ru
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Открыть в Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Больше
3 586
Подписчики
+224 часа
-17 дней
+4230 день
Архив постов
ለመሬት ረገጥ ሀብት ግዢ አንዳንድ ጥንቃቄዎች (Precautions in Real Estate Purchase) መሬት ረገጥ ሀብትን (Real Estate) ስንገዛ ማሰብና መከወን ያሉብን ቴክኒካዊ ጉዳዮች በ22 ዝርዝሮች ተቀምጠዋል።  በብዙ ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ስናደርግ እንደዚህ በጥልቀት ማየት የሚኖርብን ሲሆን፣ እነዚህ ዝርዝሮች ከአሻሻጮቹም ሆነ ከነጋዴዎቹ እውቀት በላይ በመሆናቸው ልፋት አከል ሥራዎች ሊሆኑ ይችላሉ። በተጨማሪም አብዛኞቹ መሬት ረገጥ ሀብቶች የሚሸጡት በአካል በአገር ውስጥ ለሌሉ ደንበኞች ሲሆን፣ ባለሀብቶቹ ከማከራየት ባለፈ እንደ ኢንቨስትመንት ስለሚያዩዋቸው እንደተዘረዘሩት የሚጨነቅ ገዢም ሆነ ገንቢ እንዲሁም ተከራይ አይገጥሙንም። (ያከራየኝ ሰው ቤቱንም አይቶት አያቅም ሲባል አልሰማችሁም) በቅርቡ ግን ሁላችንም በሰማይ ላይ ተንጠልጥለን መኖራችን ስለማይቀር ሁሉም ቴክኒካዊ ዝርዝሮች ሁላችንንም አንድ በአንድ እንደሚያገቡን እሙን ነው። ስለዚህ እነዚህን ጥያቄዎች ለማወቅ አልሚዎችን ስንጠይቅ እንደደፋር ተቆጥረን  "ትገዛ እንደሆነ ግዛ አንተ ምን ስለሆንክ ነው የምትጠይቀው?" አይነት መልስ ልናገኝ እንደምንችል ይገመታል። ወደ ዝርዝሩ፦ 1. የአልሚ እና የገዢ ውሉን ህግ፣ ለህግ አዋቂ ከፍሎ ማስመርመር፤ 2. የአልሚውን የበፊት የማልማት ዝናን መፈተሽ፤ 3. ከተቻለ የተገነባን  ሀብት መግዛት፤ 4. የተገነባም ሆነ ሊገነባ ያለ ከሆነ የቤቱን ፕላን በህንጻ ነዳፊ ማስመርመር፤ ( የእሳት ማጥፍያ የውሀ ስርአት ፣ የእሳት አደጋ ግዜ ማንቅያ፣ በእሳት አደጋ ጊዜ የአደጋ ማምለጫ ደረጃ እሳትና ጭስ የመቋቋም ስርዓት፣ የምግብ ማብሰያ እና መታጠብያ ቤት ሽታ ማስወገጃ፣ በቂ ተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረግያ ወዘተርፈ መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።) 5. የህንጻ አስተዳደር (facility management) ተገማች ወርሀዊ ወጪ ስንት እንደሆነ መጠየቅ፤ 6. የመነሻ አፈር ምርመራን፣ የግንባታ ወቅት ተከታታይ የብረት እና አርማታ ምርመራ ምስክር ወረቀትን ጠይቆ ማየት፤ 7. የኤሌክትሪክ ገመዶችና ስርዓቶችን በባለሙያ ማስመርመር፣ ተጠባባቂ ኃይል አመንጪ መኖሩን እና አቅሙን መጠየቅ፤ ቁመተ ረጅም ህንጻ ከሆነ ስለመብረቅ መከላከያ ስርአት መጠየቅ፤ 8. የፍሳሽ መስመር ላይ በተጓዳኝ የሚዘረጋ የማስተንፈሻ ቱቦ እና ስርዓት መኖሩን ማረጋገጥ (የፍሳሽ ሽታ ማስወገጃ ዘዴ) 9. ህንጻው የከተማ የፍሳሽ መስመር አጠገቡ መኖሩን ማጣራት (አለበለዝያ በየወቅቱ የፍሳሽ ማስመጠጫ ተሽከርካሪ አዋኪነትን መቀበል) 10. በቂ የውሀ ማከማቻ እና አቅርቦት ስርአት እንዳለው በባለሙያ ማጣራት። 11. የፍሳሽ ማስወገጃ የቁመት ትቦዎች የሚያልፉበት ድምጽ በማያሳልፍ  በተከለለ ቀዳዳ እንደሚያልፍ ማረጋገጥ፤ (እነዚህ ቱቦዎች በድምጽ ስለሚረብሹ በየመታጠብያ ክፍሉ ተጋልጠው መገኘት የለባቸውም) 12. ለተሽከርካሪ መንገድ ቀረቤታ ካለው የድምጽ መከላከያ እርምጃዎች ምን እንደሆኑ ማጣራት፤ 13. ለሳተላይት ርቀት ማያ (TV) ወይም ለበይነመረብ ፕሮቶኮል ርቀት ማያ (IPTV) የተዘጋጀ መስመር እንዳለው ማረጋገጥ (አለበለዝያ ሁሉም ሰው የሳተላይት ሰሃኑን ሰገነት ላይ ሰቅሎ የህንጻው መልክ እንደሚበላሽ መቀበል) 14. የተጣራ እና ያልተጣራ የሚሸጥ የቤት ስፋትን ማጣራት፣ (መተላለፍያ፣ ደረጃ፣ ተሽከርካሪ ማቆምያ ወዘተርፈ.... በነዚህ ስፋቶች መካተት አለመካተታቸውን ማጣራት) 15. የከፍታ ተሽከርካሪን (lift) የሰው የመጫን አቅምን፣  ብዛትን  እና ፍጥነትን ማጣራት። 