ru
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Открыть в Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Больше
1 161
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
02-ጥበበ ወምክረ.amr0.56 KB

01-ሰላም ለክሙ.amr0.67 KB

🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀 ስርአተ ማህሌት ዘታህሳስ አባ ሳሙኤል 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁 💎መልክአ ሥላሴ ለሕፅንክሙ ሰላም ለሕፅንክሙ ምርፋቀ ጻድቃን አግብርቲሁ፤ማያተ ኢያሱ ሥላሴ እለ ትውኅዙ እምሕሊናሁ፤እንዘ በአፍአሁ አንትሙ ወአንትሙ በዉሳጤሁ፤ኢነፀረ ኀበ ሐይመት ከመ አብርሃም አቡሁ፤ወመስኮተ ነቢይ ዳንኤል ኢፈቀደ ያርኁ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ ላህም መግዝዕ ተጠብሐ፤ ጽዋዓ መድኃኒት ተቶስሐ፤ አግብርት አግብርት አግብርት ይረፍቁ፤ ውስተ ሕፅኑ ለመርዓዊ። @EOTCW 💎ነግስ፦ እንዘ ይተግህ ለጸልዩ ወያስተበርክ ለስኢል፤ መንኮብያቲሁ አጥበዎ ወልደ ማርያም ድንግል፤ አመኒ ወረዱ በሞቱ ተድባባተ ብርሐን ፅዱል፤ ቃል ለለተድባቡ ዘይብል ሳሙኤል ሳሙኤል ሳሙኤል ዘዋልድባ መነኮስ ሐያል። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ መጽአ ቃል እምሰማይ ዘይብል፤ ሳሙኤል ገብርየ በአፈቅር፤ ተፈጸመ ለከ ፍትወትከ፣ ወናሁ ተርኅወ ለከ ኃዋኅወ ሰማያት ሰራዊተ መላእክት ይጸንሑከ፣ ድልው መንበርከ፤ ጸጋ ረድኤተ ተውህበ ለከ @EOTCW 🌱🌱ዘጣዕሙ፦ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ ሳሙኤል ይቤላ ርግብየ ሠናይት፤ በአክናፈ መላእክት ትትኬለል፤ ማርያም ቅድስት ማኅደረ መለኮት። @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘሙዓቲሁ ድሙፅ፤ ወለስዕርትከ ሰላም ሐመልማለ ድማኅ ስሩፅ፤ ተወካፌ ፃማ ሳሙኤል ወጸዋሬ ኩሉ ተግሳጽ፤ለለ እነግር ስብአቲከ አስተራየኒ በገጽ፤ ከመ አስተርአየከ ሚካኤል በገዳም ወአጽ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ ደምፀ ወተሰብከ ዉስተ ዓለም፤ ዜና ምግባሩ ትሩፍ ለአረጋዊ ለገብረ መንፈስ ቅዱስ ኮከበ ገዳም። @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም እብል ለጣዕመ ልሳንከ ዘርብ፤ ወለቃልከ ሰላም ዘኲለንታታ ጥበብ፤ እደ ሱራፊ ሳሙኤል ወዘውገ ኪሩብ፤ አጢኖትከ በሥጋ መንበረ ዕበዩ ለአብ፤ መንክርኬ ወጥቀ ዕፁብ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ መንበረ ልዑል የዓጥን ቃለ ፈጣሪ ይሰምዕ፤ ብፁዓን ካህናት ጽርሐ አርያም የኃድር። @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም ለገቦከ ዘተሰትረ በሰቅ፤ ወለከርስከ ሰላም ምእላደ መንፈስ ረቂቅ፤ ሳሙኤል አስተርኢ ቅድመ ገጽነ በጻህቅ፤ አባ ክቡር ወአባ ጻድቅ፤ በረከትከ ንሴፎ ደቂቅ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ አባ ዘይሰርር በአክናፍ ከመ አዕዋፍ፤ ኃበ አምደ ወርቅ ስሙ ጽሑፍ @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም ለአቊያጺከ ወለዘዚአዎን አብራክ፤ እለ አወተራ ስግደተ ለሠዐተ ጽባሕ ወሠርክ፤ መንፈስ ቅዱስ ሳሙኤል ወዘርዓ ሀይማኖት ብሩክ፤ አንተኑ ሚካኤል መልአክ፤ ዘይቀውም ቅድመ ገጹ ለክርስቶስ አምለክ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ ኮከብ ጽዱል በገዳም ዘሐቅል፤ ሰአል አባ ወተንብል ፤ካህን ዓቢይ ወመልአከ ዘውገ ሚካኤል፤ አማን ሳሙኤል ትሩፈ ገድል @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም ለመከየድከ ሠረገላ መልክእ ጸናፊ፤ ወለአጻብኢከ ሰላም ዘኢያዕቀፎን አዕቃፊ፤ ለዕበይከ ሳሙኤል እንዘ ስብሐተ አወፊ፤ ሐውጸኒ እንዘ ሀሎከ በዐለመ ስጋ ኃላፊ፤ አመ ሐወፀከ ሚካኤል ሱራፊ። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ ወይቤ ሳሙኤል ከመ ዝኑ ረስየኒ፣ ሚካኤል አመ ሐወፀኒ፣ አማን ያዕትት ዝንጓጌ እምሰብእ @EOTCW ✨መልክዐ ሳሙኤል፦ ሰላም ለፀአተ ነፍስከ እማእፈደ ስጋ ወደም፤ ወለበድነ ስጋከ ባህሪይ ዋካ ሐቅለ ዋሊ ገዳም፤ መናኔ ፍትወት ሳሙኤል ወሐሣሤ አዲስ አለም፤ ጴጥሮስ ወጳውሊ ከመ ለሀውቶሙ ለሮም ፤ለሐወት ገዳምከ በሞትከ ዮም። @EOTCW 🌱ዚቅ፦ በከየት ወለሀወት ገዳምከ፤ ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ፤ በ፡ እንዘ አንተ ሰብእ ምድራዊ ወመልአከ ተሰመይከ፤ በ፡ ካሀነ አርያም ሳሙኤል መንበረ ሥላሴ ዘአጠንከ፤ በ፡ አንበሳ ወነብር ይሰግዱ ለከ ወይልህሱ ጸበለ እግርከ፤ በ፡ ዕንቆ ወዕጣነ ማርያም አምጽአት ለከ በቅዳሴሃ ሶበ ጸለይከ፤ በከየት ወለሀወት ገዳምከ፤ በከየት ወለሀወት ገዳምከ። @EOTCW ❄️ምልጣን፦ ኮከብ ጽዱል በገዳም ዘሐቅል፤ ሰአል አባ ወተንብል ፤ካህን ዓቢይ ወመልአከ ዘውገ ሚካኤል፤ አማን ሳሙኤል ትሩፈ ገድል @EOTCW 🔹አመላለስ፦ አማን በአማን፤ ሳሙኤል ትሩፈ ገድል @EOTCW 🔹እስመ ለዓለም፦ ክብሮሙ ለመላእክት ተከስተ ለቅዱሳን፤ ወልድ ፍጹም ወሀቤ ሕይወት፤ መድኃኒቶሙ ለነገሥት ሠያሚሆሙ ለካህናት፤ አክሊለ ሰማዕት ተስፋ መነኮሳት፤ ክርስቶስ መጽአ ውስተ አለም። @EOTCW https://t.me/Eotcw

🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 ዋዜማ ዘታህሳስ ፲፪ አባ ሳሙኤል 🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀 @EOTCW @EOTCW @EOTCW ተጸውዑ ወተአዘዙ ሱራፌል ወኪሩቤል፤ በድምጸ ከበሮ ወበጽናጽል፤ ከመ ያዕርግዎ ለሳሙኤል፤ ኀበ ሀሎ ፍስሐ ወጣዕመ ሚስጥሩ ለቃል፤ ማ፦ እንዘ ይብሉ ካህን ወድንግል @EOTCW 🔹አመላለስ፦ እንዘ ይብሉ ካህን ወድንግል፤ እንዘ ይብሉ ካህን ወድንግል @EOTCW @EOTCW ለእግዚአብሔር ምድር በምላ፦ አባ ጸሊ በእንቲአነ ጸሎትከ ይብጽዐነ አባ ጸሊ በእንቲአነ @EOTCW 💎እግዚአብሔር ነግሠ፦ ጼና አልባሢሁ አባ መባእ ጽዮን ስሂን ገነት ከመ ይርአይ ዘሜላት ዘወረደ ውስተ ገነት ከመ ይርአይ ስነ ፅጌያት @EOTCW 🔹ይት፦ ኪያከ መሠረት እንተ ብነ አባ ጸሊ በእንቲአነ እስመ ፀሎተ ጻድቅ ይስማ እግዚአብሔር @EOTCW @EOTCW 🔸ሰላም፦ አባ አነ አበ መንፈስነ ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ ሰላመ ጸሊ ለርኁቃን ወዳኅና ለቅሩባን ሰላመ ጸሊ @EOTCW 🔹አመላለስ፦ ሰላመ ጸ ለርኁቃን ለርኁቃን/2/ ወዳኅና ለቅሩባን ሰላመ ጸሊ/4/ @EOTCW https://t.me/Eotcw #Join & share #Join

