ሰዋስው ☘☘☘☘
Открыть в Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Больше1 161
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያ አንዱ ለሆነው ለሊቀ ሐዋርያት ለቅዱስ ጴጥሮስ ወንድም ለተመሰገነ ለሐዋርያው ለቅዱስ እንድርያስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ከአባ ጻዕ፣ ከአባ ያዕቆብ፣ ከዘካርያስ፣ ከስምዖን፣ ከታዖድራና ከታውፍልዖ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ ሐዋርያው ቅዱስ እንድርያስ፦ ለዚህም ቅዱስ ይሰብክ ዘንድ ዕጣው በልዳ አገር ወጣ ከእርሷም ብዙዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት አምነው ነበር አንደበቱ የሚጥም በሥራው ሁሉና በአምልኮቱ የተወደደ ያማረ ደቀ መዝሙሩ ፊልሞና አብሮት ነበር ሐዋርያ እንድርያስም ከፍ ካለ ቦታ ላይ ወጥቶ ጣዕም ባለው አንደበቱ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንዲአነብ አዘዘው። የጣዖታት ካህናትም ሐዋርያ እንድርያስ መምጣት በሰሙ ጊዜ አማልክቶቻቸውን ይረግሙ እንደሆነ ሊጣሏቸው ሽተው የጦር መሳርያቸውን ይዘው መጡ።
❤ በዚያን ጊዜ ፊልሞና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ "ከወርቅና ከብር የሰው እጅ ሥራ የሆኑ አሕዛብ አማልክቶቻቸው አፍ አላቸው አይናገሩም፤ ዐይን አላቸው አያዩም፣ ጆሮ አላቸው አይሰሙም፣ አፍንጫ አላቸው አያሸቱም፣ እጅ አላቸው አይዳስሱም፣ እግር አላቸው አይሔዱም፣ በጒሮሮአቸው አይናገሩም የሚሠሩአቸውና የሚአምኑባቸው ሁሉ እንደእነርሱ ይሁኑ" እያለ ሲያነብ ሰሙት። ስለ ቃሉ ጣዕምና ስለ ንባቡ ማማር ልባቸው ከክህደት ማሠሪያ ተፈታ ወደ ቤተ ክርስቲያንም ገብተው ከሐዋርያ እንድርያስ እግር በታች ሰገዱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አመኑ እርሱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ከእርሳቸውም ጋር ጣዖትን ከሚያመልኩ ውስጥ ብዙዎች አምነው ተጠመቁ።
❤ በዚያ ወራትም እንዲህ ሆነ በልዳ አገር አቅራቢያ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ቄስ ነበረ ለእርሱም አንድ ልጅ አለው እርሱም ከባልንጀራው ጋር ሲጫወት በድንገት ገደለው የሟች አባትም "ልጄን የገደለ ልጅህን አሳልፈህ ስጠኝ" ሲል ቀሲስ ዮሐንስን ያዘው ቀሲስ ዮሐንስም "የአገር ሰዎችን ሔጄ ሐዋርያ እንድርያስን እስከማመጣው ዋስ ሁኑኝ እርሱ የሞተውን ያነሣልኛልና" ብሎ ለመናቸው እነርሱም በተዋሱት ጊዜ ቀሲስ ዮሐንስ ወደ ሐዋርያ እንድርያስ ሒዶ ችግሩን ሁሉ ነገረው። ሐዋርያ እንድርያስም ቀሲስ ዮሐንስን እንዲህ አለው "ከእኔ ዘንድ የሚጠመቁ ብዙ ሕዝቦች ስላሉ ከአንተ ጋር እሔድ ዘንድ አይቻለኝም ግን ደቀ መዝሙሬ ፊልሞና አብሮህ ይሒድ እርሱ የሞተውን ያስነሣልሃል" አለው። ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ ከቄሱ ጋር ሒዶ የሞተውን ያስነሣለት ዘንድ ፊልሞናን አዘዘው ወደ ከተማውም ሲቀርቡ ቄሱንና ፊልሞናን ሰዎች "በከተማው ውስጥ ሁከት ሁኗልና አገረ ገዥው እንዳይገድላችሁ ወደ ከተማ አትግቡ" አሏቸው። ፊልሞናም ግን "የመምህሬን ቃል መተላለፍ አልችልምና ቢገድለኝም መምህሬ እንድርያ መጥቶ እኔንም አስቀድሞ የሞተውንም ያስነሳናል" ብሎ ወደ ከተማው ገባ። መኰንኑም ይዞ ሠቀለውና አሠቃየው።
❤ እርሱም እንዲያዝኑለትና ለመምህሩ ለቅዱስ እንድርያስ እንዲነግሩለት ቢመጸን ሰው አጣ። በኋላም አዕዋፍ መጡና እኔን እኔን ላከኝ አሉት። እርሱም ከነርሱ መርጦ ርግብን ላካት። ርግብም ኼዳ የኾነውን ለእንድርያስ ነግራ መልሱን ተመልሳ በሰው አንደበት ለቅዱስ ፊልሞና ነገረችው። መኰንኑም ይህን አይቶ ራሱ በእጆቹ ፊልሞናን ፈታውና በጌታችን አመነ። ሰይጣንም ቀንቶ በዚህ በመኰንኑ ሚስት ላይ አደረባትና አብዳ ልጇን ራሷ ገደለችው። ይህንም ለመኰንኑ ሲነግሩት ሲጨነቅ ቅዱስ ፊልሞና አይዞህ እርሱንም ቢኾን መምህሬ ያስነሳልሃል አለው። ቅዱስ እንድርያስም እንደደርሰ ያን መዠመሪያ የሞተው ሕፃን ያስነሳው ዘንድ ቅዱስ ፊልሞናን አዘዘው። እርሱም አስነሳው። የመኰንኑንም ልጅ ቅዱስ እንድርያስ አስነሳውና የመኰንኑን ሚስትም ፈወሳት። በርሷ አድሮ ያሠቃያትንም ሰይጣን ኹሉም እያዩት ወደ ጥቅሉ ጣለው።
❤ ያቺንም ለቅዱስ ደቀ መዝሙሩ የታዘዘችለትን ርግብ ባርኮ ወደ ዱር በነጻነት እንድትኖር ሰደዳት። ከዚህም በኋላ ከእሳቸው ዘንድ ወጥቶ ወደ ሌሎች አገራት ተዘዋውሮ አስተምሪ ተአምራትንም በማድረግ ብዙዎችን አስተማረ፣ አሳምኖም አጠመቀ። ከቅዱስ በርተሎሜዎስም ጋር ተገናኝተው አስተምረዋል። በኋላ ግን በፍጻሜው ወደ አንዲት አገር ገብቶ ወንጌልን ሰበከ። የዚያች አገር ሰዎች ግን ክፉዎች ነበሩና ሊቀበሉት አልወደዱም። ከነሩ ያመኑ አሉ። ያላመኑት ግን ሊገድሉት ተንኮል አበጅተው ወደነርሱ እንዲመጣ መልእክተኛ ላኩበት። እኒያ መልእክተኞች ግን ሲደርሱ በትምህርቱ ጣዕም ተማርከው እዚያው አምነው ሳይመለሱ ቀሩ። ኹለተኛም በእሳት ሊያቃጥሉት ወደው ወደርሱ መጡ፣ እርሱም ብትመለሱ ከሰማያዊው እሳት ትድናላችሁ፣ አለዚያ ግን ለእኔ ያሰባችሁት ይኾንባችኋል አላቸው። እነርሱ ግን አልሰሙትምና ቢጸልይ እሳት ከሰማይ ወርዳ አመድ አደረገቻቸው። በሌሎች ቦታዎችም ኹሉ ይህ ድንቅ ዜናው ተሰማ።
