Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Открыть в Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Больше3 587
Подписчики
Нет данных24 часа
-47 дней
+4730 день
Архив постов
TOR For maintenance Service Provider 63-2017.docx0.31 KB
Share የግንባታ ፈቃድ ማመልከቻዎች.pdf
A.A Color Code Manual for Pilot test31.pdf8.72 KB
👉በኮሪደር ልማት የተሳተፉ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች መንግስት ክፍያ ሊፈፅምላቸው እንዳልቻለ ተናገሩ
በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ካዛንችስ ካሉ ቦታዎች ለተነሱ ሰዎች በፍጥነት የተዘጋጁ የጋራ መኖርያ ቤቶችን ያዘጋጁ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች ክፍያቸውን መንግስት እንደያዘባቸው ገልፀው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳሉ ተናገሩ።
ኮንትራክተሮቹ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት መረጃ መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ኮንትራክተሮቹ በግዴታ ከ3 ሺህ በላይ ቤቶችን ለኮሪደር ተነሺዎች እንዲገነቡ ካደረገ በኋላ ክፍያ መፈፀም አልቻለም።
"በጥቃቅን እና አነስተኛ የተደራጀን እኛ ኮንትራክተሮች ከ3 ሺህ በላይ የ40/60 የጋራ መኖርያዎች ውስጥ ያሉ ለንግድ ተብለው የተሰሩ ክፍሎችን ወደ መኖርያነት ቀይረን ገንብተን ብንጨርስም መንግስት ክፍያችንን ከልክሎናል" የሚሉት ኮንትራክተሮቹ አብዛኞቹ በብድር ወስደው ስራውን ቢሰሩም አሁን ትርፉ ቀርቶ ብድራቸውን ለመክፈል ተቸግረው እንዳሉ አብራርተዋል፣ አንዳንዶቹ ብድሩን ለመክፈል የግል ንብረታቸውን ለመሸጥ እየተገደዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
እነዚህ ለተነሺዎች በኮንትራክተሮቹ የተዘጋጁ ቤቶች በአያት፣ አራብሳ፣ ቡልቡላ እና አስኮ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
"ቤቶች ልማት እና ፋይናንስ ቢሮዎችን ስንጠይቃቸው ምላሻቸው ገንዘብ የለንም ነው፣ ታድያ ገንዘብ ከሌላቸው ለምን እኛን አሰሩን?" የሚል ጥያቄ የሚያነሱት እነዚህ አነስተኛ እና ጥቃቅን ኮንትራክተሮች አንዳንዶቹ ቤተሰባቸው ጭምር ችግር ላይ እንደወደቀ ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኮንትራክተሮቹ ጋር መረጃ ይለዋወጥበት የነበረ የቴሌግራም ግሩፕን ስራው ካለቀ በኋላ ሰው መረጃ እንዳይቀያየርበት መቆለፉን ለማየት ችለናል።
የቤቶች ልማት ኮንትራክተሮቹን ወደ ስራ ሲያስገባ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዳይጠይቁ አስፈርሞ እንደነበር መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ ሰነድ ያሳያል።
"ወደን ሳይሆን በግዴታ ነው ካለ ቅድመ ክፍያ ተስማምተን የገባነው፣ እንደዛ ካልተስማማን ወደፊት ምንም ስራ ከተማ ውስጥ መስራት አትችሉም ተብለን ማስፈራርያ ተሰጥቶን ነበር" ያሉት ግለሰቦቹ አሁን ላይ ለሁሉም ስራ ሳይከፈል የተከማቸው ገንዘብ 4.4 ቢልዮን ብር ገደማ እንደሆነ ጠቁመዋል።
መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ባደረገው ተጨማሪ ከ3 ሚልዮን ብር እስከ 42 ሚልዮን ብር የተያዘባቸው ኮንትራክተሮች እንዳሉ የተረዳ ሲሆን ከነዚህ ኮንትራክተሮች ውጪም በኮሪደር ልማት ዙርያ የመንገድ ግንባታ የተሳተፉ አቅማቸው ከፍ ያለ ኮንትራክተሮችም ክፍያ ተነፍጓቸው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችላል።
Via Meseret Media
🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱Our Bricks:- Tough,Don't decay, warp or twist, resistance to water & harsh soils, don't fade....🧱ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ ጡቦችን እናመርታለን።
🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣
🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣
🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣
🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣
🧱 ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣
🧱 ለx-ray ክፍሎች፣
🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣
🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣
🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣
🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣
🧱 ለአበባ መትከያ
🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣
🧱 ለፒዛ ኦቭን፣
🧱 ለምድጃ፣
🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ፣
NEW POINT BRICK FACTORY
*We produced best quality clay bricks for various construction purposes.
