1 156
Подписчики
Нет данных24 часа
-67 дней
-2130 день
Архив постов
1 156
ቴክኒክና ሙያ ትምህርትን ለማሳደግ ያለመው የ“EASE” ፕሮጀክት በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ ።
🇪🇹29/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና (TVET) በዜጎች ዘንድ ተመራጭ እንዲሆንና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ፣ ከተባባሪ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተባለው በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫና የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት፤ በትምህርትና ክህሎት ለስራ ብቃት (EASE) የተሰኘው ፕሮጀክት ኮሌጁና የዘርፉ ተቋማት የቆሙለትን አገራዊ ዓላማ ለማሳካት ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ24 ቦታዎች፣ በአዲስ አበባ ደግሞ በሦስት ኮሌጆች ላይ እየተተገበረ መሆኑን የጠቀሱት ዲኑ፤ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንደኛው ተጠቃሚ በመሆን መጠነ ሰፊ ስራዎችን በቅንጅት እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። አቶ ተሾመ አክለውም፣ ለቀረበላቸው ጥሪ አክብሮት ሰጥተው በመድረኩ የተገኙትንና ከኮሌጁ ጋር በቀጥታ አብረው የሚሰሩ ተቋማትን አመስግነዋል።
በመድረኩ ላይ የ“EASE” ፕሮጀክት አባል የሆኑት አቶ መንክር ግርማ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ዓላማ፣ አደረጃጀትና እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። አቶ መንክር በሰጡት ማብራሪያ፤ ፕሮጀክቱ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ቅድሚያ የሚሰጠውና ተመራጭ እንዲሆን ለማድረግ ለTVET ማኔጅመንቶች፣ በየተዋረድ ላሉ ሰራተኞችና አሰልጣኞች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በትኩረት እየሰራባቸው የሚገኙትን ዋና ዋና የስራ የሴቶች አቅም ግንባታ (Women's Capacity Building) ፣ የስርዓተ ትምህርት ዝግጅት (Curriculum Development) ፣ የዲጂታል ትምህርትና ስልጠና (Digital Education & Training) ፣ የፈጠራ የታገዘ የዲጂታል ፕላትፎርም ስልጠና (Innovative Digital Platform Training) ፣ ያካተተ ስልጠና እና የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ግንባታ (Inclusive Training & Disabilities Center Building) ተዘርዝሯል ።
ይህ የምክክር መድረክ የተዘጋጀው የኮሌጁ ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት ስለ ፕሮጀክቱ እንቅስቃሴዎች በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ፣ ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቀውን ኃላፊነት በግልጽ ለመለየትና በቀጣይ ስራዎች ላይ በጋራ ለመምከር ታስቦ እንደሆነ ታውቋል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከተሳታፊዎች፣ ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ተወካዮች፣ ከኮሌጁ አመራሮች እና ከፕሮጀክቱ አባላት ጋር ገንቢ ውይይት ተካሂዷል። የመድረኩ ተሳታፊዎች ፕሮጀክቱ ለባለድርሻ አካላት ያሳየውን ግልጸኝነትና ቁርጠኝነት ያደነቁ ሲሆን ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና አንጋፋ ኮሌጅ ለሌሎች ተቋማት በምሳሌነት እንዲቀጥል በትጋት መስራት እንደሚገባ በመግለጽ በቀጣይም ከኮሌጁ ጋር በጋራ ለመስራት ሙሉ ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 156
Attention please‼️
ሰላም ለሁላችሁም ይኹን!
📛 ከነገ ግንቦት 20 እስከ ግንቦት 23 ለአራት ቀናት፣ በሁሉም የኮሙኒኬሽን አማራጮቻችን እና በአባላቶቻችን ገፆች (ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ)
ምንም አይነት የፓርቲ እና የመንግስት ስራዎች ማስተዋወቅ፣ ፕሮጀክት መመርቅ እና የመጀመር ዜናዎች አይሰራም።
ዝም….ዝም ብሎ (በፅሞና) ማሳለፍ ይኖርብናል።
ለሁሉም በቢሮ/በተቋም/በመዋቅራችሁ/አደረጃጀት ያሉትን በጥብቅ አሳውቁ።
መልካም ምሽት!!