❤ የጣዖት ካህናቱ ግን ይህንም ኹሉ ተመልክተው አላመኑም። በኋላም ይዘውት ጽኑዕ ሥቃይን እይሠቃዩ ከተማዋንም በመከራ ካዞሩት በኋላ አሠሩት። እርሱ ከክፋታቸው የተነሳ ሊመለሱ ስላልቻሉ ወደ ጌታችን እሳት አውርዶ እንዲያጠፋቸው ቢጸልይ ጌታችን በወህኒ ቤቱ ተገልጦ አጽናናውና በዚህ ጊዜ በሰማዕትነት እንደሚያርፍ ነግሮት ከርሱ ተሠወረ። በሌላውም ቀን ከእሥር ቤት አውጥተው ልክ እንደ ኤክስ በመሰለ መስቀል ሰቅለውት በድንጋይ ወግረውት በሰማዕትነት በዚች ቀን ታኅሣሥ4 ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ በሐዋርያ እንድርያስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ4 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለከ ረድአ ኢየሱስ ኬንያ። እንተ ሰበከ ወንጌሎ ወመሀርከ በኒቆምድያ። እዜምር ለከ ወእየብብ በሃሌ ሉያ። አንቅሐኒ እምኀኬትየ እንድርያስ ሐዋርያ። ከመ በእዴከ ነቅሐት እሙታን ልድያ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 4።
+ + +
❤ የዕለቱ ማኅሌት ምስባክ፦ "ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ። ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ"። መዝ18፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ1፥38-46።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወነደ እሳት ውስተ ተዓይኒሆሙ። ወአውዐዮሙ ነበልባል ለኃጥአን። ወገብሩ ላሕመ በኮሬብ"። መዝ 105፥18-19። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 11፥21-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥16-23፣ የሐዋ ሥራ 4፥29-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 9፥46-56። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ እንድርያስ የዕረፍት በዓል፣ የብፁዕ አቡነ ሙሴ የልደት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
እንኳን አደረሳችሁ
✏በዓታ_ለማርያም ፦ ታኅሣሥ ፫
👉ታኅሣሥ ፫ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን ነው። ይህንን ቀን ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች ከእናትና አባቷ ተለይታ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን በመሆኑ
👉 እመቤታችን ከአባቷ ከቅዱስ ኢያቄም ከእናቷ ከቅድስት ሐና “እም ሊባኖስ ትወጽእ መርዓት፡፡” ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሰች፡፡ ግንቦት ፩ ቀን ሊባኖስ በምትባል አካባቢ በብጽአት ተወለደች፡፡
👉እመቤታችን በጾም በጸሎትም የተገኘች የስዕለት ልጅ ናት ፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኀደረ መለኮት (የእግዚአብሔር ማደሪያ) ሆናለች፡፡ ከዚህ በኋላ እመቤታችን በእናት በአባቷ ቤት ፫ ዓመት ተቀመጠች “ከመዝ ነበረት ውስተ ቤተ አቡሃ ወእማ ፫ተ ዓመት እንዘ ትጠቡ ሐሊበ እማ” (እንዳለ በነገረ ማርያም)፡፡
👉ኢያቄምና ሐናም ልጃቸውን ሲያሳድጉ ስላደረገላቸውም ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽመው እያመሰገኑት ፫ ዓመት ኖሩ በጾም እና በጸሎት ተወስነው ለድሆችና ለጦም አደሮች ምጽዋት እየሰጡ በጐ ሥራን አበዙ፡፡
👉ልጃቸውንም ድንግል ማርያምን በንጽሕና ሲያሳድጉ ሦስት ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ሐና ባሏን ኢያቄምን “ወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር ብፅዐት አድርገን እንስጥ። ልጃችን ቤተ እግዚአብሔርን ልታገለግል እንጂ በዚህ ዓለም እኛን ልታገለግል እንዳልተሳልን አስብ አለችው።” ኢያቄምም ይህን ነገር ከሚስቱ በሰማ ጊዜ ደስ አለው።
👉ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ‹‹ልጄ ሆይ ስሚ እይ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን የአባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ ክርስቶስ ውበትሽን /ንጽሐ ባሕርይሽን/ ወድዷልና›› መዝ 44፡10-11 ብሎ እንደተናገረ ለወላጆቿ የብጽአት ልጅ የሆነችው ድንግል ማርያም ከእናት ከአባቷ ተለይታ ታህሣሥ ፫ ቀን በ፫ ዓመቷ ወደ መቅደሰ ኦሪት ገብታለች፡፡
👉 በዓታ ለማርያም ማለትም “የድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ መግባት ማለት ነው፡፡” ካህኑ ዘካሪያስም ስለምትመገበው ምግብ በተጨነቀ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ፋኑኤል ከሰማያት ወርዶ ፩ ክንፉን ጋርዶ ፩ ክንፉን አጐናጽፎ ኅብስቱን አብልቷት ወይኑን አጠጥቷት የብርሃን ጽዋ እና የብርሃን መሶብ ይዞ ወደ ሰማይ ወጥቷል፡፡ እመቤታችንም ከዚህ በኋላ ኅብስት ሰማያዊ እየተመገበች ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከመላአክት ጋር እየዘመረች ፈጣሪዋን እያመሰገነች ፲፪ ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች፡፡