🧱 For building construction,
🧱 For bank vaults,
🧱 Fence for the yard,
🧱 For road edges,
🧱 For Hotels,Restaurants,and Cafes decoration,
🧱 For x-ray rooms,
🧱 For manuals,
🧱 For kitchen,
🧱 For shower tray
🧱 To cover PBC drains,
🧱 For garden,
🧱 Furnace For steel factory,
🧱 For pizza oven,
🧱 For waste incinerator, ....."Build together the future" join our telegram channel For order 0912854327&0902378888
የዋጋ ጭማሬ (Price Increament) ስሌትበተለይ በዚህ ዘመን የግንባታ ግብአቶች ዋጋ ከዕለት-ዕለት ተቀያያሪና ተገማች ያልሆነ ሆኗል። በኮንስትራክሽን ሥራዎች ደግሞ እንደ ውላቸው የጊዜ ገደብ (Period to adjust price as per the contract) የዋጋ ማስተካከያ ጥያቄ የሚበዛበት ዘመን ሆኖ ተስተውሏል። በመሆኑም የዋጋ ማስተካከያ (price adjustment) ለማድረግ የራሱ የሆነ ስሌት ያለው ሲሆን ምን ያህል እንደጨመረ (እንደቀነሰ) ለማስላት የሚከከተለውን መንገድ እንጠቀማለን። ~ የግንባታ ግበቶች ዋጋ ጭማሬ (ቅናሽ) መጠን ~ የሠራተኛ ዋጋ (ባለሙያ፣ የጉልበት አበል) ~ የደመወዝተኛ ክፍያ (መሐንዲስ፣ አስተዳደር) ~ ሥራ ተጀምሮ የታየ አስቸጋሪ ሁኔታ ~ የማሽነሪና መሳሪያዎች ኪራይ ዋጋ ~ ሀገሪቱ ያወጣቻቸው ተጽእኖ ፈጣሪ አዋጆች ~ የብር የምንዛሬ አቅም ~ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ስሌት ማስተካከያ = የቀድሞው ዋጋ*[1+(ጭማሬ/100)] የቴግራም ቻናላችን: t.me/DSDConstruction ሊጽፉልን ካሰቡ t.me/DSDCon ቲክቶክ: www.tiktok.com/@dsdconstruction
🏷ለባከነ የግንባታ ጊዜ ''የጊዜ የጉዳት መቀጫ'' /Liquidated damage/
➡️በኮንስትራክሽን ውል ላይ የውሉ የግንባታ ስራ ተብሎ የተቀመጠውን በዲዛይኑ እና ዝርዝር ስፔስፊኬሽኑ መሰረት በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ሰርቶ ማጠናቀቅ የተቋራጩ ሀላፊነት ነው፡፡
➡️ተቋራጩ የውሉን የግናባታ ስራ በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በወቅቱ ሰርቶ ያላጠናቀቀ እንደሆነ ከውሉ ማጠናቀቂያ ጊዜ/completion date/ በኋላ ግንባታው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ለእያንዳንዱ ቀን ተቋራጩ የግንባታ መዘግየት ምክንያት ለአሰሪው የጊዜ የጉዳት መቀጫ/Liquidated damage/ የመክፈል ሀላፊነት ይኖርበታል፡፡
⏭በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ሲባል ምን ማለት ነው?
