ru
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закрытый канал
1 146
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1830 день
Архив постов
ዕለተ ማክሰኞ ጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም     የዓዲስ ዓመት የበዓል ስጦታ መርሀ-ግብር ተካሄደ። የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ማህበር  በተለያዩ ግዚያት ዝቅተኛ ተከፋይ የኮሌጁ ሰራተኞችና ለአቅመ ደካማ የአካባቢው ማህበረሰብ  የበጎ አድራጎት ስራዎችንና የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብርን ተግባራዊ እያደረገ  የመጣ መሆኑ ይታወቃ። በዛሬው ዕለትም  አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ የኮሌጁ ሠራተኞች ለ2017ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ የበዓል ስጦታ ለ138 ሠራተኞች አበርክተውላቸዋል። በፕሮግራሙ ላይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ማህበሩ በተለያዩ ግዚያት የአብሮነት ባህልን የሚያዳብር ተግባር በማከናወን  ከጎናችን መሆኑን በመግለፅ ይህንን መርሀ-ግብር ላዘጋጁ የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ህብረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም  2017 ለኮሌጃችን ትልቅ መነሳሳትን የምንፈጥርበት እና ወደ ቀደመ ክብራችን ከፍ የምንልበት 100ኛ ዓመት ክብረ በዓልን የምናከብርበት በመሆኑ ይህንን እውን ለማድረግ ሁላችንም በትጋት የምንሳተፍበት እንዲሆን አሳስበው መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላቸው በድጋሚ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። በተመሳሳይ የማህበሩ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብስራት አክሊሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ። አክለውም በትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አስታውሰው ከዚህ ትምህርት ቤት የወጡ ተማሪዎች/የትምህርት ቤቱ ፍሬዎች በሃገራችንም ሆነ በመላው ዓለም በተሻለ ደረጃ ላይ ያሉና ሃገርንም ሆነ ትምህርት ቤቱን የሚያስጠሩ በትልልቅ ደረጃ የሚገኙ መሆናቸውን የጠቆሙት ፕሬዘዳንቱ ይህንን አቅም ተጠቅመን የቀድሞ ስሙን ለማስመለስ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን በመጠቆም ሚያዝያ 19/2017 100ኛ ዓመቱን በጋራ ለማክበር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ስጦታው የተበረከተላቸው የኮሌጁ ሠራተኞችም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። በተጨማሪም የተፈሪ መኮንን የ100  ዓመትን ታሪክ የሚዳስስ 400 ገጽ ያለው የመጽሐፍ ዝግጅት ከሰዓዳ ህትመት፣ ማስታወቂያና ተያያዥ ስራዎች ድርጅት ጋር በጋዜጠኛ ብሩክ መኮንን እና የማህበሩ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብስራት አክሊሉ የውል ስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል ።                                ኮሙኒኬሽን ብድን

photo content
+9

photo content

ለመላው የኮሌጁ ማህበረሰብ አዲሱ ዓመት የሰላም፣የፍቅርና የብልጽግና ይሁንላችሁ።            ኮሙኒኬሽን ቡድን

ጳጉሜን 5፤ 2016 - የነገ ቀን “የዛሬ ትጋት፤ ለነገ ትሩፋት”

photo content

ጳጉሜን 4፤ 2016 - የህብር ቀን “ኅብረት ለሰላማችን"

photo content

ጳጉሜን 3፤ 2016 - የሉዓላዊነት ቀን  “ኀብር ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት”

ጳጉሜን 2፤ 2016 ዓ.ም - የሪፎርም ቀን “ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት”

photo content

ጻጉሜ

photo content

photo content

Video from Teshe

photo content

photo content

የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የመፃኢ ጊዜ እድላችንን ከሚወስኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር "ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት" በሚል መሪ ሃሳብ ከመላው ሀገሪቱ ለተወጣጡ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ አሁን ያለንበት ጊዜ እውቀት ብቻውን ምሉዕ እንደማያደርግ ከግምት በማስገባት ዓለም ላይ ለክህሎት ልማት ልዩ ትኩረት የተሰጠበት ወቅት ነው፡፡ እኛም እንደ ሀገር በዘርፉ መሰረት ለመጣል ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ በቅርቡ ለሀገራዊ ፍላጎቶቻችን ምላሽ የሚሰጥ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡  ይህም በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ይስተዋል ነበረውን ክፍተት የሚሞላ ብቻ ሳይሆን የሥልጠና ስርዓታችን ጊዜውን የዋጀና ለሀገራዊ ልማትና ብልጽግና ጉዞ የበኩሉን ድርሻ መወጣት የሚችሉ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያስችላል፡፡ ፖሊሲውን ተከትሎ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተግባራዊ ያደረገው አዲሱ የዘርፉ እሳቤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ልማት ፍላጎት የሚመልስ፣ በዘርፉ የነበሩ አለመጣጣሞችን የሚፈታ እንዲሁም አሰልጣኞችም ሆኑ ሠልጣኞች ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ይህም የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ እንደ ሀገር የመፃኢ ጊዜ እድላችንን ከሚወስኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ አሁን የሚሰጠው ስልጠና በዘርፉ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ አሰልጣኞች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማድረግ ባለፈ ባህሪያዊና ቴክኒካዊ ብቃቶችን በማሳደግ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት በ17 የስልጠና ማዕከላት የሚሰጠው ስልጠና በዘርፉ ልህቀትን ለማምጣት የሚያስችል እንደሆነ ያመላከቱት ክብርት ሚኒስትር በመድረኩ 24 ሺህ የሚጠጉ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል፡፡ በተያየዘም የእንጦጦ ፖሊ ቴ /ኮ አሰልጣኞች ስልጠናዉን በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ተገኝዉ እየተከታተሉ ይገኛሉ። መረጃዉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ነዉ። የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+1