👉የተወደዳችሁ ክርስቲያኖች እንኳን አደረሳችሁ እያልን
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ለበላኤ ሰብዕ የተለመች እመ አምላክ ለኛም ትለመነን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን
ፈጣሪ ሀገራችንብ ኢትዮጵያን ፍፁም ሰላም ያድርግልን 🙏 የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን
1 161
❗️ አስቸኳይ የድረሱልን ጥሪ ❗️
ከዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም
-------------------------------
ምሥራቅ ሸዋ ,ኢትዮጵያ
ታኅሣሥ ፩ ፳፻፲ወ፭ ዓ/ም
የበርካታ መናንያን መኖሪያ ታላቁ የዝቋላ ደብረ ከዋክብት ገዳም "በታጠቁ ኃይሎች" እየታመሰ ይገኛል ፡፡ ማምሻው የታጠቁ ኃይሎት በሁሉም አቅጣጫ ወደ ገዳሙ ሰብረው በመግባት መነኮሳትን በማገት ገዳሙን እያመሱት ይገኛል ፡፡ ሚዲያችን የሚመለከታቸውን አካላት ቦታው ድረስ በመደወል እየደረሰባቸው የሚገኘውን እንግልት እንዲህ በማለት ገልጸዋል "ከገዳሙ የጥበቃ ኃይሎች የሚገኙትን መሣሪያዎች በከበባ ነጥቀዋል፣ ገዳሙን በሁሉም አቅጣጫ በመግባት እያስጨነቁ ይገኛሉ ሦስት አገልጋዮችን አግተዋቸዋል ድረሱል ድረሱል" የሚል ድምፅን አሰምተዋል፡፡ የወረዳ ቤተክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመሆን ለመታደግ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
የሚመለከተው የመንግሥት የጸጥታ መዋቅር በአስቸኳይ የመነኮሳትን እንግልትና የድረሱልን ድምጽ በመስማት አስፈላጊው የፀጥታ ኃይል ወደ ቦታው እንዲልክና ለሀገር የሚጸልዩ መነኮሳትንና ደቀመዛሙርት እንዲታደግ እንጠይቃለን ሲል የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ሚዲያ ገልጿል።
✅ምንጭ፦ማህበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል✝
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 1:39-57፡ "ወተንሥአት ማርያም" - "ማርያምም፡በዚያ፡ወራት፡ተነሥታ፡ወደ፡ተራራማው፡አገር፡ወደ፡ይሁዳ፡ከተማ፡ፈጥና፡ወጣች፥ ወደዘካርያስም፡ቤት፡ገብታ፡ኤልሳቤጥን፡ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም፡የማርያምን፡ሰላምታ፡በሰማች፡ጊዜ፡ፅንሱ፡በማሕፀኗ፡ውስጥ፡ዘለለ፤በኤልሳቤጥም፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሞላባት፥ በታላቅ፡ድምፅም፡ጮኻ፡እንዲህ፡አለች፦አንቺ፡ከሴቶች፡መካከል፡የተባረክሽ፡ነሽ፥የማሕፀንሽም፡ፍሬ፡የተባረከ፡ነው። የጌታዬ፡እናት፡ወደ፡እኔ፡ትመጣ፡ዘንድ፡እንዴት፡ይሆንልኛል? እነሆ፥የሰላምታሽ፡ድምፅ፡በጆሮዬ፡በመጣ፡ጊዜ፡ፅንሱ፡በማሕፀኔ፡በደስታ፡ዘሏልና። ከጌታ፡የተነገረላት፡ቃል፡ይፈጸማልና፥ያመነች፡ብፅዕት፡ናት። ማርያምም፡እንዲህ፡አለች፦ ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ጀምሮ፡ትውልድ፡ሁሉ፦ብፅዕት፡ይሉኛል፤ ብርቱ፡የሆነ፡እርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኃይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡እስራኤልን፡ብላቴናውን፡ረድቷል። ማርያምም፡ሦስት፡ወር፡የሚያህል፡በእርሷ፡ዘንድ፡ተቀመጠች፡ወደ፡ቤቷም፡ተመለሰች። የኤልሳቤጥም፡የመውለጃዋ፡ጊዜ፡ደረሰ፥ወንድ፡ልጅም፡ወለደች።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
ታህሳስ ፫ በቅዳሴ ጊዜ
#ምንባባት
ዕብ ም ፱ ቊ ፩-1፩
፪ዮሐ ም ፩ ቊ፭-፰
ግብ ሐዋ ም ፲፩-፲፭
#ምስባክ
መዝ ፵፬ቊ ፲
ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ እዝነኪ
ርሥኢ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ
እስመ ፈተወ ንጉሥ ሥነኪ
#ትርጉም
ልጄ ሆይ ፣ስሚ እዪ ፤ጆሮሽንም አዘንብዪ፤
ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ
ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና
#ወንጌል
የቅዱስ ሉቃስ ወንጌል ም ፩ ቊ ፴፱-፶፯
#ቅዳሴ
ዘእግዝእትነ(የእመቤታችን ቅዳሴ)
@EOTCW @EOTCW @EOTCW
https://t.me/Eotcw
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 1:1-17 "መጽሐፈ ልደቱ ለእግዚእነ" - "የዳዊት፡ልጅ፡የአብርሃም፡ልጅ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ትውልድ፡መጽሐፍ። አብርሃም፡ይሥሐቅን፡ወለደ፤ይሥሐቅም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ያዕቆብም፡ይሁዳንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ፤ ይሁዳም፡ከትዕማር፡ፋሬስንና፡ዛራን፡ወለደ፤ፋሬስም፡ኤስሮምን፡ወለደ፤ ኤስሮምም፡አራምን፡ወለደ፤አራምም፡ዐሚናዳብን፡ወለደ፤ዐሚናዳብም፡ነአሶንን፡ወለደ፤ነአሶንም፡