16. የጥያራ  ማረፍያ (airport) በአካባቢው ካለ ጥያራው የሚያስነሳውን አዋኪ ድምጽ ዴሲቤል በተንቀሰቃሽ ስልክ መለካት፤ 17. አካባቢው ከቤተ እምነቶች በድምጽ ማጉልያ የሚወጡ ድምጾች እንዳሉ ማረጋገጥ፤ 18. የሚገዛው ቤት ዋና ዋና ክፍሎች አቅጣጫን ማወቅ (ለምሳሌ ወደ ሰሜን የሚከፈት ክፍል በፍጹም ፀሐይ የማያገኝ ከመሆኑ የተነሳ በአርማታ በተሰራ ህንጻ ውስጥ፣ በአዲስአበባ ከተማ አውድ እጅግ ቀዝቃዛና የሚደብት መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል) 19. የሚቻል ከሆነ አልሚው የመስኮቶች ክፍተት ላይ ትንኝ-ከላ ወንፊትን ከመስታወቶች አዳብሎ እንዲሰራ ማመላከት፤ 20. አካባቢው በቋሚነት ከሚከሰት መጥፎ ሽታ ነፃ እንደሆነ ማረጋገጥ፤ 21. ልማቱ ላይ እጅግ የበዛ አባወራ እንዲኖርበት የተነደፈ ከሆነ ወደልማቱ የሚወስዱ ተመጣጣኝ ስፋት ያላቸው መጋቢ መንገዶች እንዳሉ ማረጋገጥ፤ 22. በመጨረሻም ባለብዙ ወለል ባለብዙ መኖርያ  የጋራ መኖርያ ቤት የሚሰራ ከሆነ እና እንደ ባህላችን በቀስታ ተቁላልተው የሚሰሩ ምግቦች የሚበስሉባቸው ማብሰያ ክፍሎች የሚኖሩ ከሆነ ማብሰያ ክፍሎች ውስጥ ያለውን የሽታ ማስወገጃ ስርአት በጥልቅ መመርመር ያስፈልጋል። አንደኛ ካንዱ ቤት ወደ አንዱ ቡና እና ወጥ ሽታ እንዳንቀባበል፣ ሁለተኛው ደግሞ ሽታዎች  ከምግብ ማብሰያ ወደ መኝታ እና እንግዳ መቀበያ እንዳይገቡ ሲባል ነው። (ዳዊት በንቲ፣ መምህር እና ሕንፃ ነዳፊ)

የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበት አዋጅ ፀደቀ።
ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 34ኛ መደበኛ ስብሰባው ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣ /ማሻሻያ/ ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል። ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በምክር ቤቱ የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ገዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡  በተሻሻለው አዋጅ በፌዴራል ደረጃ በሚሰሩ ፕሮጀክቶች የካሳ ትመና ክፍያ እንዲሁም ተነሺዎችን መልሶ ለማቋቋም ስልጣንና ኃላፊነት ያለባቸውን አካላት በግልፅ ለይቶ ለመወሰን የሚያስችል ስርአት ስለመዘርጋቱ ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል። ፕሮጀክቶች በጥራት እና ጊዜ ቆጣቢ በሆነ መልኩ እንዲከናወኑና ለሀገራዊ ልማት ያላቸውን አስተዋጽዖ ከፍ የሚያደርግ ድንጋጌ በአዋጁ ስለመካታቱም አስረድተዋል። ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች በተመሳሳይ ወጪና ተቀራራቢ ጊዜ እንዲጠናቀቁ የሚያስችል አሰራር ያስቀመጠ አዋጅ እንደሆነም ተናግረዋል። ተገቢ ባልሆነ የካሳ ይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱት የፍርድ ቤት ክርክርና የባንክ አካውንት እገዳ በፕሮጀክቶች ላይ ይደርስ የነበረውን የስራ መጓተት የሚቀንስ አዋጅ እንደሆነም በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተገልጿል። በምክር ቤቱ የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እጸገነት መንግስቱ በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የካሳ ክፍያ ስርዓት ለብልሹ አሰራሮች የተጋለጠ መሆኑንና የልማት ተነሺዎች ተገቢውን ካሳ እንደማያገኙ ጠቁመው፤ የተሻሻለው አዋጅ የመንግስት እና የህዝብ ሀብት እንዳይባክን ያስችላል ብለዋል፡፡ አዲሱ አዋጅ በፍትህ ስርዓቱ ላይ የሚያመጣው ችግር እንደሌለና ተገቢ ካሳ ያላገኘ አካል እስከ ላይኛው የፍትህ ተቋም በመሄድ መብቱን ማስከበር እንደሚችልም የተከበሩ ወ/ሮ እጸገነት አስረድተዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን፤ የተሻሻለው አዋጅ ቀደም ሲል የነበረውን ብልሹ አሰራር በመቅረፍ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀትና ጊዜ እንዲጠናቀቁ ያግዛል ብለዋል፡፡ ከካሳ ክፍያ ጋር ተያይዞ የሚነሱ አለመግባባቶች ወደ ፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሚመጡ እዚያው ባሉበት ፍርድ ቤቶች ቢታዩ የሚሉ አስተያየቶችም ተነስተዋል፡፡ በሌላ በኩል አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች የካሳ ክፍያ ለማከናወን አቅም ላይኖራቸው እንደሚችል ለቀረበው ጥያቄ፤ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ሲታቀዱ ለክልሎች የሚመደበው በጀት ላይ የካሳ ክፍያን ታሳቢ በማድረግ እንደሆነ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ በተሻሻለው አዋጅ የተፈጻሚነት ወሰን አዋጁ ከጸደቀ በኋላ ለሚሰሩት የካሳ ግመታዎችና ክፍያዎች ሲሆን፤ ቀደም ሲል የካሳ ግመታ ተሰርቶ ያልተከፈላቸው የልማት ተነሺዎች ግን በነባሩ አዋጅ እንደሚስተናገዱ ተገልጿል፡፡ በመጨረሻም ረቂቅ አዋጁ በ 4 ተቃውሞ እና በ 6 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ሆኖ ጸድቋል፡፡ ምንጭ~ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8

የራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል B+G+5 ሕንፃ የስትራክቸር ስራ 88 በመቶ ደርሷል፡፡ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አዳዲሶቹንና ግዙፎቹን የኮልፌና የንፋስ ስልክ ላፍቶ ሆስፒታ
+7
የራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል B+G+5 ሕንፃ የስትራክቸር ስራ 88 በመቶ ደርሷል፡፡ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አዳዲሶቹንና ግዙፎቹን የኮልፌና የንፋስ ስልክ ላፍቶ ሆስፒታሎችን እንዲሁም  የጥሩነሽ ቤጂንግ ማስፋፊያ ግንባታን ጨምሮ በጤናው ዘርፍ በርካታ ፕሮጀክቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ግንባታዎች ውስጥ አንዱ የሆነውና ቢሮው በበጀት ዓመቱ ከጀመራቸው ፕሮጀክቶች ውስጥ የሚጠቀሰው የራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል B+G+5 ሕንፃ በጥሩ በጥሩ አፈፃፀም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በመዲናችን ከሚገኙ ቀደምት ሆስፒታሎች ውስጥ አንዱ የሆነውን የዚህን ሆስፒታል አገልግሎት ወደላቀ ደረጃ እንደሚያሻግር ተስፋ የተጣለበትና በተለይም የድንገተኛ አደጋዎች ሕክምናን በልዩነት እንዲሰጥ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ሕንፃ አሁን ላይ ከ58 በመቶ በላይ የፊዚካል አፈፃፀም ላይ ደርሷል፡፡ ቢ.ጂ.ኤም. ኮንስትራክሽን በስራ ተቋራጭነት እንዲሁም የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ እና ማማከር ድርጅት በአማካሪነት እየተሳተፉበት የሚገኘውንና  ከ798 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ይህን ፕሮጀክት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማዋል አሁን ላይ የ5ተኛ ወለል የብረት፣ የፎርም ዎርክ እና አርማታ ሙሌት ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ሲሆን  በተጨማሪም እስከ 3ተኛ ወለል የብሎኬት እና የልስን ሥራዎች ፣የህንፃ ዙሪያ ፍሳሽ ማስወገጃ ፣የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ፣የስርገት መከላከያ እና ሌሎች ተያያዥ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ

Share የመኖሪያ_ቤት_ኪራይ_ቁጥጥር_እና_አስተዳደር_መመሪያ_ቁጥር_7_2016.pdf

Share ምንጩ_ያልታወቀ_ሃብት_ማስመለስ_አዋጅ.pdf

ክፍት የስራ ማስታወቂያ