▶️አንዳንድ አሰሪዎች/client/ በግንዛቤ እጥረት በውሉ ላይ የተቀመጠው ተቋራጩና አሰሪው ለግናባታው ማጠናቀቂያ የተስማሙበትን የቀን ብዛት/የጊዜ እርዝማኔ/ መቆጠር የሚጀምረው ውሉ በግራ ቀኙ ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ እንደሆነ ይረዱታል፡፡ይሄ አረዳድ ስህተት ነው፡፡
⏹በኮንስትራክሽን ውል ስለ ጊዜ አቆጣጠር በተለይ
⏺የግንባታ ውል የተደረገበት ቀን/contract signing date/ ፣
⏺ሞቢላይዜሽን ፔሬድ/mobilization period/፣
⏺የሳይት መረከቢያ ቀን/site handover/፣
⏺የስራ መጀመሪያ ቀን/commencement date/ እና
⏺የስራ ማጠናቀቂያ ቀን/completion date/ የሚሉትን መረዳት የግንባታ የጊዜ የጉዳት መቀጫ/Liquidated damage/ የሚለውን በአግባቡ ለማወቅ ይጠቅማል፡፡
⏹በመሰረቱ በውሉ የተቀመጠው የስራ ማከናወኛ የጊዜ ገደብ መቆጠር የሚጀምረው ተቋራጩ የግናባታውን ሳይት ከአሰሪው ከተረከበ በኋላ ነው፡፡ይሄውም ከሳይት ርክክብ በኋላ የስራ መጀመሪያ ቀን /commencement date/ በመሀንዲሱ የሚወሰን እና ለተቋራጩ የሚገለጽለት ይሆናል፡፡
⏹እንግዲህ በመሀንዲሱ ከሚወሰነው የስራ መጀመሪያ ቀን ጀምሮ በውሉ ላይ የተቀመጠው ቀን ይቆጠርና የስራ ማጠናቀቂያ ቀን/completion date/ መቼ እንደሆነ ለማወቅ ያስችላል ማለት ነው፡፡
➡️እዚህ ላይ ሊታወቅ የሚገባው ነገር በኮንስትራክሽን ውሉ ላይ የተወሰነውን የስራ ክፍል ከውሉ የማጠናቀቂያ ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ውል ሊደረግ የሚችልበት እድልም አለ፡፡/Partial completion/ ማለት ነው፡፡የቀን አቆጣጠሩ ከላይ እንደተብራራው የሚሰላ ይሆናል፡፡
*⃣ስለሆነም የግንባታ መዘግየት ቅጣት የሚለው ጉዳይ የሚመጣው ተቋራጩ የውሉን የግንባታ ስራ በውሉ ስራ የማጠናቀቂያ ጊዜ /completion date/ ሳያጠናቅቅ የቀረ እንደሆነ ነው፡፡የገንዘብ ቅጣቱ የሚጣለው በተቋራጩ ላይ ነው፡፡
*⃣ተቋራጩ ግንባታውን ላዘገየበት ለእያንዳንዱ ቀን በውሉ የተቀመጠውን የጊዜ ኪሳራ መቀጫየሚከፍል ይሆናል፡፡በነገራችን ላይ እየተቀጡ መስራት ለተቋራጩ መብትም ጭምር ነው፡፡ይህ ማለት አሰሪው የውሉ ማጠናቀቂያ ጊዜ ስላለቀ ውል አቋርጣለሁ ማለት አይችልም፡፡በውሉ ላይ የተቀመጠው የመዘግየት ቅጣት ጣሪያ መጠን ከሞላ በኋላ ግን አሰሪው ውል ማቋረጥ ይችላል፡፡ውል ከተቋረጠ በኋላ የመዘግየት ቅጣት የሚባል ነገርም የለም፡፡
*⃣*⃣ሌላው ተቋራጩ ወደ መዘግየት ቅጣት እንዲገባ ከመደረጉ አስቀድሞ በአግባቡ መረጋገጥ ያለበት ነገር መሀንዲሱ ለተቋራጩ የጊዜ ማራዘሚያ/Extension of Time / ፈቅዷል ወይስ አልፈቀደም የሚለው ነጥብ ነው፡፡ምክንያቱም ለተቋራጩ የጊዜ ማራዘሚያ ተፈቅዶለት ከሆነ የግንባታ ማጠናቀቂያ ጊዜውም አብሮ ስለሚራዘምና ቀኑ ስለሚቀየር ነው፡፡