ሰልሞንን፡ወለደ፤ ሰልሞንም፡ከራኬብ፡ቦኤዝን፡ወለደ፤ቦኤዝም፡ከሩት፡ኢዮቤድን፡ወለደ፤ኢዮቤድም፡እሴይን፡ወለደ፤ እሴይም፡ንጉሥ፡ዳዊትን፡ወለደ። ሰሎሞንም፡ሮብዓምን፡ወለደ፤ሮብዓምም፡አቢያን፡ወለደ፤አቢያም፡አሣፍን፡ወለደ፤ አሣፍም፡ኢዮሳፍጥን፡ወለደ፤ኢዮሳፍጥም፡ኢዮራምን፡ወለደ፤ኢዮራምም፡ዖዝያንን፡ወለደ፤
9፤ዖዝያንም፡ኢዮአታምን፡ወለደ፤ኢዮአታምም፡አካዝን፡ወለደ፤ አካዝም፡ሕዝቅያስን፡ወለደ፤ሕዝቅያስም፡ምናሴን፡ወለደ፤ምናሴም፡አሞፅን፡ወለደ፤ አሞፅም፡ኢዮስያስን፡ወለደ፤ኢዮስያስም፡በባቢሎን፡ምርኮ፡ጊዜ፡ኢኮንያንንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ። ከባቢሎንም፡ምርኮ፡በዃላ፡ኢኮንያን፡ሰላትያልን፡ወለደ፤ሰላትያልም፡ዘሩባቤልን፡ወለደ፤ ዘሩባቤልም፡አብዩድን፡ወለደ፤አብዩድም፡ኤልያቄምን፡ወለደ፤ኤልያቄምም፡አዛርን፡ወለደ፤ አዛርም፡ሳዶቅን፡ወለደ፤ሳዶቅም፡አኪምን፡ወለደ፤አኪምም፡ኤልዩድን፡ወለደ፤ ኤልዩድም፡አልዓዛርን፡ወለደ፤አልዓዛርም፡ማታንን፡ወለደ፤ማታንም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ ያዕቆብም፡ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡የወለደች፡የማርያምን፡ዕጮኛ፡ዮሴፍን፡ወለደ። እንግዲህ፡ትውልድ፡ሁሉ፡ከአብርሃም፡እስከ፡ዳዊት፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከዳዊትም፡እስከባቢሎን፡ምርኮ፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከባቢሎንም፡ምርኮ፡እስከ፡ክርስቶስ፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፡ነው።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
ምስባክ ዘታህሳስ ፫ ነግህ
እበውዕ ቤተከ ምስለ መባዕየ
ወእሁብ ብፅዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ
ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ
መዝ ፷፭ ቊ፲፬
መባዬን ይዤ ወደ ቤትህ እገባለሁ
በመከራዬ ጊዜ በአፌ የተናገርሁትን በከንፈሮቼም ያልሁትን ስእለቴን ለአንተ እሰጣለሁ
@EOTCW @EOTCW @EOTCW
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጽያዊው ጻድቅ ለታላቁ አባት ለአቡነ ዜና ማርቆስ ለዕረፍታቸው ዓመታዊ ክብረ በዓላቸው በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ ስለ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ዕረፍት፦ በታኅሣሥ ወር በሦስተኛው ዕለት ዐርብ ጥዋት ይኸውም እመቤታችን ቅድስት ድግንል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበትና የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል በዓል በሆነበት ቀን። ያን ጊዜ ለነግህ ጸሎት እጆቹን ዘረጋ፤ በመንግሥት የተካከሉ፥ አንድ አምላክ የሆኑ፥ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ታላቅ ጻድቅ ወደሆነ አባታችን ዜና ማርቆስ ወረዱ፥ በሰማያት የሚኖሩ ሠራዊቶቻቸውም ሁሉ መልካም ጣፋጭ መዓዛም ሸተተ፤ ይህም መዓዛው ታላቁ የዠማ ወንዝ እስከ ምሁር አውራጃ ድረስ አርባ ቀን ያህል ኖረ። በዚህም ሰማያዊ ሽቱ መዓዛ ከጣዕሙ ኃይል የተነሣ የሞት ፃዕር ሳያገኛት መልአከ ሞትም ሳያስደነግጠመት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች።
❤ ሰውን የሚወድ የጻድቃን ሞገሳቸው፣ የመነኰሳት ተስፋቸው፥ የሰማዕታት አክሊላቸው የሆነ ቸር አምላካችን እግዚአብሔር በእጆቹ ውስጥ ተቀበላት አቅፎም ንጹሕ ቅዱስ በሆነ አፉ ሳማት። ነፍሱም አክሊል ተቀዳጅታ በሰማይ ወደአለች ብርሃናዊት አዳራሽ ከጌታችን፣ ከቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጋር ዐረገች።
❤ ያን ጊዜም ንጹሕ ክብር የሆነ ሥጋውን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይቀብሩ ዘንድ መነኰሳት ልጆቹ ተሰበሰቡ ያን ጊዜም፦ "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ ጣዕም ባለው ታላቅ ድምፅ ሲዘምሩ የልዑል እግዚአብሔር መላእክትን ሰሙአቸው። ዳግመኛም "በዘይት ሃይማኖቱ ለኢትዮጵያ ያበራላት የዚህ የዜና ማርቆስ በዓል በደስታ እናክብር። አሁንም የዘይት ዛፍ ሃይማኖት የተባለ የዜና ማርቆስን በዓል በታላቅ ክብር እግዚአብሔርን እያመሰገን ዛሬ እናክብ" አሉ። እዲህም የሚሉ ነበሩ፦ "ጻድቅ ሰው እንደ ዘንባባ ያፈራል በደጋ እንዳለ ዝግባም ይዛል" ሌሎችም እንዲህ የሚሉ ነበሩ፦ "በዓለም ሳለ በገድል፣ በትሩፋት የደከሙ በፈጣሪያችን እግዚአብሔር ፊቴ ለዘለዓለሙ ሕያው ሁኖ ይኖራል ጥፋትን አያይምና"።
❤ ዳግመኛ እንዲህ የሚሉ ነበሩ፦ "በጽዮን ደብረ ብሥራት ዘር ያለው ዜና ማርቆስ ብፁዕ ነው። ይህቺም ዳግሚት ደብረ ዘይት የተባለች የዜና ማርቆስ ገዳም የከበረች ደብረ ብሥራት ናት"። የአባታችን ዜና ማርቆስ መነኰሳት ልጆቹ ይህን የመላእክት ምስጋና በሰሙ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው፤ እነርሱም እግዚአብሔር አመሰገኑት፤ የገድሉንም መጽሐፍ ሁሉ ጻፉ። ይህንም የመላእክት ምስጋና ከሚዘምሩበት መጽሐፋቸው ውስጥ ጻፉቱ። በዚህም የመላእክት ምስጋና በመንፈሳዊ አባታችን ዜና ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውሰረጥ ሲዘምሩ ኖሩ።
