የፅዮን ደጆች ቅኔ ተሞሉ ለድንግል ክብር እልል እያሉ🙏🙏🙏🙏
@mahaber_Tsion በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ መዝሙሮችን ይሰጡበታል፡፡ 🙏 እስትንፋ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 ) የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇 @mahaber_Tsion @mahaber_Tsion ሀሳብ አስተያየት ካላቹ @Enatekedanemiherat ለይ
Больше- Подписчики
- Просмотры постов
- ER - коэффициент вовлеченности
Загрузка данных...
Загрузка данных...
✝️መናገሻ —አምባ ማርያም🙏 *** ከአዲስ አበባ ወደ ወለጋ በሚወስደው መውጫ በ35 ኪ, ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ነች። የተተከለቸው በ13ኛው መ,ክ,ዘ, አፄ ይስሐቅ በሀገራችን በነገሱበት ጊዜ ነው።ቅዳሴ ቤቷ ሲከበር በታላቁ ቅዱስ አባት "በአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ" ተባርኮ ሲሆን በቤተ መቅደሷ በመጀመሪያ የገባችውም ጽላት ታቦተ ልደታ ለማርያም ነበረች። ገዳሟ ስትመሠረት ቀዳሚ ስሟ "አምባ ማርያም ነበር።አሁን የምትጠራበትን "መናገሻ" የሚለውን መጠሪያ ያገኘችው አፄ ዘርዐ ያዕቆብ የጌታችንን ግማደ መስቀል ወደ ሀገራችን ባስገቡበት ጊዜ" መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር" እያለ የሚታያቸውን ህልም ለመፈፀም በተለያዩ ቦታወች ሲዘዋወሩ ወደዚህ ተራራ መጥተው መስቀሉን አስቀምጠውት ነበር እናም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያ ቦታ የመስቀሉ መኖሪያ ተራራ እንዳልሆነ ጌታችን ሲገልፅላቸው ከዛ ተነስተው ሲሄዱ ከግማደ መስቀሉ ጋር ከግብፅ ከመጡት ንዋዬ ቅዱሳት መሀከል ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ የሣለውንና አይሁድ ጌታችንን አነገሥንህ እያሉ ሲዘባበቱበት የሚያሳየውን አክሊለ ሶክ ደፍቶ ያለበትን ሥዕል በዛ በአምባ ማርያም አስቀምጠውት ሄደው ነበርና የንግሥናው ሥዕል ያለበት ቦታ ብለው ለመጥራት የገዳሙን አካባቢ "መናገሻ " አሉት በዚህ ምክንያት አምባ ማርያም የተባለው ስሟ ተቀይሮ ቀረ። ደብሯ ከተመሠረተችበት ዘመን አንስቶ ብዙ ግልጋሎቶችን ለምዕመኗ ስትሰጥ ቆይታ ግራኝ አህመድ የጥፋት ወረራው ለመፈፀም በሀገራችን በተነሳበት ጊዜ ይህችን ገዳም ሊያቃጥል ሲመጣ ተሠውራ እንደጠፋችበት በታሪክ ተመዝግቧል ለዚህም በ 1994 ዓ,ም ጋራው መድኃኔዓለም ሊሰራ መንገድ በሚጠረግበት ጊዜ በቁፋሮ የወጡት በርካታ ንዋዬ ቅዱሳት ምስክር ናቸው። ይህች ገዳም ከግራኝ አህመድ ጊዜ አንስቶ ጠፍታ ቆይታ እግዚአብሔር ነገሩን የሚገልጥበት ጊዜ ሲደር አባ ወልደ ጊዮርጊስ ለተባሉ መነኩሴ አሳወቃቸውና በ191ዐ ዓ,ም መቃኞ ሰርተው ሐምሌ 21 ቀን በእመቤታችን ስም ታቦቷን አስገቡ። ከዓመት በሗላ ዋናው ሕንፃ ቤተ መቅደስ ሥራው ተጀምሮ በ1915 ዓ,ም ከዛሬ 96 ዓመት በፊት ተጠናቀቀና ቅዳሴ ቤቷ መስከረም 21 ቀን ተከበረ። የወቅቱ ጳጳስ ግብፃዊው አቡነ ማቴዎስም ገዳሟን ባረኩና የመጀመሪያውን አስተዳዳሪ አባ ወልደ ጊዮርጊስን አድርገው ሾሙ። እኒህ መነኩሴ አባ ወልደ ጊዮርጊስ ከጊዜ በኋላ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ፓትርያርክ የሆኑት አቡነ ባስሊዮስ ነበሩ።እነሆ ገዳሟ ከዛ ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን በታላቅነቷ ትታወቃለች እርሷ ካለችበት ተራራ አናት ላይም ጋራው መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.