cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

👳‍♀️🧕አነል ሙስሊም انا مسلم 🕋

ኢንሻአላህ አላማችን ተውሂድን ማስተማርና የዱንያን ጠፊነት የአኼራን ዘላለማዊነት ማስታወስ ነው።!!! «ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ።» #ማሳሰቢያ:– ልክ ከሆንኩ ከአላህ ነው፤ከተሳሳትኩ ከነብስያዬና ከሸይጧን ነውና ስህተቴን ጠቁሙኝ እንጂ "Leave" አትበሉ 🙏 ሀሳብ እና አስታያየት ካላቹ 👇👇👇👇👇 @mustaren68

Больше
Рекламные посты
196
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ሰዎች _ዱንያ ጠፊ ናት ይላሉ ጠፊ እንደሆነችም ያውቃሉ ግን ዘላለማዊ እንደሆነች ይገነባሉ። ➖ሞት አይቀርም ይላሉ እነደሚሞቱም ያውቃሉ። ነገር ግን እንደሚኖር ሰው ይለፋሉ። ➖የተፈጠርነው አላህን ለማገልገልና ባርነታችንም ለአላህ ነው ይላሉ ።ግን ጌታ እንደሌለው ነፃ እንደሆነ ሰው ይዝናናሉ ። ያሻርካሉ ይቀጥፋሉ። ➖አላህ መሀሪ ነው አዛኝ ነው ይላሉ ። ግን በተውባ ወደሱ አይመለሱም። ➖የአላህ ቅጣት ብርቱ ነው አያያዙም የከፋ ነው ይላሉ። ነገር ግን ቅጣቱን እንደሚፈራ ሰው አይፈሩም ። ትዕዛዙቱን ይጥሳሉ ህግጋቱንም ይደፍራሉ ። አላህ ሆይ ልባቸው ከተስተካከሉት መካከል አርገን ኢማናቸው በምላሳቸው ከሆኑት እንዳንሆን ጠብቀን ያረብ 🤲🤲🤲🤲 @analemuslem2
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
[ በኔ ላይ አንድ ሰለዋትን ያወረደ ሰው ፤ አላህ በሱ ላይ አስር ሰለዋትን ያወርድበታል። ]                 . (ሙስሊም ዘግቦታል). اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد، اللهم باعك على محمد وعلى آل محمد كما باعكت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد. ሰሉ አላ ረሱሊላህ✨✨✨ ◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈ @analemuslem2 @analemuslem2
Показать все...
✨ዱንያ የአኺራ እርሻ ናት! በግልም ሆነ በቡድን የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎችና ጥረቶች በዱንያ ውስጥ አንዳችን ሌላችንን በልጦ ለመገኘት የታለመ ከሆነ የአኺራ ምንዳ ያመልጠናል። ውድድራችን በአኺራ ላይ በሚገኝ ምንዳ እና ለአላህ በሚኖረን ቅርበት ላይ ከፍተኛውን ስፍራ ለማግኘት ከሆነ ግን የታደልን ሰዎች ነን። ✨በአኺራ ላይ ምንዳችንን ከፍ ለማድረግ ከምንጥርባቸው መንገዶች አንዱ ባለን ሀይል ተጠቅመን የሙስሊሙን ህዝብ ዱንያ ለማሳመር መትጋት ነው! በዱንያው ውስጥ የሌሎች ተላላኪና ከሌሎች ጠባቂ የሆነ ህዝብ ከአኺራው በፊት ዱንያውንም የከሰረ ህዝብ ነው! #ሼር ◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈ @analemuslem2 @analemuslem2
Показать все...
🍂በወንጀሏ መብዛት ምክንያት ወደ ዲን (ወደ አላህ) ለመመለስ ለከበዳት ነፍሰ ሁሉ ከአሏህ የተሰጠን መልካም ተስፋ!!! ۞ قُلْ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ أَسْرَفُوا۟ عَلَىٰٓ أَنفُسِهِمْ لَا تَقْنَطُوا۟ مِن رَّحْمَةِ ٱللَّهِ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ يَغْفِرُ ٱلذُّنُوبَ جَمِيعًا ۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلْغَفُورُ ٱلرَّحِيمُ በላቸው «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡ 🍂አዝ-ዙመር፣53 #ሼር ◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈ @analemuslem2 @analemuslem2
Показать все...