❤ ደቀ መዛሙርቱም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል በአገኘባት በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአነጻት በደብረ ብሥራት ቤተ ክርስቲያን በስተቀኝ በኩል በታላቅ ክብር ሥጋውን አስቀመጡ። ደሙን በማፍሰስ በእውነት ሰማዕት የሆነ፣ በትዕግሥቱ ጻድቅ የሆነ፣ ለኢትዮጵያ አገር ብርሃን በሆነ ሃይማኖቱና ትምህርቱ ያበራ፤ አራቱን ወንጌላት ዙሮ ያስተማረ ታላቅ ሐዋርያ የሆነ፣ ሙሴ የጸፈውን ዐሠርቱ ቃላተ ኦሪትን የሚያሰተምር ነቢይና ካህን የሆነ፣ በሚያመለክተው ትንቢቱ ከእግዚአብሔር ዘንድ በጎ ነገር የሚመጣለት፣ በአደረበት መንፈስ ቅዱስ ራእይን የሚያይ፣ በሹመቱ ወራት ሃይማኖት ጽናትና የበጎ ሥራ መስፋፋት የተደረገበት ታላቅ ሊቀ ካህናት የሆነ፤ የአባታችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ የምስጋና ቃል ይህ ነው። ከአባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ምዕራፍ 33።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
ወገን ጐልማሳም ቢሆን ሽማግሌም ቢሆን ሚስቱ የሞተችበት ሁሉ በኢየሩሳሌም ወደአለ ቤተ መቅደስ ይሒድ እያለ ዓዋጅን ዙረው የሚናገሩ በእስራኤል አገር ሁሉ ላከ።
❤ ከዳዊት ወገን የሆነ ጠራቢው ዮሴፍም በሰማ ጊዜ በትሩን ይዞ ከናዝሬት ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ካህኑ ዘካርያስም የሁሉንም በትሮች ተቀብሎ ስማቸውን በላያቸው ጻፈ ቊጥራቸውም አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሆነ ዘካርያስም በትሮችን ወደ ቤተ መቅደስ አስገብቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ እንዲሁም ሰዎች ሁሉ ከቤተ መቅደስ ውጭ ቁመው ይጸልዩ ነበር ዘካርያስም ጸሎቱን በፈጸመ ጊዜ ለየአንዳንዱ በትራቸውን አውጥቶ ሰጠ ጠራቢው ዮሴፍም በትሩን ሊቀበል በቀረበ ጊዜ ከእርሷ ነጭ ርግብ የመሰለች ተገለጠች እየበረረችም ሒዳ በጠራቢው ዮሴፍ ራስ ላይ ተቀመጠች ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ አይተው እጅግ አደነቁ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔር አመሰገኑት።
❤ ዘካርያስ ዮሴፍን "ዮሴፍ ሆይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እንደ ተናገረ ድንግል ማርያምን ወደ ቤትህ ወስደህ ጠብቃት" አለው። ዮሴፍም ቅድስት ድንግል ማርያምን ከካህናት እጅ ተቀበላት በእርሱም ዘንድ ኖረች። ከዚህም በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ስለ እግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ሁኖ ስለመወለዱ በዮሴፍ ቤት አበሠራት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን በማርያም በአማላጅነቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ተአምረ ማርያም ተአምር 15ና የታኅሣሥ3 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ንጽሕተ ንጹሓን ከዊና ከመ ታቦተ ዶር ዘሲና ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በድንግልና ሲሳያ ኅብስተ መና ወስቴሃኒ ስቴ ጽመና"። ትርጉ፦ እንደ ሲናው የእሳታዊ መለኮት ማደሪያ (ታቦት ዘዶር) ከንጹሐን ይልቅ የነጻች ኹና በቤተ መቅደስ ውስጥ በድንግልና ኖረች (ተቀመጠች) ምግቧ ኅብስተ መና (ሰማያዊ ኅብስት) ነው፤ መጠጧም ልባም (ባለ ዕውቀት) የሚያደርግ የጸጥታ መጠጥ ነው። የቅዱስ ያሬድ ዚቅ የታኅሣሥ3 ና አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታቱ ኵሎም ዘኪዳነ ምሕረት ወዘፍልሰታ ላይ።
+ + +
❤ "ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ አዋልደ ዕብራውያን እለ ያገዝፋ ክሣዶን አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበርኪ። ኦ ድንግል አኮ ኅብስተ ምድራዌ ዘተሴሰይኪ አላ ኅብስተ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘበሰለ። ኦ ድንግል አኮ ስቴ ምድራዌ ዘሰተይኪ አላ ስቴ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘተቀድሖ"። ትርጉም፦ ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም። በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ። ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስን የተመገብሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ። ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እጅ። አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ቁጥር 39-41።
+ + +