1 156
ለኮሌጁ የእስልምና እምነት ተከታይ ባልደረቦቻችን በሙሉ
ለ1447 ኛው ለ ኢድ- አል- አድሀ (አረፋ) በአል
እንኳን በሰላም አደረሳችሁ፣ በአሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት ይሁንላችሁ።
🕌 ===መልካም በዓል=== 🕌
1 156
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ከየተፈሪ መኮንን የቀድሞ ተማሪና የህዳሴው ግድብ ዋና ተደራዳሪ ኤክስፐርት ኢንጅነር ጌድዮን አስፋው ጋር ።
🇪🇹18/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር (አልሙናይ) አስተባባሪነት በኮሌጁ "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ በድምቀት ተካሂዷል።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት ይህ መድረክ የኮሌጁ ማህበረሰብ እውቀትና ተሞክሮ የሚለዋወጥበት ትልቅ መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል ። የተፈሪ መኮንን የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር በኮሌጁ ውስጥ በርካታ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን በተለይም ከተማሪዎች ጋር ቡድን በመፍጠር የትምህርት ልህቀትን ለማጠናከር እየተሰራ ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።በተጨማሪም አልሙናዩ የአሰልጣኞችን አቅም ማብቃትና የውጭ ልምድ እንዲያገኙ ማድረግ፣ለአሰልጣኞችም ሆነ ለሰልጣኞች በኦንላይን (በስራ ላይ) የትምህርት እድሎችን ማመቻቸት እና በወር አንድ ጊዜ ተሞክሮ ያላቸውን ምሁራን በመጋበዝ የልምድ ልውውጥ ማድረግ እንደሚገኙ ገልጸዋል ።
በማስቀጠልም ክቡር እንግዳው ካላቸው የተጣበበ የስራ ኃላፊነት ላይ ጊዜያቸውን ሰውተው በኮሌጁ በመገኘታቸው ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን የቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን መሪ እና የአልሙናይ ቪዚተርስ አዘጋጅ ፕሮፌሰር ግርማን አመስግነዋል።
በዕለቱ የተፈሪ መኮንን የቀድሞ ተማሪና የህዳሴው ግድብ ዋና ተደራዳሪ ኤክስፐርት ኢንጅነር ጌድዮን አስፋው በመገኘት ሰፊና አስተማሪ የህይወትና የስራ ልምዳቸውን አጋርተዋል።
ኢንጅነር ጌድዮን በ1957 ዓ.ም በወቅቱ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪ እንደነበሩ አስታውሰው፤ የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን በአሜሪካ ሀገር የመማር እድል ማግኘታቸውን፣ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የማስተርስ ዲግሪያቸውን በኢንፍራስትራክቸር ፕላኒንግ (Infrastructure Planning) ከጀርመን ሀገር ማግኘታቸውን አውስተዋል። የስራ ልምድ በመዘጋጃ ቤት እንደጀመሩና በምረቃቸው ወቅትም የቀድሞውን ንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለሥላሴን (ተፈሪ መኮንን) በቅርብ አግኝተው የማነጋገር እድል እንደነበራቸው በታሪክ ማስታወሻነቱ ገልጸዋል።
ኢንጅነር ጌድዮን ስለታላቁ የኢፌዴሪ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፣ ግድቡ በአሁኑ ወቅት ስላለበት ደረጃና አሰራር ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ኢንጅነር ጌድዮን አስፋው ለሰልጣኞችና ለአሰልጣኞች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ለአሁኑ ስኬታቸው መሰረት የሆኑት ቀራጭና አርአያ (ሞዴል) የነበሩ መምህራኖቻቸው መሆናቸውን በመግለጽ አስተማሪዎች ትውልድን በመቅረጽ ረገድ ያላቸው ሚና የጎላ በመሆኑ ምንጊዜም ለአስተማሪዎች ክብር መስጠት ያስፈልጋል በማለት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ሀገር ሁሉ መልካም ስም ያላቸው በመሆኑ ተተኪው ትውልድ ይህንን ታሪክ ማስቀጠል አለበት።በስልጠና አሰጣጥ ጥራትና በስነ-ምግባር ላይ ጠንክሮ መስራት ይገባል በማለት ዝንባሌን መለየትና ሀሳብን መግለጽ ሰልጣኞች ውጤታማ እንዲሆኑ ፍላጎትና ዝንባሌያቸው ሊጠና ይገባል፤ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ልምዳቸውንም ማዳበር እዳለባቸው ገልጸዋል ። ህይወት ውጣ ውረድ የበዛባት መሆኗን ተገንዝቦ መውደቅ በርትቶ ለመነሳት አቅም እንደሚፈጥር ማወቅና ጥሩ አንባቢ መሆን ያስፈልጋል በማለት አጽኖት ሰተዋል ።በመጨረሻምየዕለቱ መርሃ ግብር የኮሌጁ ማህበረሰብ ለክቡር እንግዳውና ለፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ባቀረበው ምስጋና ተጠናቋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 156
ሰላም እህት/ወንድሞች እንዴት ዋላችሁ👋
👉 የዛሬው የወርቃማው ሰኞ ማለዳ የህይወት ተሞክሮ እና እውቀት ማጋሪያ መድረክ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ነገ ማክሰኞ 18/09/2018ዓ.ም. መተላለፉ ይታወቃል።
