Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Открыть в Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Больше3 588
Подписчики
+224 часа
-17 дней
+4230 день
Архив постов
Brick quantity : bricks🚧( calculation for wall in cumbic meter
Wall length (L) = 10 meters
Wall height (H) = 5 meters
Wall thickness (T) = 0.2 meters
Volume of wall = L * H * T
= 10 x 5 x 0.2
= 10 m³
🚧( Let’s say mortar thickness 10 mm which is 0.1 m
➪ As you can see in this picture the dimension of single brick is 90 mm x 190 mm x 90mm
➪ volume of brick = 90 mm x 190 mm x 90 mm
( without mortar)
➪ volume of brick without mortal
= 0.09 x 0.09 x 0.19 = 0.001539 m³
➪ Volume of brick with brick [ +10mm each sides]
= 0.20 x 0.1 x 0.1 ( with mortar )
= 0.002m³
# of brick 🧱 in the wall = 10 / 0.002 = 5000 bricks
🚧 Let’s add 5% of wastage of bricks
☞︎ 5000 x 5/100 = 250 bricks 🧱
Total number of bricks including wastage
= 5000 + 250 = 5250 bricks 🧱
Prime Coatአዲሥ ቴክኖሌጂ ለ ኮንሥትራክሽን ባለሙያወች plastering(ልስን) ሚያሥቀር እና ቀጥታ፦ ☞ ብሎኬት, ☞ ኮለን(column), ☞ ሥላብ(slab) ላይ apply ሚሆን ሲሆን
prime coat ሚሠጣቸዉ ጥቅሞች፦ልስንን ወይም cement plastering ሙሉ ለሙሉ ሚያሥቀር ሥለሆነ በጣም ገንዘብ ቆጣቢ ነዉ። ጊዜ ቆጣቢ ነዉ ፤ ቶሎ ደርቆ ጥንካሬዉን ሥለሚያገኘ እና ቀጣዩን ሥራችን ቶሎ መጀመር ሥለሚያሥችል እንደ cement plastering (ልሥን) curing አይጠይቅም። ትልልቅ ፕሮጀክቶችም ሣይቀሩ ይህን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ላይ ናቸዉ.. .)
🏗 በአዲስ አበባ በሚያጋጥም የኮንስትራሽን የስራ ላይ አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል🚧 በዚህ ረገድ አደጋውን ለመቀነስና ለመከላከል የሀገራችን የኢትዮጵያ የህንጻ አዋጅ ምን ይላል! 🏢 በህንፃ ግንባታ ስራ ላይ እያጋጠሙ አደጋዎችና ለመከላከል ስጋቶችን ለመቀነስ እንዲሁም ከህንፃ ግንባታ ጋር የተያያዙ ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን የያዘ የህንፃ ህግ በሀገራችን ይገኛል፡፡ 🏗 የኢትዮጵያ የህንፃ አዋጅ ቁጥር 624/2001 ይህንን አዋጅ ለማስፈፀም በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው ደንብ ቁጥር 243/2003 ተጠቃሽ ናቸው፡፡ 🚧 በህንፃ ግንባታ የሚሳተፉ አካላት የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ጠብቀው ባለመስራታቸውና ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው በአዋጅ ቁጥር 624/2001 መሰረት ተጠያቂነት አለባቸው፡፡
በዚህ መሰረት:-ለሚያከናውነው ግንባታ የሚያስፈልግን የዲዛይን ስራ፣ ወይም የተሰራውን ዲዛይን መሰረት የሚከናወነውን ግንባታ የሙያ ደረጃው በማይፈቅድለት ባለሞያ ያሰራ እንደሆነ፣ ወይም ለሚያከናውነው ግንባታ ደረጃ ከሚጠይቀው የግንባታ ቁሳቁስ ያነሰ የጥራት ደረጃ ያላቸው ቁሳቁሶች በጥቅም ላይ እንዲውሉ ያደረገ እንደሆነ፣ ወይም ግንባታውን አግባብ ካለው አካል የመጠቀሚያ ፍቃድ ሳያገኝ ወይም ከተፈቀደው ውጪ ለሌላ አገልግሎት አውሎ የተገኘ እንደሆነ፣ ወይም በማንኛውም ሌሎች ሁኔታዎች ግንባታው የሕዝብን ደህንነት አደጋ ላይ በሚጥል ሁኔታ ያከናወነ እንደሆነ፣ ከአምስት ዓመት እስከ አስር ዓመት በሚደርስ እስራት እና ከብር ሃያ ሺህ እስከ ብር ሃምሳ ሺህ በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል። ማንኛውም የተመዘገበ ባለሞያ ወይም የስራ ተቋራጭ፣ በዋና ወይም በንዑስ ስራ ተቋራጭነት ወይም ከፊል ውለታ በመውሰድ ያከናወነው ህንፃ ዲዛይን ወይም የግንባታ ስራ ለሚያስከትለው ጉዳት በወንጀል ተጠያቂ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው አሰሪው ለሆነው ሰው አግባብነት ባላቸው የፍትሐብሄር ህግ ድንጋጌዎች መሰረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ የስራ ተቋራጩ ሆን ብሎም ይሁን በቸልተኝነት በሚገነባው ህንፃ በሰው ላይ ለሚደረሰው ወይም በህንጻው አካል ላይ ለሚደርሰው የስራ ጥራት ጉድለት ተጠያቂነቱ ሳይቀር ጉድለቱን የማስተካከል ግዴታ አለበት፡፡ ለእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎት በ939 ወይም በ011-1-55-53-00 ፈጥነዉ ያሳዉቁ! የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
ተቋራጭን ከሳይት ስለማባረር/Expel right/
በዚህ ጽሁፍ ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብት ለማን የተሰጠ ነው?በየትኛው ህግ?በምን ሁኔታ?በየትኛው የውል አይነት?በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት?የሚሉትን በአጭሩ ለመጠቆም እንሞክራለን፡፡
ይህ መብት ያለው የትኛው አካል ነው? የሚለውን በተመለከተ ተቋራጭን ከግንባታ ሳይት/ከግንባታ ስፍራ ለማባረር መብት ያለው አሰሪው ነው፡፡ስለዚህ መብቱ የግንባታው ባለቤት ወይም የአሰሪው ነው፡፡ስለዚህ ይህን መብት ተቋራጮች ሆኑ አሰሪ ያልሆነ ሌላ አካል ተግባራዊ ሊያደርገው አይችልም ማለት ነው፡፡
በየትኛው ህግ? ለሚለው ምላሹ በፍትሀብሄር ህጉ እና በጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት ነው፡፡በዝርዝር ሲታይ፡-
-በግንባታ ውሎች በተለይ ጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት መጠቀም የተለመደ ነው፡፡እነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች በራሳቸው ህግ አይደሉም፡፡እዚህ ላይ አንዳንድ የህግ ባለሙያዎች እንደ መመሪያ እና ህግ ስለሚቆጥሩት ይህ የግንዛቤ ክፍተት መታረም ይኖርበታል፡፡የግንባታ ውል ተዋዋዮች በስምምነታቸው እነዚህን ጀኔራል ኮንዲሽኖች የውሉ አካል ሲያደርጓቸው በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1731 መሰረት በተዋዋዮች መካከል እንደ ህግ ሆነው ይቆጠራሉ፡፡እዚህ ላይ ሌላው ጉዳይ ስፔሻል ኮንዲሽን ኦፍ ኮንትራክት ተብለው የሚቀመጡት ከጀኔራል ኮንዲሽኑ ድንጋጌዎች የተፈጻሚነት ቅድሚያ ይኖራቸዋል፡፡ለምሳሌ ከነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች ውስጥ የሲቪል ግንባታ ስራዎች ቋሚ የውል መተዳደሪያ/Standard condition of contract for the construction of civil work projects/ አንዱ ነው፡፡ይህ ጀኔራል ኮንዲሽን በከተማ ልማት ሚኒስቴር በኩል የተዘጋጀ ሲሆን ይዘቱ በዋናነት ከFIDIC 1987 version የተወሰደ ነው፡፡በአብዛኛው MoWUD 1994 ተብሎ ይጠራል፡፡ሆኖም ዋናው ነጥብ ተዋዋዮች ጥቅም ላይ ያዋሉትና የውላቸው አካል ያደረጉት የትኛውን ጀኔራል ኮንዲሽን እንደሆነ መለየትና ማወቅ የግድ ይላል፡፡
ከዚህ አንጻር MoWUD 1994 ክሎዝ 63 ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብትን አስመልክቶ በዝርዝር አስቀምጦታል፡፡በዚህ ድንጋጌ መሰረት በዋናነት አማካሪ መሀንዲሱ ለአሰሪው የተቋራጩን እንደውሉ ያለመፈጸም ሲያሳውቅ በተለይም ተቋራጩ ስራውን እንደተወው አማካሪው ሲያስታውቅ፣ተቋራጩ በአማካሪ መሀንዲሱ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ለ28ቀናት ስራውን ሳይጀምር ሲቀር፣በመሀንዲሱ ተቀባይነት የላቸውም የተባሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በ28 ቀናት ውስጥ ከሳይት ያላስወጣ እንደሆነ፣በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ስራውን በውሉ አግባብ ለመፈጸም ፈቃደኛ ያልሆነ እንደሆነ፣አማካሪ መሀንዲሱ እየከለከለው የስራውን ክፍል ለሌላ ተቋራጭ አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ ወይም ተቋራጩ የከሰረ እንደሆነ አሰሪው የ14 ቀን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት ማባረር የሚችል ይሆናል፡፡በዚህ ጊዜ ውሉ ይቋረጣል ማለት ነው፡፡/Termination of contract/
በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3288 አና ተከታዮቹ ላይ የተደነገገውም ተቋራጩ የውል ግዴታውን ባልፈጸመ ጊዜ የግንባታ ባለቤት ለሆነው ለአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ስራውን ከተቋራጩ ለመንጠቅ እና ውሉ ሳይቋረጥ ስራው በስራ መሪ ስር ሆኖ እንዲቆይ ለማድረግ መብት ይሰጠዋል፡፡እንዲሁም ውሉ ሊሰረዝ የሚችልበት ፈቃጅ የውል ቃል በግንባታ ውሉ ላይ ያለ እንደሆነ አሰሪው ቀሪውን ስራ ለሌላ ተቋራጭ በጨረታ ወይም በስምምነት በማሰራት እንዲጠናቀቅ ማድረግ ይችላል፡፡/የፍ/ህ/ቁ 3291(1) በዚህም ምክንያት አሰሪው ለተጨማሪ ወጭ/Additional cost/ የተዳረገ እንደሆነ ከተቋራጩ ላይ ለመጠየቅ እንደሚችል የፍ/ህ/ቁ 3291(2) በግልጽ መብት ይሰጠዋል፡፡ሆኖም በውል ህግ ላይ አሰሪው የተቋራጩን ግዴታ በሚያከብድ ሁኔታ ቀሪውን ስራ ማከናወን እንደሌለበት የሚያስገነዝበውን ግዴታውንም ማክበር አለበት፡፡
በየትኛው የውል አይነት? ለሚለው በዋናነት የአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ውሎችን በሚመለከት ሊተገበር የሚችል ነው፡፡ በግል የግንባታ ውሎች/private construction contract/ በተለይ ከፍ/ህ/ቁ 2610 እና ተከታዮቹ እንዲሁም ከፍ/ህ/ቁ 3019 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ውስጥ ተቋራጭን ስለማባበር አስመልክቶ ግልጽ ድንጋጌ አለመኖሩ ይህ መብት ለግለሰቦች ለመተግበር አስቸጋሪ የመሆኑን ሁኔታ ታሳቢ ተደርጐ በህግ አውጭው በማወቅ/ፐርፐዝሊ/ የተተወ ይመስላል፡፡ተዋዋዮች የግንባታ ውል ሲዋዋሉ ጀኔራል ኮንዲሽን ቢጠቀሙና በዚህም ስለተቋራጭ የማባረር መብት ድንጋጌ ቢኖረውስ የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል?ይሄን እንዴት ይተገብረዋል የሚለው ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ውሉ ግን ለተዋዋዮች ህግ ስለሚሆን በተቻለ መጠን ሊተገበር ይገባዋል የሚል እሳቤ አለኝ፡፡
*በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት? ለሚለው በዋናነት በ MoWUD 1994 ክሎዝ 63(2) ላይ እንደተቀመጠው በግንባታ ሳይት ላይ የተገኘ ቁሳቁስ በሙሉ በዝርዝር መመዝገብና ዋጋ ወጥቶለት መጠኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡በተቋራጩ የተሰራው ስራ መጠን/level of work done/ በትክክል መታወቅና በዝርዝር መመዝገብ አለበት፡፡ተቋራጩ ያለበት እዳ/ከወሰደው የቅድሚያ ክፍያ ውስጥ ያልመለሰው ማለት ነው/ መታወቅ አለበት፡፡ለተቋራጩ የተከፈለው የስራ ክፍያ ሊታወቅ ይገባል፡፡እነዚህን የሂሳብ ሁኔታዎች አመዛዝኖ እና ዋጋ አስቀምጦ ተቋራጩ የሚከፈለው ገንዘብ ካለ እንዲከፈለው ለአሰሪው የሚመልሰው ገንዘብ ካለም እንዲመልስ ሂሳብ የማስተሳሰብና ሪፖርት የማቅረብ ሀላፊነቱ የአማካሪ መሀንዲሱ ነው፡፡በዚህ ረገድ አማካሪ መሀንዲሶች ብዙ ጊዜ እንደዚህ አይነት ሪፖርት ስለማያቀርቡ የግንባታ ክርክሮች ያልተሸከፉ ይሆኑና ለፍርድ ቤቶች ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ አስቸገሪ ሁኔታ ይፈጥራሉ፡፡
*አሰሪው ይህን መብቱን ለመጠቀም ሀይል መጠቀም የሚችልበት ግልጽ ፈቃጅ ህግ ግን የለም፡፡
በመጨረሻምአሰሪና ተቋራጮች ለግንባታ ጥራት በመስራትና ለትክክለኛ እና እውነተኛ ነገር በመተባበር የኮንስትራክሽኑ ዘርፍ እድገት እንዲያሳይ ማገዝና አለመግባባቶችን በስምምነት መፍታት ቢችሉ ጠቀሜታው ለሀገርም ለራሳቸውም ነው፡፡በአሰሪና ተቋራጭ ክርክር ብዙ ትምህርት ቤት እና የጤና ተቋም እንዲሁም ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታቸው ተቋርጦ ማህበረሰቡን ከተጠቃሚነት የሚያዘገይበት ሁኔታ ወደፊት ተቀርፎና ተቃልሎ ማየት የዘወትር ምኞታችን ነው፡፡
INVITATION FOR RE-BID
IFB No. ECWCT/NCB/PG/0095/2016
1. The Ethiopian Construction Works Corporation (ECWC) hereby invites registered eligible bidders for Procurement of Sanitary Material.
2. Interested Potential Bidders are required to present renewed relevant Trade License for the Ethiopian fiscal year, VAT Registration Certificate, Tax Clearance Certificate and Online Supplier list Registration Certificate together with their offer.
3. Bidding document should be prepared in English language.
4. Interested Potential Bidders obtain a complete set of bidding document from the office of Procurement Department against payment of none refundable fee of Birr 400.00 upon presentation of Trade License renewed for the fiscal year.
5. This invitation of bid is open to all interested potential bidders regardless of their nationality and the bid evaluation and award shall be determined in accordance with the provision indicated in bidding document.
6. The deadline for bid Submission shall be on MARCH 28, 2024, at 4:00 Local time
7. Bid must be accompanied with a Bid Security of an amount of Birr 200,000.00 ETB (Two hundred thousand) in the form of certified cheque (CPO) or Bank guarantee. Bid Bond in the form of insurance bond or in any other form shall not be accepted.
8. Bids must be delivered or deposited in the Tender Box situated at the office of the Procurement Department on MARCH 28, 2024, at 4:30 Local time in Ethiopian Construction Works Corporation Procurement Department conference room, in the presence of bidders and/or their representatives who choose to attend.
9. The Ethiopian Construction Works Corporation reserves its rights to reject any or all bids.
10. Bidders may get further information at the following address:
Ethiopian Construction Works Corporation
Address: - Gurd shola behind Athletics Federation Building
In front of Andinet International school
Telephone No.011 8 72 29 58/ 0118 72 30 86/011 896 29 91
የሥራ ተቋራጭ (Contractor) የሕግ ተጠያቂነት??
በኮንስትራክሽን ውል ሁለት አይነት የግንባታ ስራ ርክክቦች ያሉ ሲሆን እነሱም ግዚያዊ ርክክብ እና የመጨረሻ ርክክብ በመባል ይታወቃሉ፡፡
1/ ግዚያዊ ርክክብ
ግዜአዊ ርክክብ በተለይ በኮንስትራክሽን ውል የተመለከቱ የግንባታ ስራዎች ተከናውነው ካበቁ በኋላ ወዲያውኑ ሁለቱ ወገኖች ማለትም አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በስራው ላይ የሚደረግ የምርመራ ማረጋገጫ ነው:: (የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3274(1)):: ይሄውም አሰሪው በትክክል የተገነባውን ግንባታ በእጁ አግብቶ መያዙን ጭምር ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ጊዜአዊ ርክክብ በዋናነት የተሰራውን የግንባታ ስራ አሰሪው መብቱን ጠብቆ በመጀመሪያ የሚረከብበት ሂደት ነው፡፡ በስራው ላይ ምርመራ መደረጉንም የሚያረጋግጥ ነው፡፡
እንግዲህ ስራው ከተመረመረ በኋላ አሰሪው ያላመነበትን ግንባታ ፈርሶ እንደገና እንዲሰራ ወይም እንዲጠገን ተደርጐ የጥራት ደረጃውን ባሟላ ሁኔታ እንዲከናወን ለማዘዝ እንደሚችል ፒፒኤ ክሎስ 85 ይፈቅድለታል:: በዚህም መሰረት ግንባታው የስራ ምርመራውን ካለፈ አሰሪው ግንባታውን የሚረከበው ይሆናል፡፡
2/ የመጨረሻ ርክክብ
የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/ በተለይ የመድህንነት ጊዜ ካለቀ በኋላ እና ተቋራጩ ጠቅላላ ግዴታዎቹን በደህና ሁኔታ የፈጸመ መሆኑን አሰሪው ሲያረጋግጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ በእጁ የሚያደርግበት ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279 ይደነግጋል፡፡
የመጨረሻ ርክክብ አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት በአስገዳጅ ሁኔታ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279(2) ላይ ተደንግጓል፡፡
በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3282 ላይ እንደተቀመጠው ከመጨረሻ ርክክብ በኋላ ተቋራጩ እስከ 10 አመት ድረስ ስለስራው አሰራር ጉድለት ተቋራጩ ሀላፊነት አለበት ፣ ለስራው ጥራት መድህን ሆኖም ይቀጥላል፡፡ ስለሆነም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተደረመሰውን ድልድይ የገነባው ሥራ ተቋራጭ ለደረሰው ጉዳት በሕግ ተጠያቂ የሚሆንበት አግባብ ሊኖር ይችላል:: ይሁን እንጂ በመጨረሻ ርክክብ ወቅት የሚታዩ ለነበሩ የጥራት ጉድለቶች ተቋራጩ ሀላፊነት የለበትም፡፡
INVITATION FOR RE-BID