❤ የዕለቱ ማኅሌቱ ምስባክ፦ "እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ። ወእሁብ ብጽዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ። ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ"። መዝ65፥13-14። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-17።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ። ርስዒ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ። እስመ ፈተወ ንጉሥ ስነኪ"። መዝ 44፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 9፥1-11፣ 2ኛ ዮሐ 1፥5-8 እና የሐዋ ሥራ 1፥12-15። የሚነበበው ወንጌልን ሉቃ 1፥39-57። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓታ ለማርያም በዓል፤ የቅዱስ ፋኑኤል በዓል፣ የአቡነ ዜና ማርቆስ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን አምላክን ለወለደች ለእናታች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ ለገባችበት (ለበዓታ ለማርያም) በዓል፣ ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ፋኑኤል እመቤታችንን ሰማያዊ መናና መጠጥን ለመገበበትና ላጠጣበት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ጽርሕ ንጽሕት ማርያም ተፈሥሒ ሀገረ እግዚአብሔር ቃል ቅዱስ ይወጽእ እምኔኪ አዕላፍ መላእክት ይትለአኩኪ"። ትርጉም፦ ንጽሕት አዳራሽ ማርያም ደስ ይበልሽ፤ የእግዚአብሔር አገር ቅዱስ የኾነው አካላዊ ቃል ካንቺ ይወጣል፤ አእላፍ መላእክት ያገለግሉሻል"።
+ + +
❤ የዕለቱ አቡን፦ ሃሌ ሉያ በ፰ "እኅትነ ይብልዋ ወይኬልልዋ ነያ ሐዳስዩ ጣዕዋ ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪሃ፣ አዝ ፤ከመ ቅርፍተ ሮማን መላትሒሃ፣ አዝ፤ልዑል ሠምራ ዳዊት ዘመራ በቤተ መቅደስ ተወክፍዋ። ትርጉም፦ እኅታችን ይሏታል ይጋርዷታል እነኋት አዲሲቱ እንቦሳ እያሉ ያመሰግኗታል። ከከናፍሮቿ የማር ወለላ ይፈሳል፤ ጉነጮቿ እንደ ሮማን ቅርፊት ናቸው፤ ልዑል ወደዳት፤ ዳዊት ዘመረላት በቤተ መቅደስ ተቀበሏት። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ የእመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ መግባት፦ እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝ ሆነች። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች "የሰጠህኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርገዋለሁ"።
❤ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻች ጊዜ በንጽሕና ሲያሳድጉ ሦስት ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ሐና ባሏን ኢያቄምን "ወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር ብፅዓት አድርገን እንስጥ ልጃችን ቤተ እግዚአብሔር ልታገለግል እንጂ በዚህ ዓለም እኛን ልታገለግ እንዳልተሳልን አስብ" አለችው። ኢያቄብም ይህን ነገር ከሚስቱ ከሐና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ለመንገድ የሚሆነውን ስንቅና ለቤተ እግዚአብሔር የሚሆነውንም መባዓ ሁሉ አዘጋጀ ቤተ ሰቦቻቸውንና ወዳጆቻቸውን ዘመዶቻቸውንም ሁሉ ጠሩ ልጃቸው ይዘው ሄደው ወደ ቤተ መቅደስ አገቧት።
❤ ካህናቱና በቤተ መቅደስም ያሉ ሁሉ በሰሙ ጊዜ እነሱን ለመቀበል ወጥተው መንፈሳዊ ሰላምታ ሰጡቸው ኢያቄምንና ሚስቱ ሐናን ልጃቸውን ማርያምንም አመሰገንዋቸው በአንብሮተ እድ ፈጽመው ባረኳቸው "እግዚአብሔር ኀዘናችሁን በዕውነት ተቀብሏችኋል የተመረጠች በምትሆን በዚች ልጅም ደስ አሰኝቷችኋል" አሏቸው።
❤ በዚህም ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ስለ ምግቧ ነገር ቢያዝልኝ ብሎ በማሰብ ደወል አስደወለና ሕዝቡ ሁሉ እንዲሰበሰብ አደረገ። በዚያም ጊዜ ሕዝቡ በተሰበሰበበት አደባባይ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል ሰማያዊ ኅብስት ሰማያዊ ጽዋ ይዞ በአየር ላይ ረቦ ታየ። ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም "ዛሬስ የእስራኤል አምላክ ክብሬን በዚህ ሕዝብ መካከል ሊገልጽልኝ ፈቅዷል" በማለት ኅብስቱንና ጽዋውን ሊቀበል ተነሣ። መልአኩ ግን ወደ ላይ ሰቀቀበት መጠቀበት። ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም ሐናን ጠርቶ "ለእናንተ ለእግዶቹ የወረደ ክብር ይሆናልና ሕፃኗን ይዘሽ ከዚህ እኛ ካለንበት ቦታ ፈቀቅ ወይም እልፍ ብለሽ ተቀመጭ" አላት ሐናም ልጅዋን ይዛ ፈቀቅ ብላ ተቀመጠች። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል ግን ከሐና እና ከልጅዋ ራስ በላይ ረቦ ቆየ እንጂ አልወረደም።
❤ ዳመኛም ዘካርያስ ሐናን "የእግዚአብሔር ምስጢር አይመረመርምና ልጅቷን ከዚያው ትተሻት ተመልሰሽ ነይ" አላት። ሐናም ብላቴናቱን በዚያው ትታት ወደ እነሱ ተመልሳ መጣች በዚያን ጊዜ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል ወርዶ ክንፎቹን አጎናጽፏት ከመሬት ወደላይ የሰው ቁመት ያህል ከፍ ብሎ ኅብስቱን መግቧት ጽዋውን አጠጥቷት ወደ ሰማይ ዐረገ።
