሌጁ  ውድ የተከበራቹ   የሴት  አሰልጣኞች  እና  የአስተዳደር  ሰራተኞች  በሙሉ  እንኳን  ለ አለም  አቀፍ  የሴቶች  ቀን  ማርች 8  አደረሳቹ!!!!! ሰኞ  የካቲት  30/2018 ዓ.ም   ስራና  ክህሎት  ቢሮ  አለም   ዓቀፍ የሴቶች  ቀን  ማርች  8   በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለማክበር  ዝግጅቱን  አጠናቋል ስለዚህ  በዕለቱ  ሁላቹሁም  ነጭ ልብስ ለብሳቹ   ጠዋት  1:00    በኮሌጅ  በመገኘት  በተዘጋጀው  መኪና     በጋራ  የሚኬድ  መሆኑን  ከወዲሁ     እናሳውቃለን። የኮሌጁ አዲስ የተቋቋመው የሴት  ፎረም  አባላት  በሙሉ  እንድታስተባብሩ  መረጃ  እንዲያዝ  እናሳውቃለን   !!! ኮሌጁ!!!

የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ቀረበ ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ ያለ
+4
የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ቀረበ ። 🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹 የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ ያለውን የሥራ ሂደት፣ የአመራር ሥርዓትና የአገልግሎት አሰጣጥ ነባራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ያካሄደውን ጥልቅ የዳሰሳ ጥናት ውጤት አቀረበ። አንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያገኘውን ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚያስችል የካይዘን የነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳ ጥናት ውጤት ለኮሌጁ አመራሮች፣ ለዳይሬክቶሬቶች ፣አካዳሚክ ኮሚሽን አባላትና ለካይዘን አስተባባሪዎች ባቀረቡት በዚህ ጥናት ተቋሙ ቀደም የተገበራቸውን የጥራት ስታንዳርዶች ይበልጥ ለማሳደግና ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የካይዘን ፍልስፍና ያለውን ሚና ጉልህ እንደሆነ ገልፀዋል ። ጥናቱ በተለይ በአካዳሚክ ዘርፍ፣ በቴክኒክ ስልጠና ክፍሎችና በአስተዳደራዊ ስራዎች ላይ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከር፣ ክፍተቶችን ደግሞ በካይዘን ቴክኖሎጂዎች ለመሙላት የሚያስችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አካቷል። የካይዘን ልህቀት ማዕከል ባለሙያዎች እንደገለጹት ይህ ጥናት አመራሩ የለውጥ ሂደቱን በባለቤትነት እንዲመራና ለታችኛው ሰራተኛ አርአያ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነው። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን