ሰዋስው ☘☘☘☘
Открыть в Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Больше1 161
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለበርባራ እንተ አግሀደት ሃይማኖታ። እንዘ ታርኢ ሥላሴ በመስኮት ቤታ። ኢያፍርሃ መጥባሕት ወሞሠርተ ሐጺን ኢያሕመመታ። ወሰላም ካዕበ ለዮልያና ካልዕታ። እንተ ሰቀልዋ በክልኤ አጥባታ"። ትርጉም፦ በቤቷ መስኮት የሥላሴን ምሳሌ እያሳየች ሃይማኖቷን የገለጠች ለኾነች ለበርባራ ሰላምታ ይገባል፤ ሰይፍም አላስፈራትም የብረት መጋዝም አላሳመመቻትም፤ ዳግመኛም በኹለት ጡቶቿ የሰቀሏት የርሷ ኹለተኛ ለምትኾን ለዮልያናም ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 8።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለአባ ሳሙኤል ተዓጋሢ በገድል ሊቀ ጽምዋን ወፅሙዳን መፍቀሬ አምላ፤ ዘረከበ ውዳሴ ሰላም እምኀበ መልአክ"። ትርጉም፦ ከመልአክ ዘንድ የሰላም ውዳሴን ያገኘ የአምላክ ወዳጅ የጨመቱና የአገልጋዮች መነኰሳት አለቃ፤ በተጋድሎ የጸና ለኾነ ለአባ ሳሙኤል ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ርኅራኄኪ ማርያም ቀሲፈ ሕፃን አኅደጎ። ለመልአክ ብኪ ትእዛዘ ጼጌኪ ዘበአንትጎ። እምድኅረ ተሥዕኖ ዐሪግ ለቀዊም ኀበ ይዛወጎ። ሳሙኤል ሶበ ጸለየ ደብረ ቀልሞን ዐሪጎ። ኀይለ ተአምር ዘሥዕልኪ ሰማየ መዘጎ"። ትርጉም፦ ማርያም የልጅሽን ትእዛዝ በማጒደሉ በአንቺ የተማጠነውን መልአክ ልጁን ከመቅሠፍት ከለከለው ርኅራኄሽ ወደሚገባው ቦታ ለመቆም እንዳያርግ ከተሳነው በኋላ ሳሙኤል ወደ ደብረ ቀልሞን ወጥቀቶ በጸለየ ጊዜ ከሥዕልሽ የተገኘ ተአምር ወደ ሰማይ ነጠቀው። ሊቆቹ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም በማኅሌተ ጽጌ ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ የደማስቆውም ገዥ የተጻፈለት እውነት መስሎት የቅዱስ ዮሐንስ ቀኝ እጁን ቆረጠው፡፡ አባ ዮሐንስም የተቆረጠች እጅን ይዞ ወደ የብርሃን እናቱ ወደሆነች ወደ እመቤታችን ሥዕል ሄዶ በብዙ ዕንባ እንዲህ ብሎ ለመናት፡- "እመቤቴ ሆይ! ለሥዕልሽ መስገድ እንደሚገባ በተጣላሁ ጊዜ ነው ይህ የእጄ መቆረጥ የደረሰብኝ፣ አሁንም ሁሉ ይቻልሻልና በቸርነትሽ ፈውሽኝ" ብሎ ከለመናት በኋላ ወዲያው ከባድ እንቅልፍ ጣለው፡፡ በእንቅልፉም ሳለ እመቤታችን ተገለጸችለትና እጁን እንደቀደሞው አድርጋ መለሰችለት፡፡ እርሱም በነቃ ጊዜ እጁ ድና ስላገኛት እጅግ ተደስቶ እመቤታችንን አመሰገናት፡፡
❤ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳም ሄዶ መነኰሰ፡፡ መምህሩ የሆኑት አንድ አረጋዊ አባትም "ዮሐንስ ሆይ አፍአዊት ከሆነች ትምህርትህ ምንም ምን አታድርግ ግን ዝምታን ተማር" አሉት፡፡ ዮሐንስም የመነኮሳቱን የመጸዳጃ ቤታቸውን እያጸዳና በሁሉ ነገር እያገለገላቸው በተጋድሎ ኖረ፡፡ መምህሩም አርምሞውን ፈትቶ ካገኙት ይቀጡት ነበር፡፡ እመቤታችንም አንድ ቀን ለመምህሩ ተገለጠችላቸውና ዮሐንስ ድርሳናትን እንዲደርስ ይፈቅድለት ዘንድ አዘዘችው፡፡ ዮሐንስም ከዚህ በኋላ ብዙ ድርሳናትን ደረሰ፡፡ ስለ ቀናች አንዲት ሃይማኖትና ስለተሣሉ ቅዱሳት ሥዕላት ብዙ የደከመው አባት አባ ዮሐንስ የእርጅና ዘመኑን ጨርሶ በዚህች ዕለት ታኅሣሥ8 በሰላም ዐረፏል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ በቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ያሬክላ፦ ይህም አባት ለእስክድርያ ለአገር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሦስተኛ ቊጥር ነው። የዚህም ቅዱስ አባት ወላጆቹ አስቀድሞ አረማውያን ነበሩ በወለዱትም ጊዜ የአረማውያንን ትምህርት መጻሕፍቶቻቸውንም ሁሉ አስተማሩት።
❤ ከዚህም በኋላ አምነው ተጠመቁ ይህን ልጃቸውንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት የሐዋርያትንም መጻሕፍት አጠና ሊቀ ጳጳሳት ድሜጥሮስም ዲቁና ሾመው ከዚህም በኋላ በእስክንድርያ አገር ቤተ ክርስቲያን ቅስና ሾመው መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። ሥራውንም ፈጸመ የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ ጠንቅቆ አወቀ።
❤ አባት ድሜጥሮስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት መርጠው በእስክድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በቀናች ሃይማኖት አጽንቶ ጠበቀ ከአረማውያንም ብዙዎችን ክብር ይግባውና ክርስቶን ወደ ማመን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ለቅዱስ ዲዮናስዮም ለምእመናን እንዲፈርድ ሥልጣን ሰጠው እርሱ ግን ዓላውያንን ወደ ቀናች ሃይማኖት እስከሚመልሳቸው ድረስ ያስተምራቸውና ይገሥጻቸው ነበር። በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ሦስት ዓመት ኑሮ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ያሬክላ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ8 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላክ አማልክት በጽዮን"። መዝ83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥1-17።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "እስመ ኀብአኒ ውስተ ጽላሎቱ በዕለተ ምንዳቤየ። ወሠወረኒ በምኅባአ ጽላሎቱ። ወዲበ ኰኵሕ አልዐለኒ"። መዝ 26፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 12፥1-8፣ 1ኛ ጴጥ 3፥8-15 የሐዋ ሥራ 21፥1-8። የሚነበበው ወንጌለሰ ሜቴ 11፥16-20። የሚቀደሰው ቅዳሴ የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ተክለ አልፋ የዕረፍት በዓል፣ የአቡነ እስትፋሰ ክርስቶስና የአቡነ ኪሮስ የልደት በዓልና የነቢያት (ገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችን ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ቃልኪዳንም ስለተቀበለበት በገዳሙ ውስጥ ርሀብ፣ ቸነፈርና መቅሰፍት ፈጽሞ አይገባም፡፡ "መምሕረ ንስሓ" በመባል የሚታወቁት አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን ወንጌልን በማስተማር፣ አስደናቂ ተአምራትን በማድረግ ድውያንን እየፈወሱ በብዙ ድካም ከተጋደሉ በኋላ ከጌታችን ቃልኪዳን ተቀብለው ታኅሣሥ 8 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ሳሙኤል ጸሎት ይማረን በከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ኤሲና እኅቱ ቅድስት ቴክላ፡- እነዚህም ቅዱሳን ለእስሙናይን በስተምራብ ካለው አውራጃ ብጺር ከሚባል መንደር የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ አባታቸው ኤልያስ እናታቸው ማርያም ይባላሉ፡፡ ኤሲም ዕድሜው እንደደረሰ ወላጆቹ ሊያጋቡት ሲሉ እርሱ ግን እምቢ አለ፡፡ ኤሲ እግዚአብሔርን እጅግ የሚፈራ ብዙ ሀብት የነበረው እጅግ ባለጸጋም ነበር፡፡ እጅግ የበዙ በጎች ስለነበሩት ጸጉራቸውን እየሸጠ ድኆችንና ጦም አዳሪዎችን ይረዳል፡፡ ዕድሜውም 20 በሆነ ጊዜ አባቱና እናቱ ሞቱ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ አረመኔው ዲዮቅልጥያኖስም በዚያ ዘመን ነግሦ የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ማፍሰስ ጀመረ፡፡
❤ አባ ኤሲም በእስክንድርያ አገር ጳውሎስ ከሚባለው ባልንጀራው ጋር የታሰሩትን ሰማዕታት እየጎበኟቸው ያገለግሏቸው ነበር፡፡ ሰማዕታቱም ለአባ ኤሲና ለጳውሎስ "እናንተም እንጂ ደግሞ ሰማዕት ትሆኑ ዘንድ አላችሁ" እያሉ ትንቢት ይነግሯቸው ነበር፡፡ በዚያም ወራት የንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ባለሟል የነበረውን የኅርማኖስን ልጅ ታላቁን ሰማዕት ቅዱስ ፊቅጦርን ወደ እስክንድርያ በግዞት እያሠቀዩ አመጡት፡፡ ኤሲና ጳውሎስም የቅዱስ ፊቅጦርን ጽናት አይተው መንፈሳዊ ቅናት ቀኑ፡፡ ኤሲም ወደ መኮንኑ ቀርቦ የጌታችንን ክብር መሰከረ፡፡ መኮንኑም ኤሲን ይዞ ማሠቃየት ጀመረ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ኤሲን በብረት አለንጋ ብዙ ግርፋትን ገረፉት፡፡ ህዋሳቱንም በሾተሎች ሰነጣጠቁ፡፡ በሥጋውም የችቦ መብራቶችን እያደረጉ አቃጠሉት፡፡ ዳግመኛም በሰንሰለት አሥረው በሚነድ እቶን እሳት ውስጥ ጨመሩት፡፡ ነገር ግን ወደ ጌታችን በጸለየ ጊዜ ጌታችን መልአኩን ቅዱስ ሱርያልን ላከለት፡፡ መልአኩም ለኤሲ "ጻድቅ ሰው ሆይ ሰላምታ ለአንተ ይገባሃል" አለውና እሳቱን አጠፋለት፡፡ እጁንም ይዞ ከጉደጓዱ አወጣው፡፡ አባ ኤሲም ወደ መኰንኑ ዘንድ ሄዶ "ከሃዲ ንጉሥ ሆይ አንተ ጣዖታቶችህ እፈሩ አምላኬ አድኖኛል" አለው፡፡ ሕዝቡም አባ ኤሲን ሕያው ሆኖ ባዩት ጊዜ እጅግ ተደንቀው "እኛም በአባ ኤሲ አምላክ አምነናል" ብለው መስክረው ብዙዎች ሰማዕት ሆኑ፡፡ አባ ኤሲንም አሠሩት፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ለእኅቱ ለቅድስት ቴክላ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላትና ወደ ወንድሟ እንድትሄድ ነገራት፡፡ እርሷም ከእንዴና ከተማ ተነሥታ ወደ ባሕር ዳርቻ በደረሰች ጊዜ መንፈሳዊት መርከብን አገኘች፡፡ እመቤታችንና አክስቷ አልሳቤጥም በውስጧ አሉ፡፡ ቅድስት ቴክላም "እመቤቶቼ ሆይ! የደረሰባችሁ ምንድነው/አዝናችሁ አያችኋለሁና" አለቻቸው፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም "በእርጅናዬ ወራት የወለድኩት አንድ ልጅ ነበረኝ፣ ወስደው አረዱብኝ" አለቻት፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያምም "ለእኔም አንድ ልጅ ነበረኝ፣ እርሱንም ወስደው ሰቅለው ገደሉብኝ" አላቻት፡፡ ቅድስት ቴክላም ይህንን በሰማች ጊዜ እጅግ አዝና "እመቤቶቹ ሆይ! በእውነት ጽኑ የሆነ ሀዘን አግኝቷችኋል" አለቻቸው፡፡ ይህንና የመሳሰለውንም ነገር እየተነጋገሩ ወንድሟ አባ ኤሲ ካለበት አደረሷት፡፡ የተገለጡላት ግን እነማን እንደሆኑ አላወቀችም፡፡