🌴የጀነት ስሞች 🌿 1) ጀነት 2) ዳሩ ሰላም 3) ዳሩል ኹልድ 4) ዳሩ ሙቃማህ 5) ጀነቱል መእዋ 6) ጀናት ዓድን 7) ዳሩል ሐየዋን 8) አል ፊርደውስ 9) ጀናቱ ነዒም 10) መቃሙል አሚን 11) 'መቀዓድ ሲድቅ' 12) 'ቀደመ ሲድቅ' ▒▒▒ ጀነት ▒▒▒ •የጀነት ፀጋዎቿ ያልቁብኛል ብሎ ጭንቀት ፤ እለያታለው ብሎ ስጋት የለም; ፀጋዎቿ ዘውታሪ ሞትም የለምና! ዱንያ ላይ የቱን ያክል ገንዘብ ቢኖርህ ገንዘብህ ቢትረፈረፍ ንብረትህ ቀድሞህ ይጠፋል አልያም ትተኸው ትሄዳለህ ። •በጀነት ውስጥ ልክ እንደ ዱንያ ጠላት የለም ለወደፊት ማሰብ የሚባል ነገርም የለም ፤ ሁሉ ነገር እንደፈለክ ነው; ጥላቻ የሚባል ነገርም ከልብ ላይ ይወገዳል ። • በጀነት ውስጥ ልክ እንደ ዱንያ ኑሮ እንድትሞላልኝ ብለህ ሰበብ ለማድረስ ደፋ ቀና ማለት የለም; ጀነት ውስጥ ሙሰቢቡ (አላህ) ነፍስ የምትፈልገውን ሁሉ አዘጋጅቷልና ••• —---------------------------------------------- ጌታችን ሆይ! ለጀነትህ ብቁ ባንሆንም ጀሐነምን መቋቋም አንችልምና በሰፊው እዘነትህ ጀነትህን ወፍቀን/አሚን ....... 🔗SHARE 🔗SHARE ╔════════════╗ ☪ JOIN: @analemuslem2    ☪ ☪ JOIN: @analemuslem2    ☪   ╚════════════╝
Показать все...
⭐️ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው። አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጋ መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው ። እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ" አሉት። ⭐️"ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?" እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት ⭐️ "ከሰው ሁሉ ሀብታመ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው። "ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት ⭐️"ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ለራስህ የምትወደውን ለሰዎች ውደድ" አሉት። ⭐️ "ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "በአላህ ተወከል"አሉት ⭐️ "በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸው? "ዚክር አብዛ" አሉት። ⭐️ "ከሰው ሁሉ በላጭ ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት። ⭐️"የተከበረና ቸር ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው "ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት። ⭐️"ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ እፈልጋለው?" ሲል "አንተም እነሱ የወደዱትን ውደድ" አሉት:: ⭐️"ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል "ጀናባህን በደንብ ታጥበ እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ መተናነስ መታመም አለብህ" አሉት። ⭐️ "ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸውም "አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት። ⭐️"ኢማኔ እንዲ ሞላ እፈልጋለው" ሲል "ፀባይህን አሳምር" አሉት። ⭐️"እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል "ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት። ⭐️"ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው "ሀራም አትብላ" አሉት:: ⭐️ "አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት። ⭐️"በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሼል የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው "መልካም ፀባይ መተናነስ እና በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት። ⭐️"በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሼል?" ሲል ሲጠይቃቸው "መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት ⭐️"በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው? "ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት። ⭐️ "የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ እፈልጋለው?" ሲል "ሰውን አትበድል" አሉት ⭐️"የቂያማ እለት አላህ እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?" "ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት። 〰 "የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው "በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት። ⭐️ "የቂያማ እለት ነውሬ እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል "የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት። ⭐️"የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል "በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት። አላህ ሱብሃን ወተአላህ ባወቅነው በሰማነው የምንሰራ ያድርገን 🔗SHARE 🔗SHARE ╔════════════╗ ☪ JOIN: @analemuslem2    ☪ ☪ JOIN: @analemuslem2    ☪   ╚════════════╝
Показать все...