👉 በመሆኑም ነገ ጠዋት 2:30 ጀምሮ ከውጪ በመጣ እንግዳ በሚሰጠው የእውቀት ማጋራት መድረክ ላይ እንድትገኙ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።
ኮሚኒኬሽን ቡድን
1 156
Repost from N/a
ሰላም እንዴት ናችሁ, ይሄ በካናዳና በworld bank የሚሰጥ የ 6 ወር ስልጠና ነው, ለናንተ ተጨማሪ እድል ስለሆነ, ከትምህርታችሁ ጎን ለጎን(ከሰዓት, ማታ/ቅዳሜና እሁድም ሊኖር ይችላል) ይሰጣል. ሰርተፊኬት አለው, ከስልጠና በኃላ ደሞ ሥራ ያስቀጥራሉ
ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች online ተመዝገቡሰላም እንዴት ናችሁ, ይሄ በካናዳና በworld bank የሚሰጥ የ 6 ወር ስልጠና ነው, ለናንተ ተጨማሪ እድል ስለሆነ, ከትምህርታችሁ ጎን ለጎን(ከሰዓት, ማታ/ቅዳሜና እሁድም ሊኖር ይችላል) ይሰጣል. ሰርተፊኬት አለው, ከስልጠና በኃላ ደሞ ሥራ ያስቀጥራሉ
ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች online ተመዝገቡ
1 156
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ እየሰለጠኑ የሚገኙ ተማሪዎች በሂልተን ሆቴል የመስክ ጉብኝት አደረጉ።
🇪🇹ግንቦት 14/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሆቴል እና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ ዉስጥ የዕንግዳ አቀባበል እና የመስተንግዶ ሰልጣኞች በኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን ትክክለኛ የሥራ ሁኔታ፣ የሙያ ባህሪ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥበብን በቅርበት እንዲገነዘቡ እና ለወደፊት የሙያ ህይወታቸው እራሳቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲያዘጋጁ ለማስቻል በሂልተን ሆቴል ጉብኝት አደረጉ። ።
በጉብኝቱ ወቅት የሆቴሉ ከፍተኛ ማኔጅመንት አባላት ለሰልጣኞቹ ስለ እንግዳ ተቀባይነት፣ ሆቴል አስተዳደር፣ የደንበኞች አያያዝ እና በዘርፉ ስለሚጠበቁ ከፍተኛ የስራ ስታንዳርዶች እና ስለ ሂልተን ሆቴል ሰፊ ገለጻ አድርገዋል። ሰልጣኞቹም በሆቴሉ ያሉትን የተለያዩ ክፍሎች በመጎብኘት በክፍል ውስጥ የተማሩትን ቲዮሪ ከተግባር ጋር የማገናኘት እድል አግኝተዋል።
ሂልተን ሆቴል ኃላፊዎች በሰጡት አስተያየት፣ ሆቴሉ በሰልጣኞች አቅም ግንባታ ላይ ካለው ፍላጎት አንጻር፣ በቀጣይም ከኮሌጁ ጋር በቅርበት በመስራት የቴክኒክና ሙያ ስልጠናውን ውጤታማ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው ከኮሌጁ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የሂልተን ሆቴል የሰው ሀይል ዳሬክተር አቶ መላኩ ስሜ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል ።
የሆቴሉ አመራሮችም በዕለቱ ጉብኝት ካደረጉ ስልጣኞች ዉስጥ በቀጣይ ስልጠናቸውን እየወሰዱ ስራ የሚሰሩበትን እድል ሆቴሉ እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል ።
ይህ የመስክ ጉብኝት ሰልጣኞቹ ከትምህርት ገበታ ወደ ኢንዱስትሪው ሲገቡ የሚጠብቃቸውን የስራ አካባቢ በራስ መተማመን እንዲቀላቀሉ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
የሆቴሉ አመራሮች ላደረጉልን ልዩ አቀባበልና
መስተግዶ በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋና
እናቀርባለን!!!!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 156
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአመራሮችን አቅም ለመገንባት ያለመ በኢዝ ፕሮጀክት ድጋፍ የተዘጋጀው የሊደርሺፕ ስልጠና ተጠናቀቀ ።
🇪🇹14/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየደረጃው ለሚገኙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ የሊደርሺፕ (የአመራርነት) ስልጠና ተጠናቀቀ ።
ይህ ስልጠና በኢዝ( EASE) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን ዋና ዓላማውም የተቋሙን መዋቅራዊ ብቃት ማጎልበትና የአመራሩን የአፈጻጸም አቅም በየጊዜው ማዳበር እንደሆነ ታውቋል።
በተሰጠው ስልጠና አመራሮቹ እራሳቸውን ወቅቱ ከሚጠይቀውና ከደረሰበት የዘመናዊ ሊደርሺፕ (Modern Leadership) ደረጃና ሳይንሳዊ እውቀት ጋር እራሳቸውን እንዲያበቁ ሰፊ አቅም የፈጠረ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል ።
በተጨማሪም አመራሩ ተለዋዋጭ የሆኑ ተቋማዊና አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት፣ ራሳቸውን ዘወትር ብቁና ዝግጁ እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል ።
የዚህ ስልጠና መጀመር ኮሌጁ የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ለማገዝ፣ የአሠራር ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም ተቋማዊ ውጤታማነትንና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