❤ አባ ኤሲም እኅቱን ቴክላን ባያት ጊዜ ደስ አለው፡፡ አብረው ስለጌታችን ክብር ይሞቱ ዘንድ ተስማሙ፡፡ ሌሊት በሆንም ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሱርያል አባ ኤሲን ነጥቶ ወደ ሰማይ ወሰደውና ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን አሳየው፡፡ የጻድቃንንና የሰማዕታትን መኖሪያቸውን የራሱንም መኖሪያውን አሳየው፡፡ መልአኩ "በሰማዕታት ስም የሚዘክሩ የዓለም ሰዎች ቢኖሩ በዕለተ ሞታቸው ቀን የዘከሯቸው ቅዱሳን አማልደው በዚህ የብርሃን ድንኳን አዳራሽ ውስጥ ለዘለዓለም በክብር ያኖሯቸዋል" እያለ እያንዳንዱን የቅዱሳንን የብርሃን ድንኳን ያለውን የቅዱሳንን መኖሪያ አሳየው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱሳን ሁሉ መጥተው አባ ኤሲን ሰላምታ ሰጡት፡፡
❤ መልአኩም አባ ኤሲን ሰማዕትነቱን እንዲፈጽም ከነገረው በኋላ ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም መልሶ አምጥቶ እሥር ቤቱ ውስጥ አስቀመጠውና ተመልሶ ዐረገ፡፡ በነጋም ጊዜ መኮንኑ አባ ኤሲንና እኅቱን ቅድስት ቴክላን ከእሥር ቤት አውጥተው ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃዩአቸው፡፡ በተሸከርካሪዎች መሣሪያ፣ በብረት ቃጠሎ፣ በችንካሮች በመቸንከር የራሳቸውንም ቆዳ በመግፈፍ ብዙ አሠቃዩአቸው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ከሕመማቸው ሁሉ ፈወሳቸው፡፡ መኮንኑም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ወደላይኛው ግብጽ ይወስዳቸውና ያሠቃያቸው ዘንድ ለእንዴናው አገር መኮንን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ 8 ቀን ያህል እንደተጓዙም መርከቧ ቆመች፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ የአባ ኤሲንና የቅድስት ቴክላን ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ እነርሱም በዚህ ደስ ተሰኝተው ጸሎታቸውን ከፈጸሙ በኋላ አንገታቸውን አሳልፈው ለሰያፊዎቻቸው ሰጧቸውና በየተራ ቆረጧቸው፡፡ ሰማዕትነታቸውንም በዚሁ ፈጽመው የክብርን አክሊል ተቀዳጁ፡፡ እግዚአብሔርም ስንሑፍ ከሚባል አገር ስሙ ኦሪ የሚባለውን ቄስ የቅዱሳንን ሥጋቸውን እንዲያነሣ አዘዘው፡፡ እርሱም መጥቶ በክብር ወስዶ የመከራው ዘመን እስኪያልፍ በንጹሕ ቦታ አኖራቸው፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ከእነርሱም ጋር አብረው ተሰይፈው የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ ቅዱሳን 477 ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ዮሐንስ ዘሀገረ ደማስቆ፡- ይኽም ቅዱስ ከደማስቆ ከከበርቴዎቿና ከታላላቆቿ ወገን ከሆነው መንሱር ከሚባለው ሰው የተወለደ በጥበብና በፈሪሃ እግዚአብሔር ያደገ ነው፡፡ የቀርሊ ፈላስፋ ከሆነው ቁልፋህ ከሚባል መነኩሴ ቁልዝማቂ መምህሩ ዘንድ የፍልስፍና ትምህርትን ተማረ፡፡ ትምህርቱንም ሲጨርስ ቁልዝማዊ መምህሩን ተሰናብቶ ወደ ከበረ ሊቅ ሳበ ሰማዕት ገዳም ሄደ፡፡ አባቱም በሞተ ጊዜ ለአገረ ገዥው ጸሐፊ ሆነ፡፡
❤ በዚያም ወራት የከሃዲው ልዩን ልጅ ቆስጠንጢኖስ ተነሥቶ በአምላክ ፈቃድ ስለተሣሉ ቅዱሳት ሥዕላት ጸብ በማንሣት አብያተ ክርስቲያናትን የሚያውክ ሆነ፡፡ ይህም አባ ዮሐንስ የቤተ ክርስቲያን ሹመት ሳይኖረው በቀናች ሃይማኖት እያጸናቸው በአምላክ ፈቃድ ለተሣሉ ሥዕላት ስግደት እንደሚገባ ምስክር ከቅዱሳት መጻሕፍት እያመጣ የሚጽፍ ሆነና ወደ ምእመናን ሁሉ የሚልክ ሆነ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም ይህንን በሰማ ጊዜ ጥርሱን እያፋጨ በዮሐንስ ብዕር አምሳል የሚጽፍ ጸሐፊ ፈልጎ አመጣና ዮሐንስ እንደጻፈው አድርጎ እንዲህ ብሎ ጻፈ፡- "ከአንተ ዘንድ ያለው ዮሐንስ ከአንተ ጋር ተዋግቼ አገርህን እማርክ ዘንድ ይህን ደብዳቤ ጽፎ ላከልኝ" ብሎ በወንጀል ለደማስቆው ገዥ ላከለት፡፡
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፰ (8) ቀን
❤ እንኳን መልአከ እግዚአብሔር እስከ ማማለድ ስልጣን ለተሰጠው ለደብረ ቀልሞን ለአባ ሳሙኤል ለዕረፍት በዓል፣ የከበሩ ሴቶች ለቅዱሳን በርባራና ዮልያና ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለእስሙናይን በስተምዕራብ ካለ አውራጃ ብጺር ከሚባል መንደር ለሆኑ ለቅዱሳን ለአባ ኤሲና ለእኅቱ ቴክላ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓላቸው፣ ለእስክንድር አገር ዐሥራ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ ለአባ ያሬክላና ለተመሰገነ ለአባ ዮሐንስ ዘአገረ ደማስቆ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ የከበሩ ሴቶች ቅዱሳን በርባራና ዮልያና፦ ይችም ቅድስት በርባራ በከሀዲው መክስምያኖስ ዘመን ታላቅ መስፍን ለሆነ ሰው ልጁ ናት ስሙም ዲዮስቆሮስ ነው እርሱም ለልጁ ለበርባራ ማንም እንዳያያት ታላቅ ጽኑ የሆነ ሕንፃ አሠራ ከዚህም ዳግመኛ መታጠቢያ የውሽባ ቤት በግንብ ሠራ የሚከፈቱ ሁለት መስኮቶችንም በውስጡ እንዲሠሩ አዘዘ። ቅድስት በርባራም ሁለቱን መስኮቶች በአየች ጊዜ ሦስት መስኮትን እንዲሠሩ ሐናፂዎችን አዘዘቻቸው ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝ የሆነ የመስቀሉን ምልክት በውኃ መታጠቢያው ላይ አሠራች።