IFB No. ECWCT/NCB/PG/0095/2016
1. The Ethiopian Construction Works Corporation (ECWC) hereby invites registered eligible bidders for Procurement of Sanitary Material.
2. Interested Potential Bidders are required to present renewed relevant Trade License for the Ethiopian fiscal year, VAT Registration Certificate, Tax Clearance Certificate and Online Supplier list Registration Certificate together with their offer.
3. Bidding document should be prepared in English language.
4. Interested Potential Bidders obtain a complete set of bidding document from the office of Procurement Department against payment of none refundable fee of Birr 400.00 upon presentation of Trade License renewed for the fiscal year.
5. This invitation of bid is open to all interested potential bidders regardless of their nationality and the bid evaluation and award shall be determined in accordance with the provision indicated in bidding document.
6. The deadline for bid Submission shall be on MARCH 28, 2024, at 4:00 Local time
7. Bid must be accompanied with a Bid Security of an amount of Birr 200,000.00 ETB (Two hundred thousand) in the form of certified cheque (CPO) or Bank guarantee. Bid Bond in the form of insurance bond or in any other form shall not be accepted.
8. Bids must be delivered or deposited in the Tender Box situated at the office of the Procurement Department on MARCH 28, 2024, at 4:30 Local time in Ethiopian Construction Works Corporation Procurement Department conference room, in the presence of bidders and/or their representatives who choose to attend.
9. The Ethiopian Construction Works Corporation reserves its rights to reject any or all bids.
10. Bidders may get further information at the following address:
Ethiopian Construction Works Corporation
Address: - Gurd shola behind Athletics Federation Building
In front of Andinet International school
Telephone No.011 8 72 29 58/ 0118 72 30 86/011 896 29 91
አዲስ ዘመን 🚧
መጋቢት 02/2016 ዕትም
የግንባታ ስራ ተቆራጮች | ጨረታ
@unitysupplydb1 <<´ገፃችን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
----------- ጨረታ | bid -----------
ዩ ኒ ቲ´ ኮንስትራክሽን ኦፊሻሎች
አዲስ ዘመን 🚧
መጋቢት 02/2016 ዕትም
የግንባታ ስራ ተቆራጮች | ጨረታ
@unitysupplydb1 <<´ገፃችን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
----------- ጨረታ | bid -----------
ዩ ኒ ቲ´ ኮንስትራክሽን ኦፊሻሎች
አዲስ ዘመን 🚧
መጋቢት 02/2016 ዕትም
የግንባታ ስራ ተቆራጮች | ጨረታ
@unitysupplydb1 <<´ገፃችን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
----------- ጨረታ | bid -----------
ዩ ኒ ቲ´ ኮንስትራክሽን ኦፊሻሎች
አዲስ ዘመን 🚧
መጋቢት 02/2016 ዕትም
የግንባታ ስራ ተቆራጮች | ጨረታ
@unitysupplydb1 <<´ገፃችን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
----------- ጨረታ | bid -----------
ዩ ኒ ቲ´ ኮንስትራክሽን ኦፊሻሎች
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
