cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Esat_tv_News

World news ትኩስ እውነተኛ ወቅታዊ ሀገራዊ ዜናዎች ከፈለጉ join ይበሉ ይቀላቀሉን👈🇪🇹 በቻናላችን አለማችን🌐🌎 ላይ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ join በማለት ይታደሙ🌎🌐 ሃሳብ አስተያየት ካአልዎት -👇⬇⬇⬇⬇⬇🔽 [💌📩📤💬inbox @riz_one123

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
196
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል አከባበር በፎቶ
Показать все...
በትናንቱ ምርጫ የተሳተፉ መራጮች የተረጋገጠ የምርጫ ውጤት በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እስኪገለፅ በትዕግስት እንዲጠባበቁ ተጠየቀ ************************* ትናንት መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም በተካሄደው ምርጫ የተሳተፉ መራጮች በቦርዱ የተረጋገጠ የምርጫ ውጤት በቦርዱ ብቻ እስከሚገለፅ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቁ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጥሪ አቀረበ፡፡ መራጮች ከሌሎች ምንጮች የሚገለጹ ማናቸውንም የምርጫ ውጤትና የውጤት ትንበያ ከመቀበልና ለሌሎች ከማጋራት እንዲቆጠቡ ቦርዱ ጠይቋል፡፡ መራጮች በምርጫው ሂደት ያሳዩትን በትዕግስትና በጨዋነት የተሞላ ተሳትፎም ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አድንቋል፡፡
Показать все...
በለንደን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት በተካሄደ የገቢ ማሰባሰቢያ ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ ************************** “ለወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል መሪ ቃል በለንደን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት በተካሄደ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰበሰበ፡፡ ገንዘቡ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከdefend Ethiopia የዩናይትድ ኪንግደም ግብረሃይል ጋር በመተባበር ባካሄዱት የገቢ ማሰባሰቢያ መሰብሰቡ ተገልጿል፡፡ በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር የተካሄደውን የገቢ ማሰባሰቢያ በማስመልከት ለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ በዚሁ ወቅት በስኬት የተጠናቀቀው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ኢትዮጵያውያን ከውስጥም ከውጪም የሀገራቸውን ሉዓላዊነት ለመፈታተን የሚሞክሩ ሀይሎችን በጋራ የመመከት የቆየ ታሪካቸውን ይበልጥ አጎልብተው የመጡበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተለያዩ አጀንዳዎችን በመፍጠር ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል እና አንድነታቸውን ለመሸርሸር የሚፍጨረጨሩትን በንቃትና በትጋት መታገል ይገባል ያሉት አምባሳደር ተፈሪ አጀንዳችን ኢትዮጵያዊነትና ኢትዮጵያን ማበልጸግ ነው ብለዋል፡፡ ማህበረሰቡን በዘር እና በጎሳ ለመከፋፈል የተደረገውን ያልተሳካ ጥረት አሸንፈው የወጡት በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እያደረጉት ያለው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያሰባሰቡት ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ (91 ሺህ 34 ፓውንድ ከ25 አምስት ሳንቲም) ከኤምባሲው በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መተላለፉን ገልጸዋል፡፡ ወቅቱ አዲሱና በህዝብ ይሁንታ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍትሃዊና ግልጽ በሆነ ምርጫ የተመረጠው መንግስት የሚቋቋምበት በመሆኑ በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የdefend Ethiopia የዩናይትድ ኪንግደም ግብረሃይል አስተባባሪ አቶ ዘላለም ተሰማ በበኩላችው የሀገሪቱን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ በመንግስት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን ለመደገፍ የሚደረገውን ጥረት ግብረ ሀይሉ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ሀገርን ለማፍረስ ሲኦልም ቢሆን እንወርዳለን ያለውን አሸባሪ ቡድን በወረደበት ሲኦል እንዲቀር የማድረግ የኢትዮጵያውያን ግዴታ በመሆኑ ማንኛውንም አስተዋጽኦ ለማድረግ ግብረሀይሉ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመጪው ኦክቶበር 9 ቀን 2021 በሚካሄደው የህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት መላው በዩናይትድ ኪንግደም እና ሰሜን አየርላንድ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲገኙ ጥሪ ማቅረባቸውን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡
Показать все...
ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ ድሮኖችን ሲያበር የተገኘ በሕግ ይጠየቃል‼️ 🗣 የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለዜጎች ሰላም መረጋገጥ እንዲሁም የቁልፍ መሰረት ልማቶችን ደህንነት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመጠበቅና ስጋቶችን ለመከላከል ሲባል ድሮኖችን ያለምንም ህጋዊ ፈቃድ ለቀረፃ መጠቀምም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡ የሀገሪቱን ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑን የጠቀሰው ተቋሙ አንዳንድ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሚመለከተው አካል ህጋዊ ፈቃድ ሳያገኙ ድሮኖችን በሀገሪቱ በሚካሄዱ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ህዝባዊ ሁነቶች ላይ ለቀረፃ ሲጠቀሙ እና ሲያበሩ እየተስተዋለ መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጉዳዩ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አውቀው ከህገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አሳስቧል፡፡ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ ድሮኖችን ለቀረፃ ሲጠቀም እና ሲያበር የተገኘ ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ በህግ እንደሚጠየቅ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስጠንቅቋል። @Esat_t_news
Показать все...
የአማራ ክልል ምክር ቤት ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬን አፈ-ጉባዔ አድርጎ ሾመ‼️ የአማራ ክልል ምክር ቤት ወ/ሮ ፋንቱ ተስፍዬን አፈጉባዔእንዲሁም አቶ አማረ ሠጤን ም/አፈ-ጉባኤ በማድረግ መርጧል። አፈ-ጉባዔዎቹ ሀቅና ህግን በማስቀደም የወከላቸውን ህዝብ ለማገልገል ቃለ መሀላ ፈፅመዋል። @Esat_t_news
Показать все...
. "ውበት እንደ እንደ ሳባ. . . ሁሉም የሚመኛት ማንም ያላገኛት፣ በአፈጣጠር ቅኔ፣ለኔው የተቀኛት፣ ውበት ላይ ስብዕና. . . በሱ ላይ አዕምሮ፣ የጥበቡ ዋቢ፣ሰንደቅ የተፈጥሮ! ስወድቅ ምርኩዜ ናት፣ ስነሣ ማጌጫ፤ እሷ ማለት ለኔ የዘላለም ምርጫ! አግኝቼ አልጠግብሽ፣ ኖረሺኝ አላጣሁ፣ ካወቅኩሽ ጀምሮ ከሐሴቴ አልወጣሁ፣ በቁንጽል ሣቋ ላይ. . . እናቴን ዐያለሁ. ... ሐገሬን ዐያለሁ እህቴን አያለሁ ኢትዮጵያን🙏🙏🙏🙏 አያለሁ . . ." . . . . By Girma🙈🙈
Показать все...
ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቀጣይ አምስት አመታት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ እንዲመሩ ተመረጠዋል‼️ እየተካሄደ ባለው የአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የምክር ቤት ምስረታ ስነ-ስርአት ላይ በቀጣይ አምስት ዓመታት ከተማ ከንቲባ እንዲመሩ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በሙሉ ድምጽ ተመርጠዋል። @Esat_t_news
Показать все...
ወ/ሮ ፋይዛ መሀመድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ ጉባኤ በመሆን ተመርጠዋል‼️ 35 ዓመታቸው ሲሆን የመጀመሪያ በኢኮኖሚክስ እና ቢዝነስ አድምኒስትሬሽን ዲግሪያቸውን ሰርተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱ ሲሂን እንግሊዝና ዴንማርክ በተለያዩ ስራዎች ላይ አገልግለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ በመሆን አሁንም ድረስ በማገልገል ላይ ናቸው፡፡ በሀገር ውስጥና በውጪ የያዙትን ልምድ በመጠቀም ለአዲስ አበባ ህዝብ ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን 138 ድምፁ ፀድቆ አሁንም በምክትል አፈ ጉባኤነት ለማገልገል ቃል ገብተዋል፡፡ @Esat_t_news
Показать все...
ኢትዮጵያውያን ሴት አትሌቶች በበርሊን ማራቶን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸነፉ ‼️ ኢትዮጵያውያን ሴት አትሌቶች በዛሬው ዕለት በጀርመን በተካሄደው የቢኤምደብልዩ በርሊን ማራቶን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል። አትሌት ጎይቶም ገብረሥላሴ በውድድሩ 2:20.09 በሆነ ሰዓት በመግባት አሸንፋለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሕይወት ገብረኪዳን 2:21.23 በሆነ ሰዓት በመግባት ሁለተኛ ስትወጣ አትሌት ሔለን ቶላ 2:23.05 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ወጥታለች። @Esat_t_zena
Показать все...
የተለያዩ የክልል መስተዳደሮች አዲስ መንግስት የሚመሰርቱበት ቀን ይፋ አደረጉ ************************** የአማራ ክልል፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል፣ የሲዳማ ክልል እና የጋምቤላ ክልል በቀጣይ ሳምንት አዲስ መንግስት ይመሰርታሉ፡፡ የአዲሱ መንግስት ምስረታ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል መስከረም 19፣ በጋምቤላ ክልል፣ በአማራ ክልል እና በሲዳማ ክልል መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚሆን ክልሎቹ አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም፣ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የአዲሱ መንግስት ምስረታ መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚሆን አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡ በእንዳልካቸው አክሊሉ
Показать все...