▶️የሀገራችንን የህግ ማእቀፍ በዚህ ረገድ ምን ይላል? የሚለውን ለመመለስ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1887 እስከ 1895 ድረስ የተደነገጉትን መዳሰስ ይጠይቃል፡፡
*⃣በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1889 ላይ ተዋዋዮች በውላቸው ምናልባት አንደኛው ወገን እንደውሉ ግዴታውን ያልፈጸመ እንደሆነ ወይም አጓድሎ የፈጸመ እንደሆነ ወይም አዘግይቶ የፈጸመ እንደሆነ የሚከፍለውን የመቀጮ መጠን አስቀድመው በውላቸው ለመወሰን እንደሚችሉ በሚፈቅድ መልኩ ተደንግጓል፡፡
*⃣እዚህ ላይ የውል ግዴታን አዘግይቶ መፈጸም ስለሚያስከትለው ቅጣት የሚዋዋሉት በተለይ የግንባታ ጊዜ የጉዳት መቀጫ/liquidated damage/ የሚመለከት ይሆናል፡፡
▶️የመዘግየት ቅጣት ስምምነት ባለ ጊዜ አሰሪው የውሉ ስራ እንዲፈጸምና የቅጣት ገንዘቡንም ለመቀበል መብት እንደሚኖረው የፍ/ህ/ቁ 1890(2) ይደነግጋል፡፡
*⃣እንደዚሁም አሰሪው ኪሳራ ባይደርስበት እንኳ የመዘግየት ቅጣት ገንዘቡ ሊከፈለው እንደሚገባ የፍ/ህ/ቁ 1892(1) ይደነግጋል፡፡እንግዲህ ተቋራጩ ግንባታውን በወቅቱ ያላጠናቀቀው አሰሪውን ሆነ ብሎ ለመጉዳት አስቦ ጉልህ በሆነ ቸልተኝነት ወይም በከባድ ጥፋት መሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ አሰሪው በውሉ ከተቀመጠው የቅጣት ገንዘብ በላይ በደረሰበት ትክክለኛ ጉዳት መጠን ልክ ከተቋራጩ ላይ ኪሳራ ለመጠየቅ እንደሚችል የፍ/ህ/ቁ 1892(2) ይደነግጋል፡፡
▶️ሌላው የመዘግየት ቅጣት መጠን በዳኞች ሊቀነስ የሚችልበት እድል ስለመኖሩ የፍ/ህ/ቁ 1893 ይደነግጋል፡፡ይሄውም ተቋራጩ ግዴታውን በከፊል የፈጸመ ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡
*⃣ይህ ማለት ተቋራጩ ባከናወነው ስራ ሁሉ ቅጣት የሚጣልበት አይሆንም ማለት ነው፡፡
▶️በዚህ ረገድ በሲቪል ግንባታ ስራዎች ቋሚ የውል መተዳደሪያ አንቀጽ 47(1) ላይ ተቋራጩ ስራውን በውሉ የማጠናቀቂያ ጊዜ ካላጠናቀቀ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ቀን የውሉን ዋጋ 1/1000 እንደሚከፍል እና ይሄውም አጠቃላይ መጠኑ ከውሉ ዋጋ ከ(10-20%)መብለጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡
*⃣ሆኖም ግን በከፊል ለተከናወነው ስራ መሀንዲሱ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በሰጠ ጊዜ የቅጣቱ መጠን የሚሰላው ባልተከናወነው ስራ መጠን ዋጋ ላይ በመመስረት ይሆናል ማለት ነው፡፡
▶️በመጨረሻም የመዘግየት ቅጣት በኛ ሀገር ከላይ እንዳየነው እንደቅጣት የሚቆጠርና በህጉ ቅጣቱ እውቅና የሚሰጠው ሲሆን በኮመን ሎው የህግ ስርአት ግን ቅጣት አይደለም፡፡
*⃣በኮመን ሎው የጊዜ የጉዳት መቀጫ በአሰሪው ላይ ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል ሆኖ መመዛዘን የሚኖርበት ሲሆን የቅጣት አይነት ተመሳሳይ ባህሪ ካለው ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