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን🙏🙏🙏 የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ?የእግዚአብሔር ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን🙏🙏🙏 በዚህ ቻናል የሁሉም ክብረ በዓላትና ወርኃ በዓላት ፀዋትወ ዜማና ወረብ እንዲሁም በየሳምንቱ የእሁድ መዝሙር፤ምስባክ ከነ ትርጉማቸዉ ማህበር ቀለም የሚሰማ ስለሆነ ማህበረ ካህናት ወዲያቆናት ማህበረ ምዕመናን ወምዕመናት እንድትሰሙና ከሊቃውንቱ ጋር ምስጋና የባህርዩ የሆነው አምላካችን እግዚአብሔርን እንድታመሠግኑ እያልኩኝ በዓሉ ከመድረሱ በፊት ማህበር ቀለሙን እንድታጠኑት ይለቀቃል፡፡ በተጨማሪም እንደምትመለከቱት የየዕለቱን የቅዱሳን ታርክ ማለትም ስንክሳር ዘቅዱሳን፤መዝሙራት፤የቅዱሳን ስዕላት፤እና የተለያዩ መርሐ ግብሮችን ይዘን እየቀረብን መሆናችንን ታዉቃላችሁ።በዚህም ስለምንቀጥል ቻናላችንንና ትምህርታችንን ሼር በማድረግ እርዳታችሁ አይለየን በማለት ከታላቅ ትህትና ጋር እንጠይቃለን። https://t.me/Eotcw

photo content

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለገላውዴዎስ ድንግል ወንጹሕ ወመስተዐግሥ"። ትርጉም፦ ድንግል፣ ንጹሕና ታጋሽም ለኾነ ለገላውዴዎስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአባ በኪሞስ ፈላሲ ክብር፤ ብእሴ እግዚአብሔር፤ ዘፍጹም በገድሉ፤ በኀበ አባ ሲኖዳ ዘተዐውቀ መንበሩ ወአክሊሉ"። ትርጉም፦ በአባ ሲኖዳ ዘንድ መንበሩና አክሊሉ የታወቀ ለኾነ፤ በገድሉ ፍጹም የኾነ የእግዚአብሔር ሰው፤ ለከበረው መነኵሴ ለአባ በኪሞስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለከ ፀዋሬ ክቡድ አስፈሬዳ። ወመንሥኤ ምውት በምድረ በዳ። ዐስበ ፃማከ በኪሞስ ወዘተቀንዮትከ ፍዳ። መንበረ ብርሃናዌ ወአክሊለ ክቡር ፀዓዳ"። እግዚአብሔር አርአዮ ለአባ ሲኖዳ"። ትርጉም፦ በምድረ በዳ የሞተውን ለምታነሣ፤ ከባድ ቅርጫት (እንቅብ) የምትሸከም ለኾንኽ ላንተ ሰላምታ ይገባል፤ በኪሞስ የድካምኽን ዋጋና የአገልግሎትኽ ክፍያ የሚኾን ብርሃናዊ መንበርንና ነጭ የክብር አክሊልን እግዚአብሔር ለአባ ሲኖዳ አሳየው። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 11። https://t.me/Eotcw

photo content
+1

እያለ መከራቸው፡፡ እግዚአብሔርንም ይህን የሚናገራቸው ሰይጣን መሆኑን ገለጸላቸውና "አንተ የሐሰት አባት ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ሀሳብ ትቃረናለህ" ብለው በገሠጹት ጊዜ መልኩን ለውጦ ጥቁር ባሪያ ሆነ፡፡ "እነሆ ከንጉሡ ጋር አጣልቼ ደማችሁን እንዲፈስ አደርገዋለሁ" ብሎ ወደ ከሃዲው ንጉሥ ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ሄዶ "ፊቅጦርንና ገላውዴዎስን ካልገደልካቸው በአንተ ላይ ይነሱብሃል፣ አንተንም ገድለው መንግሥትህን ይወስዳሉ፣ እነርሱም የመንግሥት ልጆች መሆናቸውን ዕወቅ" አለው፡፡ ❤ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ገላውዴዎስን አስጠርቶ የአባቱን ሹመት እንደሚሾመው ቃል ከገባለት በኋላ ለጣዖቱ እንዲሠዋ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስ ግን በድፍረት ጣዖቱንና ንጉሡን