Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Открыть в Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Больше3 591
Подписчики
+324 часа
+67 дней
+4430 день
Архив постов
📓ጥብቅ ማስታወቂያ ለጋራ መኖሪያ ህንፃ ግንባታ ለተመዘገባችሁ ስራ ተቋራጮች በሙሉ
+9
ለግንባታ ግብዓት (የአርማታ ብረት እና የሬዲሚክስ ኮንክሪት አቅራቢዎች) የቀረበ ጥሪ!!
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዋጅ ቁጥር 84/2016 በአንቀጽ 22 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በካፒታል ፕሮጀክት ቤቶችን እንደሚገነባ ይታወቃል።
በዚሁ መሰረት በያዝነው በ2018 በጀት ዓመት በከተማ አስተዳደሩ 100 ሺህ ቤቶችን በፍጥነትና በጥራት ገንብቶ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ነድፎ ወደ ትግበራ ገብቷል ስለሆነም ለ100 ሺህ ቤቶች በቂ የሆነ የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እንዲኖር ከብረትና አጠቃላይ የኮንክሪት ስራ ግብዓት አቅራቢዎች ጋር መወያየት የሚፈልግ በመሆኑ በስራው ላይ የተሰማራችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በሙሉ ግሪክ ክለብ አጠገብ በሚገኘው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮዉ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋናው መስሪያ ቤት ማለትም እሁድ በ05/04/2018 ዓ.ም ጠዋት 2:30 ላይ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን ።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ-የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
+6
B&F እምነበረድ እና ግራናይት ማመረቻ እና መሸጫ
እምነበረድ በተመጣጣኝ ዋጋ
እናቀርባለን
_ጎጃም እምነበረድ በካሬ 4500 ብር
_black stone በካሬ 4800 ብር
_Limestone በካሬ 2900 ብር
_የአክሱም ግራናይት በካሬ 6500ብር
ሰልክ
09,82,17,40,64
Telegram username
@Marble2233
ስለ ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ግልጽ ጨረታ: መመሪያ ቁጥር 1073/2017 የፌዴራል መንግሥት የግዥ አፈፃፀም መመሪያ መሠረት
54/ለ/ ግዥው በሀገር ውስጥ ባሉ ተጫራቾች ሊሟላ የሚችል ሲሆን ግምታዊ ዋጋው ከሚከተለው የገንዘብ መጠን ያልበለጠ ሲሆን፣
1) ለግንባታ ሥራ ዘርፍ እስከ 3,000,000,000.00 (ሦስት ቢሊዮን ብር)
2) ለዕቃ ግዥ እስከ ብር 1,000,000,000.00 (አንድ ቢሊዮን ብር)
3) ለምክር አገልግሎት ግዥ እስከ ብር90,000,000.00 (ዘጠና ሚሊዮን ብር)
4) ከምክር ውጪ የሆኑ አገልግሎት ግዥ እስከ ብር 250,000,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን ብር)
Clause 54 , page 69
Cost Breakdown example pdf
https://t.me/cotm2022
🔺ታምራት ፕሌት እና ጄቦልት አቅራቢ🏗
📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን
✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና ማጠፊያ ማሽኖች አሉን
🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን
📐ማንኛዉንም የሞደፊክ ስራዎችን እንሰራለን
📍ኢትዮጵያ ዉስጥ የትም እንልክሎታለን!
➕➕➕➕➕➕➕➕➕
📍አድራሻችን፦ ቁ.1 አዉቶብስ ተራ(መሳለሚያ)
ቁ.2 መርካቶ
ቁ.3 ተክለሀይማኖት
📞0904040477
📞0911016833
👉በስራ ላይ ከሚገጥሙን አንዳንድ ከውል አስተዳደር ጋር የተያያዙ ነገሮችን በጥያቄ መልክ እንይ፦
1) ስራ ለመስራት የተዋዋለ ተቋራጭ ድርጅት ሊከፈለው የሚገባ ክፍያ አንሶ እንዲከፈለው ቢደረግ የሚሰራውን ስራ ሊያቆም ይችላል?
2) በተቆጣጣሪ መሀንዲስ የተፈቀደ የኮንትራት ጊዜ ማራዘሚያ ውል ሰጪው ድርጅት (Client) ሊከለክል ይችላል?
3) ተቆጣጣሪ መሀንዲስ የተረጋጋጠ የዕዳ (Negative) የክፍያ ሰርተፍኬት መስጠት ይችላል?
Explanation:-
👉ከላይ ተዘረዘሩትን የኮንስትራክሽን ውል ጉዳዮች አንድ በአንድ እንመልከት።
1) Where a sum due under a contract is not paid in full by the final date for payment and no effective notice to withhold payment has been given, the person to whom the sum is due has the right (without prejudice to any other right or remedy) to terminate the performance of his obligations under the contract to the party by whom payment ought to have been made. የውል ሰጪው ድርጅት/ግለሰብ (Client) ተቋራጭ ድርጅቱ ስላልተከፈለ ክፍያ የሚገልፅ ደብዳቤ ደርሶት በ45 ቀን ውስጥ ተገቢውን ክፍያ ያልፈፀመ እንደሆነ ተቋራጭ ድርጅቱ ከ30 ቀን ያላነሰ ጊዜ በውስጥ ውሉን ስለማቋረጥ የሚገልፅ ደብዳቤ በመስጠት ውሉን ሊያቋጥ ይችላል፡፡
2) በመደበኛ የግንባታ ውሎች መሰረት የጊዜ ማራዘሚያ ጥያቄዎችን አግባብነት ያላቸውን መስፈርቶችን በማረጋገጥ እና ውል ሰጪው እንዲያውቀው በማድረግ መስጠት ይችላል፡፡ ይህንን ውሳኔ በባለቤት በኩል መከልከል የሚያስችለው የውል አግባብ የለም፡፡
3) በክፍያ ወቅት ከተሰራው የስራ መጠን በላይ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሊከፈል ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ወቅት ባለቤት እላፊ ተከፍሏ ያለውን መጠን ተቋራጭ ድርጅቱ በ45 ቀናት ውስጥ ተመላሽ እንዲያደርግ አጠቃላይ የውል ሁኔታዎች ይገልፃሉ፡፡ ይህ ሁኔታ ተፈፃሚ በማይሆንበት ባለቤት ወለዱን ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ ክፍያውን እንዲያገኝ የውል ሁኔታው ያስገድዳል፡፡
🚪✨ በተለያየ ዲዛይን የምንሰራቸው በሮች ውስጥ-:ሙሉ መስታወት ,ግማሽ መስታወት,ሙሉ ድፍንቦርድ,ግማሽ ድፍን ቦርድ የሆኑ የተለያየ ዲዛይን ያላቸውን በሮች ለውጪም ለ ዉስጥም መገጠም ሚችሉ ውሃ የማያበላሻቸው ፣ ድምፅ የሚከላከሉ እና ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ upvc በሮች ናቸው።
የቤትዎን እና የ ቢሮዎን በሮች ውበት እና ደህንነት በ ደሊና upvc በሮች ይጠብቁ።
📍 Location: ጋዜቦ አደባባይ፣ ሙልሙል ዳቦ ቤት አጠገብ
📞 Call us: 0930099146,0930099145
DELINA UPVC AND ALUMINUM
"A modern choice"
አዲሱ ህግ
በቅድሚያ ክፍያ ገንዘብ የሚገዙ ማሽነሪዎች፣
መመሪያ 1073/2025 አንቀጽ 138 ንዑስ አንቀጽ 7 ለአሸናፊው ተጫራች በሚፈቀድ የቅድመ ክፍያ ገንዘብ ለመንገድ ሥራና ለሕንጻ ግንባታ ሥራ የሚገዙ ማሽነሪዎች ዝርዝር፣
List of Machinery to Be Purchased with Advance Payment (Pursuant to Article 138(7) of the Directive).
▶️ ማስታወቂያ
▪️የስራ ተቋራጮች ምዝገባ መራዘሙን ስለማሳወቅ
https://t.me/ethioconradio
የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ
መመሪያ 648/2013 መሠረት ስራ ተቋራጮች ባላቸው ደረጃ እስከ ምን ያህል ፕሮጀክት ዋጋ መጫረት ይችላሉ?
ዝርዝሩን ይመልከቱ👆
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
ኳንቲቲ ስንሠራ የምንጠቀማቸው Units Of Measurement detail ማንበብ ከፈለጉ
ዳሎል የቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ
https://t.me/cotm2022
+3
አዲሱን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የሚገነቡ ቤቶች ከ60 እስከ 70 በመቶ የግንባታ ግብዓት ወጪን ይቀንሳል
ለሀገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን Cold-Formed Steel (CFS) የግንባታ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሚገነቡ ቤቶች ከ60 እስከ 70 በመቶ የግንባታ ግብዓት ወጪን እንደሚቀንስ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ቶማስ ደበሌ በመዲናዋ የሚከናወነውን የቤቶች ግንባታ አስመልክቶ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ አዲሱን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የሚገነቡ ቤቶች ከ60 እስከ 70 በመቶ የግንባታ ግብዓት ወጪን እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡
በመዲናዋ የቤት ልማት ኘሮግራም ረጅም እድሜ ቢኖረውም በመፍጠርና መፍጠን ባለመመራቱ ምክንያት ከተማ አስተዳደሩ ለበርካታ ዕዳ ተዳርጎ እንደነበር አይዘነጋም ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
ለዚህም ከተያዘው ዓመት ጀምሮ በመዲናዋ 1ዐዐ ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ ዘርፈ ብዙ አንቅስቃሴዎች እየተደረጉ እንደሚገኝ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የቤት ልማት ኘሮጀክት ቀደም ሲል የቤት ባለቤት ለመሆን ገንዘብ ሲቆጥቡ የነበሩ ዜጎችን ቅድሚያ ታሳቢ ለማድረግ ታቅዷል፡፡
1ዐዐ ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ሲታሰብ 5ዐ ሺውን በመንግስትና በግለሰቦች አጋርነት እንዲሁም 5ዐ ሺውን በመንግስት አቅም ለመገንባት አስፈላጊ የሚባሉ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡
የዲዛይንና የፋይናንስ ሥራዎችን በራስ አቅምና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ግንባታውን ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡
ለአገራችን የመጀመሪያ የሆነውን Cold- Formed Steel (CFS) የግንባታ ቴክኖሎጂን በመጠቀም 26 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ትላንት የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጣቸው ይታወሳል፡፡
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