https://t.me/ptconstruction
በአዲስ አበባ ሁለተኛው ምዕራፍ የ ኮሪደር ልማት እየተከናዎኑ ያሉ ስራዎች ::
+3
ማስታወቂያ:-NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ
መገኛ አድራሻው ቦታ:-📍- ተክለሃይማኖት በርበሬ በረንዳ
ስልክ ቁጥር:-🔺📞+251- 944454610 🔺📞+251- 952730999 #LTZ 28 #LTZ 38 #LTZ 48 #CHS ከ ባለ 12mm ጀምሮ .... #RHS #I BEAM #U CHANNEL #H BEAM #Mesh Wire #የ ኣጥር ሽቦ #Galvanized Pipe #Angle #Aluminium Sheet #D ብረት#8 ቁጥር #ፌርሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ! ስትፈልጉ በቀጥታ ይደውሉ.. .
👉በአደይ አበባ ፋብሪካ የቀን ሰራተኛ ላይ ግድግዳ ተንዶበት ህይወቱ አለፈ
🏷ዛሬ ዓርብ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋድ 4ሰአት ከ25 ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አደይ አበባ ግቢ ዉስጥ በደረሰ የስራ ላይ አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ህይወቱ ያለፈዉ ግለሰብ ዕድሜዉ 32 ዓመት የተገመተ የቀን ሰራተኛ ሲሆን በፋብሪካዉ ምድር ቤት ዉስጥ የነበረ የቀድሞ የዉሀ ገንዳን ግድግዳ በማፍረስ ላይ እያለ ግድግዳዉ ተንዶበት በደሰበት ከፍተኛ ጉዳት ህይወቱ ማለፉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የፖሊስ አባላት እንዲሁም የፋብሪካዉ ሰራተኞች የግለሰቡን አስከሬን ማዉጣት ችለዋል።
💫በትላንትናዉ ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ፊጋ መብራት ሀይል እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በህንጻ ግንባታ ስራ ላይ የነበረ የ27 ዓመት ወጣት ህይወቱ ማለፉ ብስራት መዘገቡ ይታወሳል።
በማናቸዉም የህንጻና መሰል ግንባታዎች መሰል አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊዉን የደህንነት መርሆዎችን መከተል የሚገባ ሲሆን ለዚሁም ከባለሞያዎች ባሻገር አሰሪዎች ከፍተኛ ኃላፊነት አለባቸዉም ተብሏል።
Via ዳጉ ጆርናል
@etconp
የአርማታ ብረታ ብረት አቅራቢ🏗🇪🇹
Ethio-Base Business Group💠
• 18-24
• Grade75
• የሀገር ውስጥ እና የቱርክ
የአርማታ ብረታ ብረት
• በጅምላና በችርቻሮ
• በተመጣጣኝ ዋጋ እናቀርባለን
📍አድራሻ፦ ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ቡልጋሪያ በሚወስደው ድልድይ ጫፍ ላይ ያገኙናልEthio-Base Business Group ☎️+251911731977 📞+251972670787
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