❤ ከዚህም በኋላ ዘካርያስና የአይሁድ ሊቃውንትም የምገሰቧ ነገር ከተያዘልንስ ከሰው ጋራ ምን ያጋፋታል ቦታዋ ወይም መኖሪያዋ በቤተ መቅደስ ይሁን እንጂ ብለው ዙፋን ዘርግተው ስጋጃውን አንጥፈው ምስጋና የባሕርዩ የሆነ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በታላቅ ክብር ወደ ቤተ መቅደስ አገቧት በብላቴናይቱ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል ተገልጿልና።
❤ በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ። ከሴቶች ሁሉ የተመረጠች ይቺ ናት በቤተ መቅደስም በመኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲፈጸምላት እርሷ ለእግዚአብሔር የተሰጠች የስለት ልጅ ናትና ለሚጠብቃት ይሰጧት ዘንድ ካህናት እርስበርሳቸው ተማከሩ በሴቶች ላይ የሚደርስ በርሷ ላይም ይደርስባታል ብለው ስለፈሩ በቤተ መቅደስ ውስጥ ይተዋት ዘንድ ለእርሱ ትክክል መስሎ አልታያቸውም ስለዚህም ሊጠብቃት ለሚገባው በእርሷ ላይ እጮኛ ሊአኖሩ ወደዱ።
❤ ከዚህም አስቀድሞ ሊቀ ካህናት ዘካርያስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ልጄ ማርያም ሆይ አንቺ እንዳደግሽና ለካለ መጠን እንደደረስሽ ዕወቂ ልትታጪ ትወጃለሽን እግዚአብሔርን የሚፈራ መልካም የሆነ የተባረከ ጐልማሳ እንፈልግልሽን ወይም በሕይወትሽ ዘመን ሁሉ በቤተ መቅደስ ተቀምጠሽ እግዚአብሔርን ልታገለግዪው የምትሺ ከሆነ በሴቶች ላይ የሚደርሰው በሚደርስብሽ ወራት ወደ ቤተ መቅደስ ደጅ ከመግባት ትጠበቂ ዘንድ በኦሪቱ የተጻፈውን የርግማን ሥርዓት በአንቺ ላይ እንሠራለን" አላት። ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም "እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋዩ በፊታችሁ ነኝ አባትና እናትም የሉኝም ስሙ ቡሩክ ምስጉን ከሆነ ከእግዚአብሔር በታች በእናትና አባት ፈንታ እናንት ናችሁና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንደምታውቁ አድርጉ" ብላ መለሰች።
❤ ካህናቱና ማኅበሩም ሁሉ ዘካርያስን "ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ስለዚች ብላቴና ማርያም ወደ እግዚአብሔር ጸልይ" አሉት። ዘካርያስም ገብቶ ሲጸልይ በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና እንዲህ አለው "ዘካርያስ ሆይ ወጥተህ ከዳዊት ወገን ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን ሁሉ ወንዶች ሰብስብ የየአንዳንዱንም በትር ከስሙ ጋር ውሰድ ወደ ቤተ መቅደስም በምሽት አግብተህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይበት በነጋ ጊዜም በትሮቻቸውን አውጣ እግዚአብሔርም በበትሩ ላይ ምልክት ለገለጠልህ ለዚያ ሰው ማርያምን ተቀብሎ ሊጠብቃት ይገባዋል"። ካህኑ ዘካርያስም ወጥቶ አንድነት ለተሰበሰቡ ሕዝቡ የእግዚአብሔር መልአክ የነገረውን ነገራቸው በዚያንም ጊዜ ከዳዊት
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ዮሐ. 9:1-12፡ "ወእንዘ የሐልፍ እምህየ " - "ሲያልፍም፡ከመወለዱ፡ጀምሮ፡ዕውር፡የሆነውን፡ሰው፡አየ። ደቀ፡መዛሙርቱም፦መምህር፡ሆይ፥ይህ፡ሰው፡ዕውር፡ሆኖ፡እንዲወለድ፡ኃጢአት፡የሠራ፡ማን፡
ነው? እርሱ፡ወይስ፡ወላጆቹ፧ብለው፡ጠየቁት። ኢየሱስም፡እንዲህ፡ብሎ፡መለሰ፦የእግዚአብሔር፡ሥራ፡በእርሱ፡እንዲገለጥ፡ነው፡እንጂ፡እርሱ፡ወይም፡
ወላጆቹ፡ኃጢአት፡አልሠሩም። ቀን፡ሳለ፡የላከኝን፡ሥራ፡ላደርግ፡ይገባኛል፤ማንም፡ሊሠራ፡የማይችልባት፡ሌሊት፡ትመጣለች። በዓለም፡ሳለሁ፡የዓለም፡ብርሃን፡ነኝ። ይህን፡ብሎ፡ወደ፡መሬት፡እንትፍ፡አለ፡በምራቁም፡ጭቃ፡አድርጎ፡በጭቃው፡የዕውሩን፡ዐይኖች፡ቀባና፦ ሂድና፡በሰሊሖም፡መጠመቂያ፡ታጠብ፡አለው፤(ትርጓሜው፡'የተላከ'፡ነው)። ስለዚህ፡ሄዶ፡ታጠበ፥እያየም፡መጣ። ጎረቤቶቹም፡ቀድሞም፡ሲለምን፡አይተውት፡የነበሩ፦ይህ፡ተቀምጦ፡ይለምን፡የነበረ፡አይደለምን? አሉ። ሌላዎች፦ እርሱ፡ነው፡አሉ፤ ሌላዎች፦አይደለም፡እርሱን፡ይመስላል፡እንጂ፡አሉ፤እርሱ፦እኔ፡ነኝ፡አለ። ታድያ፦ዐይኖችህ፡እንዴት፡ተከፈቱ፧አሉት። እርሱ፡መልሶ፦ኢየሱስ፡የሚባለው፡ሰው፡ጭቃ፡አድርጎ፡አይኖቼን፡ቀባና፦ወደሰሊሖም፡መጠመቂያ፡ሄደህ፡ታጠብ፡አለኝ፤ሄጄ፡ታጥቤም፡አየሁ፡አለ። ያ፡ሰው፡ወዴት፡ነው? አሉት፦አላውቅም፡አለ። በፊት፡ዕውር፡የነበረውን፡ሰው፡ወደ፡ፈሪሳውያን፡ወሰዱት። ኢየሱስም፡ጭቃ፡አድርጎ፡ዐይኖቹን፡የከፈተበት፡ቀን፡ሰንበት፡ነበረ። ስለዚህ፥ፈሪሳውያን፡ደግሞ፡እንዴት፡እንዳየ፡እንደ፡ገና፡ጠየቁት። ርሱም፦ ጭቃ፡በዐይኖቼ፡አኖረ፥ታጠብኹም፥አያለኹም፡አላቸው። ከፈሪሳውያንም፡አንዳንዶቹ፦ይህ፡ሰው፡ሰንበትን፡አያከብርምና፡ከእግዚአብሔር፡አይደለም፡አሉ።ሌላዎች፡ግን፦ኀጢአትኛ፡ሰው፡ እንደነዚህ፡ያሉ፡ምልክቶች፡ሊያደርግ፡እንዴት፡ይችላል፧አሉ። በመካከላቸውም፡መለያየት፡ኾነ። ከዚህም፡የተነሣ፡ዕውሩን፦አንተ፡ዐይኖችኽን፡ስለከፈተ፡ስለ፡ርሱ፡ምን፡ትላለኽ? ደግሞ፡አሉት።ርሱም፦ነቢይ፡ነው፡አለ። አይሁድ፡የዚያን፡ያየውን፡ወላጆች፡እስኪጠሩ፡ድረስ፡ዕውር፡እንደ፡ነበረ፡እንዳየም፡ስለ፡ርሱ፡