ሰደባቸው፡፡ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ኅርማኖስ የተባለው ባለሟሉ "እንደ ልጄ ፊቅጦር ዐመፀኛ ነውና ወደ እስክንድርያ ልከነው በዚያ እንዲገድሉት እናድርግ" ብሎ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስን መከረው፡፡ አሠቃይተው እንዲገድሉትም ከደብዳቤ ጋር አድርገው ወደ እንዴናው ሀገር ዥ ወደ ጨካኙ አርያኖስ ላኩት፡፡ ❤ አርያኖስም ቅዱስ ገላውዴዎስን ባየው ጊዜ ደንግጦ በክብር ተቀበለው፡፡ እጅ ነሥቶም ከሳመው በኋላ "ጌታዬ ስለምን የንጉሡን ትእዛዝ ትተላለፋለህ?" እያለ መከረው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስም "ንጉሡ ያዘዘህን ትእዛዝ ልትፈጽም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላኩም" አለው፡፡ መኰንኑም እስኪቆጣ ድረስ ብዙ ጊዜ እያባበለው ተነጋገሩ፡፡ ከዚህም በኋላ አርያኖስ እጅግ ተቆጣና በያዘው ጦር ወግቶ ቅዱሱን ገደለው፡፡ ቅዱስ ገላውዴዎስም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ምእመናንም የመከራው ዘመን እስኪፈጸም ቅዱስ ሥጋውን ወስደው ከቅዱስ ፊቅጦር ጋር በሣጥን አኖሩት፡፡ የቅዱስ ፊቅጦርም እናት ቅድስት ሶፍያ ወደ እንዴና ሀገር መጥታ የሁለቱን ቅዱሳን ሥጋቸውን ወደ አንጾኪያ ወስዳ በክብር አኖረችው፡፡ ❤ የዚህ ታላቅ ሰማዕት የቅዱስ ገላውዴዎስ ገዳም በሀገራችን የሰሜኑ ክፍል ከባሕርዳርና ወደ ጎንደር በሚወስደው መንገድ ላይ ይገኛል፡፡ ገዳሙን ለየት የሚያደርገው ነገር በገዳሙ ክልል ውስጥ የተቀበረ ሰው አስክሬኑ በቀጣዩ ቀን ይሰወራል፡፡ ወደየት እንደሚሄድም አይታወቅም፡፡ ማንኛውም አስክሬን በተቀበረ በማግሥቱ በቦታው ላይ ፈጽሞ አይገኝም፡፡ ይህ አሁንም ድረስ በግልጽ የሚታይ ነው፡፡ ከሰማዕቱ ከቅዱስ ገላውዴዎስ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና የሰኔ 11 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወይነግሩኑ እለ ውስተ መቃብር ሣህለከ። ወጽድቀከኒ ውስተ ሞትኑ። ይትዐወቅኑ ውስተ ጽልመት መንክር"። መዝ 87፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 12፥9፣ 1ኛ ጴጥ 4፥6-12 እና የሐዋ ሥራ 17፥28-ፍ.ም። የሚበበው ወንጌል ማቴ 6፥7-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ገላውዴዎስ የልደት በዓልና የነቢያት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን ለየግብጽ ደቡብ ከሆነ ከመጺል አውራጃ ከሬስ ከተማ ሰዎች ወገን ለሆነ በሌሊት እንዲሁም በቀን ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያ ይጸልይ ለነበረ ለቅዱስ አባ በኪሞስ ለዕረፍት በዓልና በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን ለሆነ በንፅህናው የመላእክት አርአያ ላለው ለተባለ ለከበረ ለሰማዕት ለቅዱስ ለገላውዴዎስ ለልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከኤጲስ ቆጶስ በርተሎሜዎስና ከሰማዕቱ ከቅዱስ በጥላን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ አባ በኪሞስ፦ ይኸውም ቅዱስ አባት የግብጽ ደቡብ ከሆነ ከመጺል አውራጃ ከሬስ ከተማ ሰዎች