❤ አባቷም ወደዚህ ሕንፃ በገባ ጊዜ ይህን ልጁ ያሠራችውን አይቶ አናፂዎችን ጠየቀ እነርሱም "ይህን እንድንሠራ ልጅህ አዘዘችን" አሉት እርሷንም ጠርቶ "ለምን እንዲህ አደረግሽ" አላት። እርሷም "አባቴ ሆይ አስተውል ልዩ ሦስት በሆነ በሥላሴ ስም ሥራ ሁሉ ይፈጸማልና ስለዚህ ሦስተኛ መስኮት አሠራሁ ይህም መስቀል ዓለሙ ሁሉ በእርሱ በዳነበት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አምሳል ነው አንተም አባቴ ሆይ ከስሕተትህ ተመለስህ የፈጠረህን አምላክ አምልከው" አለችው። አባቷም ከእርሷ ይህን በሰማ ጊዜ ሰይፋን መዝዞ በኋላዋ ሮጠ እርሷም ሸሸች በፊቷም የነበረች ዐለት ተሠንጥቃ በውስጧ ገብታ ሠወረቻት።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ አባቷ ተመለሰች እርሱም እንዲአሠቀሠያት ለሌላ መኰንን አሳልፎ ሰጣት እርሱም ታላቅ ሥቃይን አሠቃያት በዚያም ዮልያና የምትባል ሴት ነበረች ቅድስት በርበሠራንም አየቻትና የምታጽናናትና የምታረጋጋት ሆነች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅድስት በርባራ ተገለጸላትና አረጋጋት።
❤ ከዚህም በኋላ አባቷ በሰይፍ ራሷን እንዲቆርጡ የባልንጀራዋ የዮልያና ራስ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ። በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እሳት ወርዶ አባቷንና ጓደኛው የሆነ መኰንን መርትያኖስን አቃጠላቸው ያም በውሽባ ቤት ውስጠሰ በመስቀል ምልክት ያሠራቸው መታጠቢያ ለታመመ ሁሉ ከእርሱ በታጠበ ጊዜ የሚያድን በውስጡ ታላቅ ፈውስ ያለበት ሆነ።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱሳን ሰማዕታትን ሥጋቸውን ወስደው ከከተማ ውጭ ባለች ቤተ ክርስቲያን ስሟ ገላልያ በሚባል ቦታ አኖሩአቸው ይህ ሥጋቸውም በቅዱሳን ሰማዕታት በአቡቂርና በዮሐንስ በምስር አገር በአለ ቤተ ክርስቲያናቸው እስከ ዛሬ አለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳት ሰማዕታት በርባራና ዮልያና ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
❤ አባቷም ወደዚህ ሕንፃ በገባ ጊዜ ይህን ልጁ ያሠራችውን አይቶ አናፂዎችን ጠየቀ እነርሱም "ይህን እንድንሠራ ልጅህ አዘዘችን" አሉት እርሷንም ጠርቶ "ለምን እንዲህ አደረግሽ" አላት። እርሷም "አባቴ ሆይ አስተውል ልዩ ሦስት በሆነ በሥላሴ ስም ሥራ ሁሉ ይፈጸማልና ስለዚህ ሦስተኛ መስኮት አሠራሁ ይህም መስቀል ዓለሙ ሁሉ በእርሱ በዳነበት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አምሳል ነወሰ አንተም አባቴ ሆይ ከስሕተትህ ተመለስህ የፈጠረህን አምላክ አምልከው" አለችው። አባቷም ከእርሷ ይህን በሰማ ጊዜ ሰይፋን መዝዞ በኋላዋ ሮጠ እርሷም ሸሸች በፊቷም የነበረች ዐለት ተሠንጥቃ በውስጧ ገብታ ሠወረቻት።
+ + +
❤ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን፡- የትውልድ ሀገራቸው ደቡባዊ ግብፅ ሲሆን በ14 ዓመታቸው ነው አስቄጥስ ገዳም ገብተው የመነኮሱት፡፡ በመነኰሱበት ዕለትም መልአክ ከጎናቸው ቆሞ ታይቷል፡፡ ታላቁ አባት አባ አጋቶን ካረፉ በኋላ ገዳመ አስቄጥስን ያስተዳደሩት አቡነ ሳሙኤል ናቸው፡፡ በዓለም ታሪክ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁለት በተከፈለችበትና "የውሾች ጉባኤ" በተባለው በ451 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ላይ የእነ ልዮን የክህደት ቃለ ጉባኤ ለአቡነ ሳሙኤል ተልኮላቸው ነበር፡፡ እሳቸውም ቃለ ጉባኤውን ተቀብለው መነኰሳቱን ሰብስበው እያሳዩአቸው በእሳት አቃጥለውታል፡፡ በዚህም ጊዜ በገዳሙ ለ14 ቀን ያህል ቀስተ ደመናና ብርሃን ወርዶ ታይቷል፡፡ ልዮንም ይህንን ሲሰማ ለንጉሡ በመንገር አቡነ ሳሙኤልን ሊያስገድላቸው ሲል እመቤታችን ለአቡነ ሳሙኤል ተልጻላቸው ወደ ደብረ ቀልሞን እንዲሄዱ ነገረቻቸው፡፡ እሳቸውም ተነስተው ደብረ ቀልሞን ገቡ፡፡ በገዳሙ በአበምኔትነት ተሹመው ማገልገል ጀመሩ፡፡
❤ አቡነ ሳሙኤል በዚሁ ዘደብረ ቀልሞን ገዳም የእግዚአብሔርን መልአክ አማልደው መልአኩን ምሕረት ያሰጡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መልአኩ የታዘዘውን ባለመፈጸሙ ኃይሉን አጥቶ በምድር ወድቆ ቀርቶ ነበር፡፡ ሁለት ልጆች በገዳሙ ውስጥ ሆነው በቅዳሴ ጊዜ ሲሮጡና ሲዘፍኑ መልአኩ ሁለቱንም ልጆች በሞት እንዲቀስፋቸው ተላከ፡፡ ከልጆቹም አንደኛው መልኩ እጅግ የተዋበ ድምፁም ያማረ ስለነበር መልአኩ አሳዝኖት "አንተንስ የፈጠረህ ይቅሰፍህ?" ብሎ ተወውና በማዳላት ሌላኛውን መልኩም ድምፁም የማያምረውን ልጅ ብቻ ቀስፎ ሊያርግ ሲል ኃይሉን ተነጥቆ በመሬት ላይ ወደቆ ቀረ፡፡ ሄዶም ከቤተልሔሙ በራፍ ላይ ወደቀ፡፡ በቀጣዩ ቀን ዲያቆኑ ለተልእኮ ሲሄድ እዚያ ወድቆ ቢያየው እጅግ ደንግጦ "ሰማያዊ ነህ ወይስ ምድራዊ? ከዚህስ ምን ትሠራለህ?" አለው፡፡ መልአኩም "በአፈጣጠሬስ ሰማያዊ ነበርኩ ነገር ግን ምግባሬ ምድራዊ አድርጎኛል" አለው፡፡ መልአኩም በመቀጠል "እባክህ ሄደህ አባ ሳሙኤልን ከበዓቱ ጥራልኝ" አለው፡፡ ዲያቆኑም አቡነ ሳሙኤልን ጠርቶለት አቡነ ሳሙኤል መጡና በሐዘን ውስጥ ሆነው "ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ?" አሉት፡፡ መልአኩም "አማልደኝ" አላቸው፡፡