ለፈገግታ😂 «ስንት ተምች አለ መሰለህ¡ አንዱ ገጠሬ ነው አሉ። ህዝቦቹ ተሰብስበው ሙሐደራ ካላደረክልን አሉት። ሚምበር ላይ ወጥቶ √ "አዩሃ ናስ! ስለ ምን እንደ ምነግራችሁ ታውቃላችሁ ኣ❓" ሲላቸው "አናውቅም" አሉት። "እንግዲያውስ ለማያውቁ ሰዎች ማስተማር ድካም ነው።" ብሎ ወረደ! በሌላም ቀን መጥተው "እሺ ዛሬ አስተምረን" አሉት። አሁንም ሚምበር ላይ ወጥቶ √ "አዩሃ ናስ! ስለ ምን እንደ ምነግራችሁ ታውቃላችሁ ኣ❓" ሲላቸው በአንድ ድምፅ "አዎን! እናውቃለን" አሉት። "እንግዲያውስ ለሚያውቅ ሰው መናገር ፋይዳ የለውም።" ብሎ ወረደ። ለሶስተኛ ጊዜ መጥተው "እባክህ አስተምረን" አሉት። አሁንም ሚምበሯ ላይ ወጥቶ √ "አዩሃ ናስ! ስለ ምን እንደ ምነግራችሁ ታውቃላችሁ ኣ❓" ሲላቸው ቀድመው ተወያይተው ነበርና ግማሻቸው "አዎን" ሲሉ ግማሻቸው "አናውቅም" አሉ። "እንግዲያውስ ያወቁት ለማያቁት ያሳውቁ!" ብሏቸው እርፍ!!»😂😂 #ሼር ◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈ @analemuslem2 @analemuslem2
Показать все...
አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ!! አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ!! አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን ትተህ ከእስልምና ምን ቀረህ? ሶላት የኢስላም ምሰሶ ፤ የኢማን መገለጫ -ካባ- መሆኑን አታውቅምን!? አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! አንተ ስትቀር ሁሉም ፍጥረታት ለጌታቸው ሰጋጆች ናቸው። አላህ እንዲህ ብሏል፡- “በሰማያት ያለው ሁሉ፤ በምድርም ያለው ሁሉ፤ ፀሀይና፣ ጨረቃም፣ ከዋክብትም፣ ተራሮችም፣ ዛፎችም፣ ተንቀሳቃሶችም፣ ከሰዎች ብዙዎችም ለአላህ የሚሰግዱ መሆናቸውን አታውቅምን!? ብዙዎችም ቅጣት ተገባቸው። አላህ የሚያዋርደው ሰው ለርሹ ምንም አክባሪ የለውም፤ አላህ የሻውን ይሰራልና።” አንተም የማትሰግድ ከሆነ ከነዚያ ቅጣት ከተወሰነባቸው አንዱ ትሆነናለህ።አ ንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን መተው ክህደትና (በአላህ ላይ) ማጋራት መሆኑን አታውቅምን!? ነቢዩ < አንዲህ ብለዋል፡- ÂŤ ﺑﻴﻦ ﺍﻟﺮﺟﻞ ﻭﺑﻴﻦ ﺍﻟﺸﺮﻙ ﻭﺍﻟﻜﻔﺮ ﺗﺮﻙ ﺍﻟﺼﻼﺓ ‏» ‏[ﺭﻭﺍﻩ ﺴ] «በሰውየውና በሽርክ ወይም በክህደት መሀል (ያለው) ሶላትን መተው ነው።” ÂŤ ﺍﻟﻌﻬﺪ ﺍﻟﺬﻱ ﺑﻴﻨﻨﺎ ﻭﺑﻴﻨﻬﻢ ﺍﻟﺼﻼﺓ : ﻓﻤﻦ ﺗﺮﻛﻬﺎ ﻓﻘﺪ ﻛﻔﺮ ‏» ‏[ﺃﺧﺮﺟﻪ ﺃﺣﺪ ﻭﺍﻟﺘﺮﻣﺬﻱ ﺝﺤﺤ ﺍﻷﻟﺒﺎﻧﻲ ]. “በኛና በነሱ (በካህዲያን) መሀል ያለው ቃል-ኪዳን (ድንበር) ሶላትን መተው ነው። (ሶላትን) የተወ በእርግጥ ካደ።” አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን መተው እንዲሁም (ከሶላት) መዘናጋት ሙናፊቅነት መሆኑን አታውቅም!? አላህ እንዲህ ብሏል፡- ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ : ٥٤٢ “ሙናፊቆች አላህን ሊያታልሉ ይፈልጋሉ፤ እሱ አታላያቸው ሲሆን። ወደ ሶላት ሲቆሙ እየሰለቹ፣ ለሰዎች የሚያሳዩ ሆነው ይቆማሉ። አላህንም ጥቂትን እንጂ አያወሱም።” ነቢዩም < ይህን ማስተላለፋቸው ተዘግቧል። ÂŤ ﺃﺛﻘﻞ ﺍﻟﺼﻼﺓ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻘﻴﻦ ﺻﻼﺓ ﺍﻟﻌﺸﺎﺀ ﻭﺻﻼﺓ ﺍﻟﻔﺠﺮ، ﻭﻟﻮ ﻳﻌﻠﻤﻮﻥ ﻣﺎ ﻓﻴﻬﻤﺎ ﻷﺗﻮﻫﻤﺎ ﻭﻟﻮ ﺣﺒﻮًﺍ‏» ‏[ﻣﺘﻔﻖ ﻋﻠﻴﻪ ]. “በሙናፊቆች ላይ እጅግ የሚከብደው ሶላት ኢሻዕ እና ሱብሂ ነው። (ሁለቱን በመስገድ) የሚገኘውን ምንዳ ቢያውቁ ኖሮ እየዳሁም ቢሆን (ወደ መስጊድ) ይመጡ ነበር።” አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! እስቲ አስተንትን ሙናፊቆች ለይዩልኝ (ሪያዕ) ቢሆንም እንኳ ይሰግዳሉ፤ አንተ ግን በፍጹም አትሰግድም!! አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ፡- ሶላትን መተው ዝንጉነት እና የልብ መድረቅ መሆኑን አታውቅምን!? ነቢዩ < እንዲህ ብለዋል፡- ÂŤ ﻟﻴﻨﺘﻬﻴﻦ ﺃﻗﻮﺍﻡ ﻋﻦ ﻭﺩﻋﻬﻢ ﺍﻟﺠﻤﻌﺎﺕ، ﺃ ﻟﻴﺨﺘﻤﻦ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻰ ﻗﻠﻮﺑﻬﻢ، ﺛﻢ ﻟﻴﻜﻮﻧﻦ  ﺍﻟﻐﺎﻓﻠﻴﻦ ‏» ‏[ﺭﻭﺍﻩ ﺴ ]. “ህዝቦች የጁምዓ ሶላትን ከመተው ይከልከሉ! ወይም አላህ በልቦቻቸው ላይ ያሽግባቸዋል። ከዚያም ከዝንጉዎች ይሆናሉ።” አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ፡- ሶላትን መተው ስራን ሁሉ እንደሚያበላሽ አልሰማሐሃምን!? የሚከተለውን የነቢዩን < ንግግር ተመልከት። ÂŤ  ﺗﺮﻙ ﺻﻼﺓ ﺍﻟﻌﺼﺮ ﺣﺒﻂ ﻋﻤﻠﻪ ‏» ‏[ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ]. “የአስርን ሶላት የተወ ስራው በርግጥ ተበላሸበት።” አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን መተው ከከሀዲያንና ወንጀለኞች ጋር ለእሳት ቅጣት እንደሚዳርግ አታውቅምን!? የጀነት ሰዎች የጀሀነም ሰዎችን (ጀሀነም የገቡበትን ምክንያት) ሲጠይቋቸው የሚሰጧቸውን ምላሽ ሲናገር አላህ እንዲህ ይላል፡- “ሰቀር (የገሀነም ጉድጓድ) ውስጥ ምን አስገባችሁ? (እነሱም) ይላሉ፡- ከሰጋጆች አልነበርንም…።” እንዲሁም በሌላ ምዕራፍ፡- “ከነሱም በኋላ ሶላትን ያጔደሉ፣ ስሜታቸውንም የተከተሉ ምትኮች ተተኩ። ለወደፊት ገይን (የገሀነም