ወገን የሆነ ነው፡፡ እርሱም የአባቱን በጎች የሚጠብቅ ነበር፡፡ ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ በጐልማሳ አምሳል ተገለጠለትና "በአንድነት ሄደን እንመነኩስ ዘንድ ትሻለህ?" አለው፡፡ እርሱም "አዎን አለ" ሁሉቱም ተስማምተው አብረው ወደ አስቄጥስ ገዳመ ተጓዙ ሦስት አረጋውያን መነኰሳት አገኙ አባ በኪሞስ ከእነርሱ ጋር ሃያ አራት ዓመታትን ኖረ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ በኪሞስ ከዚያ ተነሥቶ የሦስት ቀን ጎዳና ያህል ተጓዘና ሩቅ ወደሆነ በረሀ ውስጥ ገባ ሰይጣናትም በእሪያዎችና በዘንዶዎች አምሳል ሆነው መጡበት፡፡ ሊነክሱትም አፋቸውን ከፍተው ከበቡት እርሱ ግን የአጋንንት ሐሳብ ዐውቆ በእግዚብሔር ኃይል እፍ አለባቸው በዚያን ጊዜ ተበተኑ፡፡ እርሱም ወንዝ አግኝቶ ሰባት ሰባት ቀን እየጾመ በዚያ ሦስት ዓመት ኖረ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ በመሀል በእጁ ተምር ያንን ይመገባል ውኃም በጥቂቱ ይጠጣል። በሌሊት ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ በቀንም እንዲሁ ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልያል፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አርባ አባር ቀን እየጾመ ሃያ አራት ዓመታት ያህል ኖረ፡፡ አርባውም ቀን ሲፈጸም አንድ ጊዜ ይመገባል፡፡ ከዚህም በኋላ ቆዳው ከዐንጥንቱ ጋር እስኪጣበቅ ሰማንያ ቀን ጾመ፡፡ በዚህም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ይበላና ይጠጣ ዘንድ እንጀራና ውኃን አመጣለት ያም ውኃና እንጀራ ሳያልቅ እስከ አረፈ ድረስ ብዙ ዓመታት ሲመገበው ኖረ፡፡ ፈጣሪ እግዚአብሔር በሌሊት ራእይ ተገልጦ ወደ አገሩ እንዲመለስ አዘዘው፡፡ እርሱም ወደ ሀገሩ ተመልሶ በዚያች ትንሽ በዓት አበጅቶ መኖር ሲጅር ብዙዎች ወደ እርሱ መጥተው ፈውስን የሚያገኙ ሆኑ፡፡ እርሱም ጣዕም ባለው አንደበቱ ወንጌልን እያስተማራቸው ድውያንንም ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ ❤ በአንዲት ዕለትም የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ በኪሞስን ነጥቆ ወስዶ ወደ ኤፍራጥስ ምድር አደረሰው፡፡ የዚያች አገር ሰዎች ሕግን በመተላለፍ ከእውነተኛ ሃይማኖት ወጥተው ነበርና፡፡ አባ በኪሞስም አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖትና ወደ በጎ ምግባር መለሳቸውና ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በአንዲት ዕለትም ሸጦ የዕለት ምግቡን ያገኝ ዘንድ አገልግሎችን ተሸክሞ ወደ ከተማ ሲሄድ በጎዳና ላይ ደክሞት አገልግሎቹን አስቀምጦ ያርፍ ዘንድ ተቀመጠ፡፡ ወዲያውም ከአገልግሎቹ ጋር የእግዚአብሔር ኃይል ተሸክሞ ወስዶ ከሚሸጥበት ቦታ አደረሰው፡፡ ❤ በዚያንም ወቅት አባ ሲኖዳ ከፍተኛ የዕንቁ ባሕርይ ምሰሶ በራእይ አየና "ይህ ታላቅ ግሩም የሆነ ምሰሶ ምንድነው?" ብሎ ደነገጠ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና "ይህ አባ በኪሞስ ነው" አለው፡፡ አባ ሲኖዳም አባ በኪሞስን ያገኘው ዘንድ ወደ እርሱ አገር በእግሩ ተጓዘ፡፡ ከዚያችም ቀን በፊት ከቶ አላየውም ነበር፡፡ ሄዶም ባገኘው ጊዜ ሁለቱ ቅዱሳን ሰላምታ ተሰጣጡ። አባ በኪሞስም ወጥ ሊአበስል ወደደ አባ ሲኖዳንም "ይቺን እንስራ ያዛትና ሔደህ ውኃ ቀድተህ መልተህ አምጣልኝ" አለው። በዚያንም ጊዜ አባ ሲኖዳ ተነሣና ያቺን እንስራ ተሸክማት ውኃውንም ቀድቶ መልቶ አመጣለት ወጡንም ፈልቶና በስሎ አገኘው በዚያንም ጊዜ አባ በኪሞስ መሆኑን አወቀ ከእርሱም ጋር ሰላምታን ደገመ እጅ በመነሣሣትም ሰላምታ ተለዋወጡ። ከዚህም በኋላ ሲኖዳ ስለርሱ ያየውን ራእይ ነገረው በእርሱም ዘንድ ጥቂት ቀኖች ኖረ። ❤ ዳግመኛም በአንዲት ዕለት አብረው ሲጓዙ አንድን የሞተ ሰው ራስ ቅል አገኙና አባ ሲኖዳ በበትሩ ነቅነቅ አደረገውና "ምውት ሆይ! ያየኸውን ትነግረን ዘንድ በጌታችን ስም ተነሥ" አለው፡፡ ወዲውም ነፍሱ ወደ ዐፅሙ ተመልሳ ሥጋ ለብሶ ተነሣና ሰገደላቸው፡፡ በሲኦል ያየውንም ሁሉ በዝርዝር ነገራቸው፡፡ በየወገናቸው በሲኦል ውስጥ የሚሠቃዩትንና እርሱም የማያምን አረማዊ መሆኑን ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም "ክብር ይግባውና በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያመኑ ትእዛዙን ግን ያልጠበቁ በአሕዛብ ሥራባ በአረማውያን ርኩሰት የኖሩ በሲኦል ከእኛ በታች የሚኖሩ ክርስቲያኖች አሉ" ብሎ ነገራቸው፡፡ ቅዱሳኑም "በል ተመልሰህ ተኛ" አሉትና እንቀድሞው ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ሲኖዳ አባ በኪሞስን ተሰናብቶ ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡ ❤ ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ ቅዱስ አባ በኪሞሰሰ አገልጋዩን ጠርቶ የሥጋውን መቅበሪያ ቦታ አሳየው፡፡ ወዲያውም በሆድ ዝማ ሕመም ጥቂት ታመመና፡፡ ቅዱሳንን በአንድነት ወደእርሱ ሲመጡ አያቸው፡፡ በዚያንም ጊዜ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። መላእክትም ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት እስከአደረሷት እያመሰገኑና እየዘመሩ አሳረጓት፡፡ መላ ዕድሜውም ሰባ ዓመት ሆነ ዐሥረሠ ሁለት ዓመት በዓለም ውስጥ ሃምሳ ስምንት ዓመት በምንኩስና ሥራ ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ በኪሞስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ11 ስንክሳር። + + + ❤ ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ገላውዴዎስ፡- ገላውዴዎስ ማለት "ዕንቈ ጳዝዮን" ማለት ነው፡፡ የመላእክት አርአያ ያለቅ ቅዱስ ገላውዴዎስ አባቱ አብጥልዎስ የሮሙ ንጉሥ የኑማርያኖስ ወንድም ነው፡፡ አባቱን የአንጾኪያ ሰዎች እጅግ ይመኩበትና ይወዱት ነበር፡፡ በሕይወት እያለም በጦርነት ድል ሲያደርግ የሚያሳይ ሥዕሉን በከተማው ላይ አሠርተው ያከብሩት ነበር፡፡ ልጁ ቅዱስ ገላውዴዎስ ግን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እየተማረ አደገ፡፡ የሮሙ ንጉሥም ዜናውን ሰምቶ ሊያየው ወደደና ልጁን እንዲልክለት መልእክት ላከ፡፡ ሄዶ ሲያየውም ንጉሡ ከነሠራዊቱ ወጥቶ በክብር ተቀበለው፡፡ ❤ ጣዖት አምላኪ የሆኑ የቁዝና የሌሎችም ሀገሮችን ቅዱስ ገላውዴዎስ ድል እያደረጋቸው ጣዖቶቻቸውንም ይሰባብርባቸው ነበር፡፡ ወደ አንጾኪያም በተመለሰ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታችንን ክዶ ጣዖት ማምለክ መጀመሩን ባየ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ከቅዱስ ፊቅጦርም ጋር ሆነው የመጻሕፍትን ቃል ዕለት ዕለት ያነቡ ነበር፡፡ ሁለቱም ስለ ጌታችን ክብር ሰማዕት ሆነው ደማቸውን ያፈሱ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ ሰይጣንም በሽማግሌ አምሳል ተገልጡ ያዘነላቸው በመምስል "ልጆቼ ሆይ መልካም ጎልማሶች ናችሁ፣ የነገሥታት ልጆችም ናችሁ፣ እኔ ስለ እናንተ አዝንላችኋለሁ ስለዚህም ከንጉሡ ጋር ተስማምታችሁ አማልክቶቹን እያጠናቸሁ ትእዛዙንም እየፈጸማችሁ ኑሩ፡፡ ነገር ግን ክርስቶስን በቤታችሁ አምልኩት ይህ ዲዮቅልጥያኖስ ግን እጅግ ጨካኝና ኃይለኝ ነው"

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 6:1-5፡ "ወባሕቱ ዑቁ ምጽዋተክሙ" - "ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤ ያለዚያ በሰማያት ባለው አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም። እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኵራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል። ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኵራብና በመንገድ ማእዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.43 KB

10/4/2015 ዓ.ም (፲/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ዘረወ ወወሀበ ለነዳይ። ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም። ወይትሌዐል ቀርኑ በክብር። መዝ. 111፥9 🕯 ትርጉም ለገሰ፤ ለችግረኞችም ሰጠ። ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል። ሥልጣኑ በክብር ከፍ ከፍ ይላል። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 5÷36-41፡ "ወአንሰ ብየ ሰማዕት" - "እኔ፡ግን፡ከዮሐንስ፡ምስክር፡የሚበልጥ፡ምስክር፡አለኝ፤አብ፡ልፈጽመው፡የሰጠኝ፡ሥራ፥ይህ፡የማደርገው፡ሥራ፥አብ፡እንደ፡ላከኝ፡ስለ፡እኔ፡ይመሰክራልና። የላከኝ፡አብም፡ርሱ፡ስለ፡እኔ፡መስክሯል።ድምፁን፡ከቶ፡አልሰማችኹም፥መልኩንም፡አላያችኹም፤ ርሱም፡የላከውን፡እናንተ፡አታምኑምና፡በእናንተ፡ዘንድ፡የሚኖር፡ቃሉ፡የላችኹም። እናንተ፡በመጻሕፍት፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡እንዳላችኹ፡ይመስላችዃልና፥እነርሱን: ትመረምራላችኹ፤እነርሱም፡ስለ፡እኔ፡የሚመሰክሩ፡ናቸው፤ ነገር፡ግን፥ሕይወት፡እንዲኾንላችኹ፡ወደ፡እኔ፡ልትመጡ፡አትወዱም። ከሰው፡ክብርን፡አልቀበልም፤ዳሩ፡ግን፡የእግዚአብሔር፡ፍቅር፡በራሳችኹ፡እንደሌላችኹ፡ዐውቃችዃለኹ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

3.13 KB

10/4/2015 ዓ.ም (፲/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ወተወከፍከኒ ከመ አእምር። እገኒ ለከ እግዚኦ እስመ ግሩመ ተሰባሕከ። መንክር ግብርከ ወነፍስየ ትጤይቆ ጥቀ። መዝ 138፥14                   🕯  ትርጉም ግሩምና ድንቅ ኾኜ ተፈጥሬያለኹና አመሰግንኻለኹ። ሥራኽ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