❤ አቡነ ሳሙኤልም በእመቤታችን ሥዕል ሥር ሄደው እመቤታችንን እያለቀሱ በመጸለይ ተማጸኗት፡፡ እመቤታችንም ተገለጠችላቸውና "ሕዝቡን ሁሉ ሰብስበህ 41 እግዚኦታና 41 በእንተ ማርያም አድርሰህ ክንፍና ክንፉን ይዘህ ተንስዕ በስሙ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወበስማ ለእግዝእትነ ማርያም ብለህ አንሳው" አለቻቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤልም እመቤታችን እንደነገረቻቸው አደረጉለትና መልአኩ ኃይሉ ተመለሰለት፡፡ ወዲያውም በማዳላት ሳይቀስፈው የቀረውን ልጅ ቀስፎ ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ያም መልአክ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከደብረ ቀልሞን ገዳም በረድኤት ተለይቶ አያውቅም፡፡
1 161
ተሾሙ።
❤ እመቤታችን ማርያምም ለብፁዓዊ ሙሴ ልፋፈ ጽድቅ፣ ሰኔ ጎልጎታን፣ ባርቶስና ራዕየ ማርያምን ሰታቸዋለች። ወገባቸውን ከጠጉር በተሰራ መታጠቂያ ይታጠቁ ነበር። አቡነ ዘበሰማያትም በጀመሩ ጊዜ ሰባቱ ሰማያት ተከፍተውላቸው ከአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ጀምሮ ሁሉንም ቅዱሳን በግልጥ ያያሉ። ሲሰግዱ እንባቸው ደረታቸውና እግራቸውን እያራሰ በመሬት ይፈሳል። በዓለም ብዙ የዋሻ ቤተ ክርስቲን አንጸዋል። የሕንፃ ሥራ ከመደመራቸው በፊት 40ቀን ይጾማሉ። ሁለቱ መላእክት ቅዱስ ፍርክኤልና ቅዱስ ፍናኤል እየረዷቸው መቅደስን ያንጻሉ። የዋሻ ቤተ መቅደስ ስራ ጎን ለጎን መስቀልና ሌሎች ንዋየ ቅዱሳት ይሰራሉ። የሚሰሯቸው መቅደሶች ከፊሉ የሚታዩ ምዕመናን የሚገለገሉባቸው ሲሆን የቀሩት የማይታዩ ስውራን የሚገለገሉበት ነው።
❤ አቡነ ሙሴ ጵጵስና የተሾሙት በ12ቱ ሐዋርያት በአንድነት ነው። ዘመናቸውን ሁሉ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በመሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስን መንበር አጥነዋል። በድንግልናቸው በንጽሕናቸው የከበሩ 12ክንፍ የተጎናጸፉ ናቸው። ጥቂቶች ለማየት የታደሉትን ብሔረ ብፁዓን ሄደው አይተዋል።
❤ አቡነ ሙሴ በግብፅና በእስራኤል መካከል ሲካር በሚባል ቦታ ካገለገሉ በኋላ ጣዖታትን ለማሳፈር ወደ መቄዶንያ ሄደው ጣዖት አምላኪውን ንጉሥ ገሰጹት። ንጉሥ ተቆጥቶ አጥንታቸው እስኪሰበር ድረስ በብረት አስደብድቦ በብረት አልጋ ላይ አስተኝቶ እሳት አነደደባቸው። ቅዱስ ሚካኤልና ገብርኤል ግን ዳሰው ፈወሷቸው። በማግስቱ ወደ ፍርድ አደባባይ ቢወስዷቸው ምንም እንዳልሆኑ ንጉሡ በማየቱ በንዴት ሰውነታቸውን በሰይፍ አስቆራረጠ። ከሰውነታቸው ደም፣ ውሃ፣ ወተትና መዓር ወጣ። ጌታችንም አድኗቸው በስምህ የተማፀነውን መልካም ነገር አደርግታለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገባላቸው።
❤ በግብፅ አንስጣስዮስ ቴዎዶስዮስ ተብለው ሲነግሱ መላእክት የአባቱ የዳዊት መንግሥት ቅባት ቀቧቸው፤ የመንግሥት ልብስ አለበሷቸው፤ የመንግሥት ሥርዓትን ሁሉ ሰጧቸው። የጣዖታትን ቤት አፍርሱ ቤተ ክርስቲያንን ሥሩ በማለት ኅዳር12 አዋጅ ነጋሪን ላኩ። ጌታችን በግብፅ ተሶዶ ሳለ ለአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የተናገረው ትንቢት ተፈፀመ "ከልጅህ የሚወለድ በግብፅ ያሉትን ጣዖቶች አፍርሶ ሃይማኖትን ያጸናል" ብሎ ነበር። እዲሁም ቅድስት አርሴማ ሳትወለድ በስሟ የተሰየመውን ታቦት በግብፅ ያገኙና ያከበሩ ናቸው (ገድለ አርሴማ 7ኛ ተዓምር)።
❤ በግብፅ ደብረ ምጥማቅ ማርያም በመጀመሪያ ሰርተው የቀደሱት አቡነ ሙሴ ናቸው። በተጨማሪ ብዙ የህንጻ ቤተ ክረስቲያንና የዋሻ ቤተ ክረስቲያን አንጸዋል። እንደ ቅዱሳን ብዙ ድንቅ ተዓምር አድርገዋል። ለምሳሌ አውሬ ገድሏቸው ተጠራቅሞ የነበረ አፅም ላይ ጸልየው አራት ሺህ የሞቱ ሰዎችን ከሞት አስነስዋል። 40ዓመት በንግሥና ከቆዩ በኋላ ከብዙ ተከታዮቻቸው ጋር ወደ አስቄጥስ ገዳም በደመና ስጓዙ በበረሃው ተርበው ለወደቁት ወደ እግዚአብሔር ሲጸልዩ መና ወርዶላቸው መግበዋል አስቄጥስ ገዳም ሲደርሶ አቡነ መቃርስ ነበሩ የተቀበሏቸው፡፡ አቡነ ሙሴ በአስቄጥስ በአቡነ እንጦንስ ስም የመጀመርያውን ቤተ ክርስቲያን ሰርተው ከፈፀሙ በኋላ አቡነ እንጦንስንና አቡነ መቃርስ በምንኵስና ልብስ፣ በመላእክት አስኬማ፣ በቅንዓት፣ በቀሚስና በቆብዕ ላይ ለ40ቀን ጸልየው ጥር22 ተክለማርያም ብለው ሰይመው አመነኰሷቸው። በዚያውም አቡነ መቃርስ ከበታቻቸው ብፁዓዊ ሙሴን ሾሙ። በአስቄጥስ ብዙ ተከታዮቻቸውን አመንኵሰው ቀድሞ ወደ ሰሯቸው ቤተ መቅደሶች ይልኳቸው ነበር። የቀሩት ደግሞ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አብረዋቸው መጥተዋል።