ሸለቆ) ይገባሉ።” አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን በመተውህ ከባድ መዓት (ጥፋት) ያረፈብህ መሆኑን አታውቅምን!? ነቢዩ < እንዲህ ብለዋል፡- ÂŤ ﺍﻟﺬﻱ ﺗﻔﻮﺗﻪ ﺻﻼﺓ ﺍﻟﻌﺼﺮ، ﻓﻜﺄﻧﻤﺎ ﻭﺗﺮ ﺃ ﻭﻣﺎﻟﻪ‏» ‏[ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ] “የአስር ሶላት ያመለጠው ቤተሰቦቹንና ንብረቱን እንደ አጣ (እንደ ተነጠቀ) ነው።” የአምስቱንም ወቅት ሶላት መተውህስ ምን ያስከትል ይሆን!? አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ሶላትን መተው መረበሽን፣ አለመረጋጋትን፣ ጭንቀትን፤ የኑሮ ጥበትን (እንደሚያመጣ) አታውቅምን!? አላህ እንዲህ ይላል፡- «ከግሳጼዬ የዞረ፤ የጥበት ህይወት አለለት፤ የትንሳኤም ቀን እውር ሆኖ እንቀሰቅሰዋለን። ጌታይ ሆይ ለምን እውር አድርገህ ቀሰቀስከኝ? በርግጥ አይናማ የነበርኩ ስሆን ይላል። (ነገሩ) እንደዚሁ ነው። ተዓምራችን መጥቶልህ ሳለ እንደዘነጋኀው አንተም ዛሬ ትዘነጋለህ ይለዋል።» ዋ ንዴትህ! ዋ ፀፀትህ! አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ። እንዴት ጊዜ ያልፋል፤ እድሜህ (ያለ አግባብ) ይገባደዳል; ልብህ ከጌታህ ተጋርዶ ሳለ!? እንዴትስ በቅርቢቱ አለም (ዱንያ) ከሚገኙት ነገሮች ሁሉ ይበልጥ ጣፋጭ እና ማራኪ የሆነውን ነገር ሳትቀምስ ዱንያን ትሰናበታታለህ!? ይህም አላህን በማምለክ፣ በማውሳት፣ በማመስገን እና ለርሱም በመስገድ የሚገኝ ሲሆን። አንተ ሶላትን የተውክ ሆይ! ለሶላትህ ቀላል ስፍራ የሰጠኀው አንተ ዘንድ ታላቅ ስፍራ የሚሰጠው ምን ይሆን? ሶላቱን ያጓደ ሌሎች ስራዎቹን ይበልጥ እንደሚያጓድል አታውቅምን!? ሀሰን እንዲህ ብሏል፡- “የአደም ልጅ ሆይ! ሶላትህ አንተ ዘንድ ጥሩ ስፍራ ከሌለው ምንድን ነው አንተ ዘንድ ጥሩ ስፍራ ሊኖረው የሚችለው!?” አንተ ዝንጉ የሆንክ ሆይ! ወደ ጌታህ ተመለስ! ሶላትህን ትተህ ሞት ከመምጣቱ በፊት። አንተ ሶላትን ችላ የምትል ሆይ! • የታላቁን ሶላት ደረጃ ካወቅክ • የሰጋጆችን ቁጥር ስፍር የሌለውን ሽልማት መመልከትከቻልክ (እና) • ሶላትን የሚያጓድሉ ሰዎችን ብርቱ ቅጣት ከተገነዘብክ በኋላ አሁንስ ምላሽህ ምን ይሆን? ሶላትን በማጓደልና ችላ በማለት ትቀጥላለህን!? ሶላትን ትቶ መተኛትንና ከወቅቱ ማዘግየትን ትገፋበታለህን!? ወንድሜ ሆይ! የት አለ ከፍ ያለው ሞራልህ? የት አለ ጠንካራው ቁርጠኝነትህ? የቱ ላይ ነው ለጀነት ታጥቆ መነሳት? የት አለ የሶላትን ወቅት መጠባበቅ? (ኧረ) የት አለ ወደ ጁምዓ እና ወደ ጀምዓ ሶላት በጊዜ መሄድ? 🔗SHARE 🔗SHARE ╔════════════╗ ☪ JOIN: @analemuslem2 ☪ ☪ JOIN: @analemuslem2  ☪   ╚════════════╝
Показать все...