አላመኑም፥ እነርሱንም፦እናንተ፡ዕውር፡ኾኖ፡ተወለደ፡የምትሉት፡ልጃችኹ፡ይህ፡ነውን፧ታድያ፡አኹን፡እንዴት፡ያያል፧ብለው፡ጠየቋቸው። ወላጆቹም፡መልሰው፦ይህ፡ልጃችን፡እንደ፡ኾነ፡ዕውርም፡ኾኖ፡እንደ፡ተወለደ፡እናውቃለን፤ ዳሩ፡ግን፡አኹን፡እንዴት፡እንዳየ፡አናውቅም፥ወይም፡ዐይኖቹን፡ማን፡እንደ፡ከፈተ፡እኛ፡አናውቅም፤ ጠይቁት፡ርሱ፡ሙሉ፡ሰው፡ነው፤ርሱ፡ስለ፡ራሱ፡ይናገራል፡አሉ። ወላጆቹ፡አይሁድን፡ስለ፡ፈሩ፡ይህን፡አሉ፤ርሱ፡ክርስቶስ፡ነው፡ብሎ፡የሚመሰክር፡ቢኖር፡ከምኵራብ፡እንዲያወጡት፡አይሁድ፡ከዚህ፡በፊት፡ተስማምተው፡ነበርና። ስለዚህ፥ወላጆቹ፦ሙሉ፡ሰው፡ነው፥ጠይቁት፡አሉ። ስለዚህ፥ዕውር፡የነበረውን፡ሰው፡ኹለተኛ፡ጠርተው፦እግዚአብሔርን፡አክብር፤ይህ፡ሰው፡ኀጢአተኛ፡መኾኑን፡እኛ፡እናውቃለን፡አሉት። ርሱም፡መልሶ፦ኀጢአተኛ፡መኾኑን፡አላውቅም፤ ዕውር፡እንደ፡ነበርኹ፡አኹንም፡እንዳይ፡ይህን፡አንድ፡ነገር፡ዐውቃለኹ፡አለ። ደግመውም፦ምን፡አደረገልኽ፧እንዴትስ፡ዐይኖችኽን፡ከፈተ፧አሉት። ርሱም፡መልሶ፦አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ፡አልሰማችኹምም፤ስለ፡ምን፡ዳግመኛ፡ልትሰሙ፡ትወዳላችኹ፧እናንተ፡ደግሞ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ልትኾኑ፡ትወዳላችኹን፧አላቸው። ተሳድበውም፦አንተ፡የርሱ፡ደቀ፡መዝሙር፡ነኽ፥እኛ፡ግን፡የሙሴ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ነን፤ እግዚአብሔር፡ሙሴን፡እንደ፡ተናገረው፡እኛ፡እናውቃለን፥ይህ፡ሰው፡ግን፡ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡
አናውቅም፡አሉት። ሰውዬው፡መለሰ፡እንዲህም፡አላቸው፦ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡እናንተ፡አለማወቃችኹ፡ይህ፡ድንቅ፡ነገር፡ነው፥ ዳሩ፡ግን፡ዐይኖቼን፡ከፈተ። እግዚአብሔርን፡የሚፈራ፡ፈቃዱንም፡የሚያደርግ፡ቢኖር፡ያንን፡እግዚአብሔር፡ይሰማዋል፡እንጂ፡
ኀጢአተኛዎችን፡እንዳይሰማ፡እናውቃለን። ዕውር፡ኾኖ፡የተወለደውን፡ዐይኖች፡ማንም፡እንደ፡ከፈተ፡ዓለም፡ከተፈጠረ፡ዠምሮ፡አልተሰማም፤ ይህ፡ሰው፡ከእግዚአብሔር፡ባይኾን፡ምንም፡ሊያደርግ፡ባልቻለም፡ነበር። መልሰው፦አንተ፡ዅለንተናኽ፡በኀጢአት፡ተወለድኽ፥አንተም፡እኛን፡ታስተምረናለኽን፧አሉት።ወደ፡ውጭም፡አወጡት። ኢየሱስም፡ወደ፡ውጭ፡እንዳወጡት፡ሰማ፤ሲያገኘውም፦አንተ፡በእግዚአብሔር፡ልጅ፡
ታምናለኽን፧አለው። ርሱም፡መልሶ፦ጌታ፡ሆይ፥በርሱ፡አምን፡ዘንድ፡ማን፡ነው፧አለ። ኢየሱስም፦አይተኸዋልም፡ከአንተ፡ጋራም፡የሚናገረው፡ርሱ፡ነው፡አለው። ርሱም፦ጌታ፡ሆይ፥አምናለኹ፡አለ፤ሰገደለትም። ኢየሱስም፦ የማያዩ፡እንዲያዩ፡የሚያዩም፡እንዲታወሩ፡እኔ፡ወደዚህ፡ዓለም፡ለፍርድ፡መጣኹ፡አለ። ከፈሪሳውያንም፡ከርሱ፡ጋራ፡የነበሩት፡ይህን፡ሰምተው፦እኛ፡ደግሞ፡ዕውሮች፡ነንን? አሉት። ኢየሱስም፡አላቸው፦ዕውሮችስ፡ብትኾኑ፡ኀጢአት፡ባልኾነባችኹም፡ነበር፤አኹን፡ግን፦ እናያለን፡ትላላችኹ፤ኀጢአታችኹ፡ይኖራል።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
02/1/2015 ዓ.ም (፪/፩/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ደቂቀ እጓለ እመሕያው እስከ ማእዜኑ ታከብዱ ልበክሙ።
ለምንት ታፈቅሩ ከንቶ ተሐሱ ሐሰተ።
አእምሩ ከመተሰብሖ እግዚአብሔር በጻድቁ። መዝ. 4÷2
🕯 ትርጉም
እናንት የሰው ልጆች እስከ መቼ ድረስ ልባችሁን ታከብዳላችሁ?
እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ ዕወቁ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 6:35-48፡ "ወይእዜኒ አፍቅሩ ጸላእተከ" - "ነገር፡ግን፥ጠላቶቻችኹን፡ውደዱ፤መልካም፡አድርጉ፤ ምንም፡ተስፋ፡ሳታደርጉም፡አበድሩ፥ዋጋችሀም፡ ታላቅ፡ይሆናል፥የልዑልም፡ልጆች፡ትሆናላችሁ፥እርሱ፡ለማያመሰግኑ፡ለክፉዎችም፡ቸር፡ነውና። አባታችሁ፡ርኅሩኅ፡እንደ፡ሆነ፡ርኅሩሆች፡ሁኑ። አትፍረዱ። አይፈረድባችሁምም፤ አትኰንኑ፡አትኰነኑምም። ይቅር፡በሉ፡ይቅርም፡ትባላላችሁ። ስጡ፡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት፡መስፈሪያ፡ተመልሶ፡ይሰፈርላችኋልና፥የተጨቈነና፡የተነቀነቀ፡
የተትረፈረፈም፡መልካም፡መስፈሪያ፡በዕቅፋችሁ፡ይሰጣችኋል። ምሳሌም፡አላቸው፦ዕውር፡ዕውርን፡ሊመራ፡ይችላልን፧ሁለቱ፡በጕድጓድ፡አይወድቁምን፧ ደቀ፡መዝሙር፡ከመምህሩ፡አይበልጥም፤ፈጽሞ፡የተማረ፡ሁሉ፡ግን፡እንደ፡መምህሩ፡ይሆናል። በወንድምህም፡ዐይን፡ያለውን፡ጕድፍ፡ስለ፡ምን፡ታያለኽ፥በራስህ፡ዐይን፡ግን፡ያለውን፡ምሰሶ፡ስለ፡
ምን፡አትመለከትም? በዐይንህ፡ያለውን፡ምሰሶ፡ራስህ፡ሳታይ፥እንዴት፡ወንድምህን፦ወንድሜ፡ሆይ፥በዐይንህ፡ያለውን፡ጕድፍ፡ላውጣ፡ፍቀድልኝ፡ልትል፡ትችላለህ? አንተ፡ግብዝ፥አስቀድመህ፡ከዐይንህ፡ምሰሶውን፡አውጣ፡ከዚያም፡በኋላ፡በወንድምህ፡ዐይን፡ያለውን፡ጕድፍ፡ታወጣ፡ዘንድ፡አጥርተህ፡ታያለህ። ክፉ፡ፍሬ፡የሚያደርግ፡መልካም፡ዛፍ፡የለምና፥እንዲሁም፡መልካም፡ፍሬ፡የሚያደርግ፡ክፉ፡ዛፍ፡የለም። ዛፍ፡ሁሉ፡ከፍሬው፡ይታወቃልና፤ ከሾህ፡በለስ፡አይለቅሙም፥ከዐጣጥ፡ቍጥቋጦም፡ወይን፡አይቈርጡም። በልብ፡ሞልቶ፡ከተረፈው፡አፉ፡ይናገራልና፥መልካም፡ሰው፡ከልብ፡መልካም፡መዝገብ፡መልካሙን፡ያወጣል፥ክፉ፡ሰውም፡ከልብ፡ክፉ፡መዝገብ፡ክፉውን፡ያወጣል። ስለ፡ምን፦ጌታ፡ሆይ፥ጌታ፡ሆይ፥ትሉኛላችሁ፥የምለውንም፡አታደርጉም? ወደ፡እኔ፡የሚመጣ፡ዅሉ፡ቃሌንም፡ሰምቶ፡የሚያደርገው፥ማንን፡እንዲመስል፡አሳያችኋለሁ። ቤት፡ሲሠራ፡አጥልቆ፡የቈፈረ፡በአለት፡ላይም፡የመሠረተ፡ሰውን፡ይመስላል።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