የስራው መጠሪያ: office engineer የስራው አይነት: በተመደቡበት የሚሰራ - ቋሚ የስራው ዘርፍ: #ሲቪል_ምህንድስና_እና_ኮንስትራክሽን የስራው ቦታ: አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ የትምህርት ደረጃ: የመጀመሪያ ዲግሪ የልምድ ደረጃ: ከፍተኛ የተፈላጊ ሰው ብዛት: 2 ደሞዝ/ክፍያ: ወርሃዊ የማመልከቻ ማብቂያ ቀን: June 30th, 2024 የስራው ዝርዝር: Job Overview: We are seeking two highly organized and detail-oriented Office Engineers to join our growing team. The Office Engineers will be responsible for supporting project planning, design, and construction administration tasks to ensure successful project execution. Key Responsibilities: •  Assist in the preparation and review of project plans, drawings, and specifications. •  Coordinate with project managers and site engineers to ensure project requirements are met. •  Prepare and maintain project documentation, including reports, schedules, and contracts. •  Review and process submittals, RFIs, and change orders. •  Assist in project budgeting and cost control, ensuring alignment with project goals. •  Conduct site visits to monitor project progress and ensure compliance with design specifications. •  Assist in resolving technical issues and provide support to the construction team. •  Communicate effectively with clients, consultants, and subcontractors. •  Ensure all project activities adhere to safety regulations and quality standards. •  Maintain up-to-date knowledge of industry best practices and standards. Qualifications: •  Bachelor’s degree in civil engineering, construction management, or a related field. •  Minimum of 2 years of experience in a similar role within the construction industry. •  Proficiency in using engineering software and tools (e.g., AutoCAD, MS Project). •  Strong organizational and time management skills. •  Excellent written and verbal communication abilities in English. •  Ability to handle multiple tasks and prioritize effectively. •  Strong analytical and problem-solving skills. •  Knowledge of construction methods, materials, and regulations. •  Ability to work both independently and as part of a team. •  Attention to detail and accuracy in all tasks. Benefits: •  Competitive salary based on experience. •  Opportunities for professional development and career growth. •  A supportive and dynamic work environment. • Involvement in prestigious and impactful projects.   *Applicants should be proficient in English and Affan Oromo language in writing, speaking, listening and reading.   