ከነብዩና ሙሐመድ  ባህሪያት ውስጥ ጥቂቶቹ:- 1. ክብራቸው ብለው የማይበቀሉ፤ 2. ለግላዊ ፍላጎታቸው ብለው የማይቆጡ፤ 3. እውነት ተናጋሪ፤ 4. ቃል ኪዳን አክባሪ፤ 5. ለስላሳና አመለ-ሸጋ ፤ 6. ከልጃገረድ ይበልጥ ዓይንአፋር፤ 7. ዕይታቸው ቁጥብ ፤ 8. አመለካከታቸው ማስተዋል የሆነ ፣ 9. ከአንደበታቸው ክፉ የማይወጣ ፣ 10. ክፋትን በክፋት የማይመልሱ፤ 11. የለመናቸውን ሰው ባዶ እጁን የማይመልሱ፣ 12. የማይከብዱና ሰውን የማያስበረግጉ ፤ 13. አቅራቢና ተግባቢ፣ 14 ንግግርን የማያቋርጡ ፤ 15. ጉርብትናቸውን የሚያጠብቁ ፤ 16. እንግዳቸውን የሚያከብሩ ፣ 17. መልካም መመኘት ( ተፋኡል ) የሚወዱ፤ 18. መጥፎን መጠርጠር (ተሻኡም) የሚጠሉ ፣ 19. ደካማን የሚረዱ ፣ 20. ግፍ የተዋለበትን ሰው ማገዝ የሚወዱ፣ 21. ሶሐቦቻቸውን የሚያማክሩ ፣ 22. የታመመውን ባልደረባቸውን የሚጠይቁ፤ 23. እርቆ የሄደውን የሚያፈላልጉ፤ 24.ለሞ*ተው ዱዓ የሚያደርጉ ፣ 25. እሳቸው ዘንድ ሁሉም በሐቅና በፍትህእኩል የሆነ ፣ 26. ማንንም ሰው የማያስበረግጉ፤ 27. ከድሆችና ከሚስኪኖች ጋር መቀማመጥ የሚወወዱ ፤ 28. ድሀን በድህነቱ የማያንቋሽ**ሹ፣ 29. ለንጉሥም ቢሆን የማያጎበድዱ ፣ 30. ለአላህ  ፀጋ ቢያንስም  ዋጋ የሚሰጡ ፣ 31. ምግብን አያነውሩና አቃቂር የማያወጡ ፣ 32. መልካም መዓዛ ያላቸውን ነገሮች የሚወዱ ፣ 33. ብዙ ንግግር የማያበዙ ፣ 34. ፈገግታቸውን የሚያስቀድሙ ፣ 35. አስቀድመው ሰላምታ የሚሠጡ፣ 36. በለሰላምታ የሚያነሳሱ ፣ 37. አጥ*ፊዎችን በሰዎች ፊት የማይገስፁ ፤ 38. ከተቃውሞ የራቁና ከሐሜት የፀዱ፤ 39. ከፈገግታ በስተቀር ድምፅ አውጥተው የማይስቁ ፣ 40. ችግር በገጠማቸው ግዜ ፈጥነው ለሶላት የሚነሱ ፣ 41. አላህን ሁሌም የሚያስታውሱ ታላቅ መሪ ነበሩ። ባጠቃላይ እናታችን አዒሻ (ረዓ) እንዳለችው  የነብዩ  ባሕሪ ቁርኣን ነበር። اللهم صلى وسلم على نبينا محمد ይሄ የሚነገረን ዝም ብሎ ሳይሆን እኛም ይሄንን ባህሪ እንድንላበስ ነው። ትምህርቱ ጠቃሚ ሁኖ ካገኙት ለሎችም ሟር ያድርጉ!! Tedi Beykirta 🔗SHARE 🔗SHARE ╔════════════╗ ☪ JOIN:@analemuslem2   â˜Ş ☪ JOIN:@analemuslem2   ☪   ╚════════════╝
Показать все...
بِسْمِ اللّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيْمِ السَّلاَمُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ #ማለዳ_መልዕክት • ትናንት የሞቱት ለዛሬ ጠዋት እቅድ ነበራቸው ፡፡ ዛሬ ጠዋት የሞቱት ለዛሬ ማታ እቅድ ነበራቸው ፡፡ ህይወትን ማረጋገጫ እንዳለው ሰው አትያዝ ። በአይን ብልጭታ ያህል ሁሉም ነገር ሊለወጥ ይችላል።ስለዚህ ብዙ ጊዜ ከልብህ ይቅር በል ከልብህ ውደድ ስትወድ ግን ዲንህን  ዉደድ ፡፡ አንተ እንደገና ይህን ዕድል በጭራሽ ማግኘት ላትችል ይሆናል ፡፡ @analemuslem2 @analemuslem2
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.