❤ የኢትዮጵያ የመጀመርያው ጳጳስ አቡነ ሰላማ በማረፋቸው ሁለቱ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ ጳጳስ እንዲልኩላቸው ከእጅ መንሻ ጋር ወደ ግብፅ ላኩ። አቡነ አትናቴዎስ ፈቃደ እግዚአብሔር ጠይቀው አቡነ ሙሴ ከአስቄጥስ ገዳም ለኢትዮጵያውያን አባት እዲሆኑ አቡነ ሚናስ ብለው ሾሙ። ከሦስት ሺህ ልጆቻቸው ጋር ሆነው ብዙ ቅርስ ይዘው አባታችን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ሕዝቡ በደስታ ተቀበሏቸው። ብዙ መጽሐፍትን ከአረብኛ ወደ ግእዝ ቋንቋ ተርጉመው ጽፈዋል። ይጽፉበት የነበረው ብዕር አድሮ በማግስቱ ለምልሞ አብቦ ይገኛል። ቀለም ይበጠብጡበት የነበረው የቀንድ ዋንጫም ከመሬት ተጣብቆ ያገኙት ነበር። በእጃቸው ሲያላቅቁት ከመሬት ጠበል ይፈልቃል፣ በጠበሉም ህሙማንን ፈውሰውበታል።
❤ በኢትዮጵያ አምስት መቶ የዋሻ ቤተ ክስቲያን ያነጹ ሲሆን በአጠቃላይ በመላው ዓለም ከዐሥር ሺህ በላይ ቤተ ክርስቲያ ሰርተዋል፣ አንጸዋል (መለከት መጽሔት 2007 ዓ.ም)። በእንቁና በእብነ በረድ ከሰራቸው ቤተ ክርስቲያኖች መካከል በአራራት ደብር (ከምድር ጥፋት በኋላ የኖኅ መርከብ መጀመርያ ያረፈችበት) በጻድቁ ኖኅ ስም፣ አብርሃም ሥላሴን በድንኳኑ ባስተናገደበት ስፍራ በቅድስት ሥላሴ ስም፣ በሕንድ (በሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ መቃብር ቦታ) በቅዱስ ቶማስ ስም፣ በአርማንያና በፋርስ (በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋውን ባሳረፉበት ቦታ) በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም።
❤ በኢትዮጵያ በአቡነ ሙሴ ከታነጹት ቤተ ክርስቲያ ውስጥ የተወሰኑት፦
1.የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም (ባለ ሰባት መቅደስ ፎቅ)፣ የረፍታቸው ቦታ፣ በትረ ሙሴያቸውና የእጅ መስቀላቸው ያለበት (ሰሜን ወሎ ዳውንት)
2.ደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ላይ በምሥራቅ በኩል ስውር ቤተ መቅደስ (ድርሳነ፡ራጉኤል)
3.አእማድ ቅድስት ሥላሴ ገዳም (መቄት) እንደ አቡነ አሮን መንክራዊ ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማይገባው፣
❤ በመጨረሻ ብጹዕ አቡነ ሙሴ በቤተ ሚናስ ቤተ መቅደስ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ ገዳም መሰከረም4 በዕለተ እሁድ አረፋ። ወርሃዊ በዓላቸው ወር በገባ በ4 ነው። በተለይ ጋብቻን ሚቀድሱ፣ ክህነት የሚባርኩ፣ መናንያንን የሚያጸኑ አረጋዊን አባት ናቸው። ከአባታች አቡነ ሙሴ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም ያሳተመው መጽሔት።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፰ (8) ቀን
❤ እንኳን ለኢትዮጵያኑ ጻድቃን ለደብረ ድማሕ(ዲማ) ገዳም አበምኔት በፊትም በኋላም የሚያዩ ለሆኑ ለታላቁ አባት ለአቡነ ለተክለ አልፋ ለዕረፍት በዓል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ማልኝ ብለው በአባይ ወንዝ ውስጥ ለዘጠኝ ዓመት ለጸለዩ ለአቡነ እስትፋሰ ክርስቶስ ለልደት በዓል፣ በክርስቶስ ለሚታመንየሰማዕታትንና የጻድቃንን በየዕረፍታቸው ቀን ለእያንዳንዳቸው ርኁባንን በማጥገብ የተራቆቱትን በማልበስ መታሰቢያቸውን ለሚያደርግ ለነበረ ለቅዱስ ገብረ ማርያምና፣ለታላቁ አባት ለአቡነ ኪሮስና ከግብጽ ለኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ተሾመው ለመጡ በኢትዮጵያ ብዙ የዋሻ ቤተ ክርስቲያንን ላነጹ ለብጹዓዊ ለአቡነ ሙሴ ዘድባ ለልደታቸው በዓል ለልደት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ ስለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ልደት፦ (የተወለዱበት) ቦታ ዳውንት ፀወን ዓባይ ይባላል። በአካባቢውም በገዳሙ አንፃር በሰሜን በኩል የእናታቸው አገር ደብረ ድባ የቄርሎስ ቦታ ይባላል የአባታቸውም አገር የእግዚአብሔር አብ ደብር አጠገብ ዳውንት ወይም ደብረ አስጋጅ ይባላል።
❤ አባታቸው ስም ቅዱስ መልአከ ምክሩ ሲሆን የእናታቸው ስም ቅድስት ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ደጋጎች እግዚአብሔር እንዳዘው በሕጉ ጸንተው ተስማምተው የሚኖሩ መልካም ሥራን በመሥራት እንደ ዘካርያስና እንደ ኤልሳቤጥ እውተኞች ነበሩ። እነርሱም ሁለት ደጋጎች ልጆች አሏቸው፤ የተባረከ መልካም ፍሬ በመጾምና በመጸለይ እግዚአብሔር የሚያገለግል በጸሎቱ ሰውን የሚጠቅም በጻድቃንም ዘንድ የተመረጠ ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ዘወትር ወደ እግዚአብሔር እና ወደ ድንግል ማርያም ይለምኑ ነበር እግዚአብሔር በዓይነ ምሕረት ተመለከታቸው ልመናቸውንም ሰምቶ አባታች አቡነ እስትንፋስ ክርስቶስ ሚያዝያ 8 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ8 ቀን ተወለዱ፤ በተወለዱበትም ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ጣዕም ባለው አንደበትም አመሰገኑ ዘጠኝ ጊዜም ሕፃናትን ለሚያናግሩ ገዢ ለሚሆኑ ለሥላሴ፣ ለእመቤታችንና ለመስቀሉ ሰገዱ፡፡