*Apply using @papikia19 telegram account
BROTHERS TRADING PLC

በድጋሚ የወጣ የአጥር ስራ ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ማስታወቂያ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ክልል ውስጥ የአስኮ 40/60 የጋራ ህንፃ ባለቤቶች ኃ/የተ/ህብረት ስራ ማህበር ለአጥር ግንባታው አስፈላጊ የሆኑትን ግብዓቶች በማቅረብ የጉልበት ዋጋን በጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ የኮንዶሚኒየሙን ዙሪያ አጥር ለማሳጠር ይፈልጋል። በዚሁ መሰረት በጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-     የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የዘመኑን ግብር የከፈለ፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆነ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No) ማስረጃ የሚያቀርብ መሆን ይኖርበታል።     2ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉት በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው ሆነው ደረጃ ስምንት እና ከዛ በላይ መሆን አለባቸው።     ተጫራቾች ለጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ማስከበሪያ ዋስትና /CPO/ ብር 10,000.00 ማስያዝ ይኖርባቸዋል።     ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጉልበት ዋጋ ለስራው የሚያስፈልጉትን ማሽነሪዎችና መሳሪያዎች ያካተተ መሆን ይኖርበታል።     ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ማስታወቂያ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አስኮ 40/60 ሳይት ብሎክ 3 አንደኛ ፎቅ ካለው የማሀበሩ ፅ/ቤት የማይመለስ ብር 400.00 በማህበሩ የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000366344547 ገቢ በማድረግ የባንክ ደረሰኙን ይዞ በመቅረብ መግዛት ይችላል።     ተጫራቾች የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን ሰነድ በመሙላት የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ መመሪያ በሚያዘው የፋይናንሻልና ቴክኒካል ፕሮፖዛላችሁን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ው ከወጣበት ግዜ አንስቶ በ15 ቀን ጊዜ ውስጥ በማህበሩ ፅ/ቤት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።     ተጫራቾች የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ሰነዱ ላይ ህጋዊ ማህተም እና ፊርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ህጋዊ ማሀተም የሌለው ሰነድ ከውድድር ውጭ ይደረጋል።     ተጫራቾች የቦታውን ጠቅላላ ሁኔታ በሳይቱ ላይ በአካል በስራ ሰዓት‍‍‍‌‌‍‍‍‌‌‌‍‌‌‍ በመገኘት መመልከት ይችላሉ።     ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ው በተዘጋ በነጋታው ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ይከፈታል።     ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ማብራሪያ፡- በስልከ ቁጥር-0974-99 93 94/0911_83-38-28 ወይም የማህበሩ ጽ/ቤት ቢሮ በአካል በመቅረብ መጠየቅ ይቻላል። የአስኮ 40/60 የጋራ ህንፃ ባለቤቶች ኃ/የተ/ህብረት ስራ ማህበር

የሰኔ_17_ቀን_2016_ዓ_ም_የተዘለለ_የሀራጅ_ሽያጭ_ማስታወቂያ.PDF0.91 KB

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗 - Статистика и аналитика Telegram-канала @consite