photo content
+3

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታላቅ የንግሥ ዓመታዊ ክብረ በዓል ታኅሣሥ 11 በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን። + + + ❤ "ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ፤ ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኵሎሙ መጻሕፍት ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ"። ትርጉም፦ የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ አገርን በጥዑም ማሕሌትና በማያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ለቅዱስ ያሬድ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ስለ መዋሉ፦ ዐፄ ገብረ መስቀል የቅዱስ ያሬድ ባሕረ ጥበባት ዜማን ጣዕም ሰምተው ከተረዱ በኋላ ሊቃውንትና ካህናቱን ሰብስበው "ይኽን የያሬድ ዜማ ተቀበሉትና ለቅድስት ቤተክርስትያን መገልገያ ይኹን" ባሉ ጊዜ ካህናትና ሊቃውንቱ "ምን ምልክት ዐይተን እንቀበለው? እንደሐዋርያት እጅና እግሩን ለተሳለ ቀኖት (ችንካር)፤ አፉን ለመረረ ሐሞት ሰጥቶ አላየነው?!" ብለው ሲመልሱላቸው ዐፄ ገብረ መስቀልም "እንግዲያውስ አንድ ሱባዔ እንያዝና እርሱ አምላካችን ይግለፅልን!" ብለው ሱባዔ ያዙ። ❤ ካህናት እና ሊቃውንት በታኅሣሥ ወር ከሰኞ (ታኅሣሥ 1) እስከ እሑድ (ታኅሣሥ7) አንድ ሱባዔ ይዘው የአክሱም ጽዮን ማርያምን ቤተክርስቲያን እየዞሩ አራት መቶ እግዚኦታ እና አርባ አንድ በእንተማርያም እያደረሱ ምሕላውን አከናወኑ። ❤ በሰባተኛው ቀን ታኅሣሥ 7 ቀን በዕለተ እሑድ ልመናቸውን ጨርሰው ሲያሳርጉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዐርብ እንደተሰቀለ ኾኖ ስለካህኑ ቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊነት ሊመሰክር በጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ጉልላት ላይ ተገለፀ። ❤ አባታችን ቅዱስ ያሬድም ይኽንን አስመልክቶ፦ "ዘበመስቀሉ ተቀነወ ወበነቢያት ተሰብከ መላእክት ወሊቃነ መላእክት ሰብሕዎ ኪያሁ ንሰብክ መድኅነ"። ትርጉም፦ በነቢያት ትንቢት የተነገረለትና በመስቀሉ ላይ የተቸነከረው ጌታ መላእክት እና የመላእክት አለቆች አመሰገኑት፤ እኛም እርሱ መድኃኒት እንደኾነ እንናገራለን። ❤ ቀኑም ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ዜማ ማስተማር የጀመረበት ፥ የነቢያት "ይወርዳል - ይወለዳል" ትንቢት የተፈጸመበት መኾኑን ለማጠየቅ "ስብከት" ተባለ። ❤ ታኅሣሥ 7 በዚያችም ቀን ቅዱስ ያሬድ ከሰማይ የተቀበለው ዜማ ወደ ቤተክርስቲያን ገባ የቤተክርስቲያን ብርሃኗ በራ!። ይህ በዓል ከወራዊ በዓሉ ጋራ አብሮ ታኅሣሥ 11 በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ❤ "የመላእክትን እንጀራ የሰው ልጅ በላ፥ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠኻቸው" የተባለው የቅዱስ ዳዊት የትንቢት ቃል ተፈጸመ ምንኛ ይደንቅ!። ምንጭ፦ የቤተክርስቲያን ብርሃን ቅዱስ ያሬድ (ታደሰ ዓለማየሁ)። https://t.me/Eotcw