❤ የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን አወቁ። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ እስትፋሰ ክርስቶስ።
+ + +
❤ ስለ አቡነ ኪሮስ ልደት፦ በሮም አገር እግዚአብሔርን የሚፈራ ስሙ ዮናኒ የሚባል አንድ ሰው ነበር። በአባቱ ዙፋን ተቀምጠ ድንቅ ሥራንም ሠራ አባቱ ከሠራው ሥራም ምንም አላጐደለም ስድሳ ዓመት ኖረ ስሙ አብያ የሚባል ልጅም ወለደ በክብርም ዐረፈ።
❤ አብያም በአባቱ ዙፋን ነገሠ አባቱ ከሠራው መልካም ሥራ አንድም ስንኳን አላጐደለም። የሚስቱም ስሟ ሜናሴር ይባል ነበር ሠላሳ ዓመትም መካን ሆና ኖረች። ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ ሜናሴርም ፀነሰች ሁለት ልጆችም ወለደች ታላቁን ቴዎዶስዮስ ታናሹን ዲላሶር አለችው። በመልካም አስተዳደግ አሳደጓቸው ከዚህ በኋላ አባታቸው አብያ በክብር ዐረፈ።
❤ ቴዎዶስዮስም በአባቱ በአብያ ዙፋን ነገሠ። ከሦስት ዓመት በኋላ ዲላሶር ቴዎዶስዮስን "ከአባቴ ገንዘብ ድርሻዬን ስጠኝ" አለው። ቴዎዶስዮስም "ወንድሜ ሆይ የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው የአንተም የእኔ ነውና ከእኔ በታች የፈቀድከውን የሚከለክልህ ማነው?" አለው። "ልጅ ስለሆንክ ግን ፈጽሜ ከፍዬ አልሰጥህም" አለው በዚህም ምክንያት እርስበርሳቸው ተጣሉ። ዲላሶርም በሌሊት ተነስቶ ተሸሽጐ ወጥቶ አድርስ ወደ ሚባል ተራራ ሄደ። በዚያም ትንሽ ዋሻ አግኝቶ እስከ ዐሥር ቀን በውስጧ ተቀመጠ። መንፈስ ቅዱስም "ኪሮስ ሆይ ብሎ ጠርቶ ለብዙዎች አባት ትሆናለህ በቃልህም እንክርዳድ ኃጢአት ይነቀላል ጽድቅ ስንዴ ያፈራል። አሁንም ከዚህ ተነስተህ ወደ ፊትህ የአንድ ቀን ጐዳና ሒድ። በዚያም ባሕታዊ መነኵሴ ታገኛለህ ከእርሱም የምንኵስናን ልብስ ትለብሳለህ" አለው። ይህን ብሎት ከእርሱ ተሰወረ። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ኪሮስ።
+ + +
❤ አቡነ ተክለ አልፋ ዘደብረ ድማህ (ዲማ) ፡- ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ አልፋ ልደታቸውም ዕረፍታቸውም ታኅሣሥ 8 ነው፡፡ "ተክለ አልፋ" ማለት ለዘለዓለም የሚኖር ድንቅ ሥራ ማለት ነው፡፡ ጻድቁ ቀደምትና ዓበይት ከተባሉት ከ72 ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በደብረ ድማህ አበምኔትነት ተመርጠው ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ የሴቶችን ማኅፀን የምታበላሸውንና መካን የምታደርገውን "እመ ሙላድ" የተባለችውን ዛር አቡነ ተክለ አልፋ በመቋሚያቸው እንደ አውሬ አባረው አጥፍተዋታል፡፡ እርሷም እንደ ሰው ትልካ ሄዳ ማኅፀን የምታጠፋ ነበረች፡፡
❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ተክለ አልፋ ሹመትን አልፈልግም ብለው በጸሎት ብቻ ተወስነው የኖሩ በዲማ ትልቅ ክብር ታላቅ አባት ናቸው፡፡ በተወለዱበት ዕለት ታኅሣሥ 8 ቀን ሲያርፉ ማረፋቸውን መቁዋሚያቸው ናት በሰው አንደበት "አባታችን ዐረፉ" ብላ ለመነኮሳቱ የተናገረችው፡፡ ጻድቁ የጠቀበሩት በተሾሙበትና ለ35 ዓመታት ባገለገሉበት በዚያው በዲማህ (ዲማ) ነው፡፡ ከአባታችን ከአቡነ ተክለ አልፋ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
+ + +
❤ ሰማዕቱ አባ ገብረ ማርያም፡- ይህም ቅዱስ የሰማዕታትንና የጻድቃንን በየዕረፍታቸው ቀን ለእያንዳንዳቸው ርኁባንን በማጥገብ የተራቆቱትን በማልበስ መታሰቢያቸውን የሚያደርግ ነው፡፡ እንዲህም ባለ ሥራ ላይ እያለ ይን ጊዜ እስላሞች ወደ ሸዋ አገር መጡ፡፡ እርሱም ያማሩ የክህነት ልብሶቹን ለብሶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ጸሎትን ጸለየ ሲጸልይም እስላሞች ወደርሱ መጥተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ አባት በቅዱስ ገብረ ማርያም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 8 ስንክሳር።
+ + +
❤ ብጹዕ አቡነ ሙሴ ዘድባ፦ በአባታቸው የእቤታችን ጠባቂ የአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የልጅ ልጅ ሲሆኑ፤ በእናቸው በኩል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር በቃና ዘገሊላ ሰርግ የተገኘችበት የዶኪማስ የልጅ ልጅ ናቸው። የአባታቸው ስም ቅዱስ ዮስጦስ ሲባል፤ የእናታቸው ስም ቅድስት ጵስርስቅላ (ሶልያና ማርያም) ይባላል።
❤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት ታኅሣሥ 8 ቀን ተወለዱ። በዚህች ቀን ከእናታቸው እቅፍ በመውረድ "ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን፤ ከጨለማ ወደ ብርርሃን ላወጣኸኝ" ብለው ፈጣርያቸውን አመስግነዋል። በ40ኛው ቀን የጌታ ሐዋርያት ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ፊሊጶስና እንድርያስ ሆነው ጥር 17 ቀን ክርስትናን አቡነ ሙሴን አነሱዎቸው። በ3 ዓመታቸው ወላጆቻቸው ለቤተ ከክርስቲያን ሰጧቸው። ቅዱስ ፋኑኤልና ቅዱስ ዮናኤል ሕብስት ሰማያዊ እያመጡ ይመግቧቸው ነበር። ከዚህ በኋላ መምህራቸው ዝክረ ጻድቅ ብሉያትንና ሐዲሳትን አስተማራቸው። በወንጌላዊው በቅዱስ ማርቆስ እጅ ዲቁና
1 161
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ማጂ ወረዳ ላይ አንድ የቤተክርስቲያን ምዕመናንን ማንቂያ እና የበገና የመጀመሪያ ዙር ጥቂት ተማሪዎችን ማስመረቂያ ጉባኤ ከታህሳስ 19-23/2015 ዓ.ም ለማዘጋጀት አስበናል እና ለዚህ ስራ እያስተባበርን እንገኛለን። እዚህ አካባቢ ያለው ማኅበረ ቅዱሳን ቅርንጫፍ ከተቋቋመ ገና ሁለት አመት አልሞላውም፤ የተጠናከረ ገንዘብ አቅም የለውም። ሰበካ ጉባኤውም በሙዳይ ምጽዋት ነው የሚተዳደረው የተለየ የገቢ ምንጭ የለውም። እና ሁለቱም አካላት ሊደግፉን አቅም ስለሌላቸው በግላችን ነው ገቢ አሰባስበን ጉባኤውን ለማዘጋጀት ያሰብነው። እዚህ አካባቢ ያለው ምዕመን ስለክርስትና ሕይወቱ ጠለቅ ያለ ዕውቀት የሌለው (ስመ ክርስቲያን የምንለው አይነት)፤ በልማድ የሚኖር በአዚም ውስጥ ያለ ነው። ግን ከተሰራበት ደግሞ የሚቀበል ልቦና፤ የሚነሳሳ መንፈስ አላቸው እና ይህንን በማሰብ ዘማርያን እና መምህራን ከአዲስ አበባ በማስመጣት የ5 ቀን ጉባኤ ለማዘጋጀት እያሰብን ነው መድኃኔዓለም ከፍጻሜ ቢያደርስልን።
ነገር ግን የትራንስፖርት ወጪው እንኳን 10 ሰው ለማስመጣት ከ 30,000-50,000 ብር ያስወጣል። በተጨማሪም የተጋባዦች አበል፣ የምግብ ወጪዎች ሲጨመር ሂሳቡ እስከ 80,000 ብር ደርሷል። እና ይህንን ከምናውቃቸው ሰዎች ጋር እየተነጋገርን ገቢ የማሰባሰብ ስራ እየሰራን ነው። እና እናንተም ሀሳቡን ከወደዳችሁት በግላችሁ የአቅማችሁን አስራታችሁንም በመስጠት ሆነ የአቅማችሁን አስተዋጽኦ በማድረግ እንዲሁም በያላችሁበት አካባቢ፣ ስራ ቦታ ወይም በምታውቋቸው ሰዎች በኩል ፈቃደኛ የሆኑ ካሉ ሀሳቡን በማስረዳት የተወሰነ ገቢ የማሰባሰብ ስራ መስራት ከቻላችሁ እንድታግዙን በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ጉባኤው ሳይጀምር ሁኔታዎችን በአግባቡ ለማስተካከል እስከ ታኅሳስ 10/2015 ዓ.ም ነው ገቢ ማሰባሰቡን ስራ ለማጠናቀቅ ያሰብነው። እና የየራሳችሁን ሀሳብ ብትገልጹልኝ ስል እጠይቃለሁ።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000139714327 ቴዎብስታ ስቡሕ
ለበለጠ መረጃ 0923257837
እግዚአብሔር ፈቅዶ ጉባኤው ከተሳካ ደግሞ ቪዲዮ ቀርጸን ለሁሉም እንዲዳረስ በYouTube የምንለቀው ስለሚሆን የስራውንም ውጤት ማየት ትችላላችሁ።
<<የሰማይ፡አምላክ፡ያከናውንልናል፥እኛም፡ባሪያዎቹ፡ተነሥተን፡እንሠራለን። መጽሐፈ ነህምያ 2÷20>>
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማር. 16፥15-ፍ፡ም፡ "ወይቤሎሙ ሑሩ ውስተ ኲሉ ዓለም" - "እንዲህም፡አላቸው፦ወደ፡ዓለም፡ሁሉ፡ሂዱ፥ወንጌልንም፡ለፍጥረት፡ሁሉ፡ስበኩ። ያመነ፡የተጠመቀም፡ይድናል፥ያላመነ፡ግን፡ይፈረድበታል። ያመኑትንም፡እነዚህ፡ምልክቶች፡ይከተሏቸዋል፤በስሜ፡አጋንንትን፡ያወጣሉ፤በዐዲስ፡ቋንቋ፡ይናገራሉ፤እባቦችን፡ይይዛሉ፥ የሚገድልም፡ነገር፡ቢጠጡ፡አይጎዳቸውም፤እጃቸውን፡በድውዮች፡ላይ፡ይጭናሉ፡እነርሱም፡ይድናሉ። ጌታ፡ኢየሱስም፡ከነርሱ፡ጋራ፡ከተናገረ፡በኋላ፡ወደ፡ሰማይ፡ዐረገ፡በእግዚአብሔርም፡ቀኝ፡ተቀመጠ። እነርሱም፡ወጥተው፡በየስፍራው፡ሁሉ፡ሰበኩ፥ጌታም፡ከእነርሱ፡ጋራ፡ይሠራ፡ነበር፥በሚከተሉትም፡ምልክቶች፡ቃሉን፡ያጸና፡ነበር"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
7/4/2015 ዓ.ም (፯/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ሌሊተ ተዛዋዕኩ ምስለ ልብየ ወአንቃህክዋ ለነፍስየ።
ቦኑ ለዓለም ይገድፍ እግዚአብሔር።
ወኢይደግምኑ እንከ ተሣህሎ፡፡ መዝ 76፥6
🕯 ትርጉም
በሌሊት ከልቤ ጋራ ተጫወትኹ÷ ነፍሴንም አነቃቃዃት።
እግዚአብሔር ለዘለዓለም ይጥላልን?
እንግዲህስ ቸርነቱን አይጨምርምን?
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ዮሐ. 21:20-ፍ፡ም፡ "ወተመይጦ ጴጥሮስ" - "ጴጥሮስም፡ዘወር፡ብሎ፡ኢየሱስ፡ይወደው፡የነበረውን፡ደቀ፡መዝሙር፡ሲከተለው፡አየ፤እርሱም፡ደግሞ፡በእራት፡ጊዜ፡በደረቱ፡ተጠግቶ፦ጌታ፡ሆይ፥አሳልፎ፡የሚሰጥህ፡ማን፡ነው? ያለው፡ነበረ። ጴጥሮስም፡ይህን፡አይቶ፡ኢየሱስን፦ጌታ፡ሆይ፥ይህስ፡እንዴት፡ይሆናል? አለው። ኢየሱስም፦እስክመጣ፡ድረስ፡ይኖር፡ዘንድ፡ብወድስ፥ምን፡አግዶህ? አንተ፡ተከተለኝ፡አለው። ስለዚህ፦ያ፡ደቀ፡መዝሙር፡አይሞትም፡የሚለው፡ይህ፡ነገር፡ወደ፡ወንድሞች፡ወጣ፤ ነገር፡ግን፥ ኢየሱስ፦እስክመጣ፡ድረስ፡ይኖር፡ዘንድ፡ብወድስ፡ምን፡አግዶህ? አለው፡እንጂ፡አይሞትም፡አላለውም። ስለ፡እነዚህም፡የመሰከረ፡ይህንንም፡ጽፎ፡ያለ፡ይህ፡ደቀ፡መዝሙር፡ነው፥ምስክሩም፡እውነት፡እንደ፡ሆነ፡እናውቃለን። ኢየሱስም፡ያደረገው፡ብዙ፡ሌላ፡ነገር፡ደግሞ፡አለ፤ሁሉ፡በእያንዳንዱ፡ቢጻፍ፡ለተጻፉት፡መጻሕፍት፡
ዓለም፡ራሱ፡ባልበቃቸውም፡ይመስለኛል።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
7/4/2015 ዓ.ም (፯/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
እጸርኅ ኀበ እግዚአብሔር ልዑል።
ኀበ እግዚአብሔር ዘረድአኒ።።
ፈነወ እምሰማይ ወአድኃነኒ። መዝ 56፥2
🕯 ትርጉም
ወደሚረዳኝ እግዚአብሔር ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለኹ።
ከሰማይ ልኮ አዳነኝ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
