cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

beni melese

ፈጣን ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት ይህንን የቴሌግራም ቻናል Join በማለት ይከታተሉ👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/gizatmeles

Больше
Эфиопия10 801Амхарский9 090Категория не указана
Рекламные посты
200
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ኢትዮጵያውያን የተናበቡበት ነው! የአፍሪካ ጉዳይ ማድረግም ያስፈልጋል። በአገር ቤት ብቻ ሳይሆን በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትናን ላይ የታወጀውን ጥቃት በቁጣ ተቃውሟቸውን እያሰሙበት ነው። ይህ በለንደን የተደረገ ሰልፍ ነው። በሌሎች አገራትም ሰልፎች እየተደረጉ ነው። ዳያስፖራው የጀመረው ንቅናቄ የሚያኮራ ነው። በሰልፎቹ ጥቃቱ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ጭምር መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል። የአፍሪካ ነፃነት ምልክት የሆነት ተቋም፣ የአፍሪካ ምልክት የሆነው ሰንደቅ፣ በአፍሪካ አገር በቀል የሆነውን ፊደል ጠልተው ነው እናፈርሳታለን ያሉት። ዋና ዋና የአፍሪካ አገራትንም ጭምር የሚመለከት መልዕክት ይዞ በመውጣት፣ ዶክተር ወዳጀነህ እንደገለፀው "የአፍሪካ ትምክት" የሆነች ተቋም መጠቃቷን ማሳወቅ ያስፈልጋል። አፍሪካውያንም፣ በዓለም የሚገኙ ጥቁሮችንም ባለውለታቸው እንደተጠቃች ማሳወቅ ያስፈልጋል። ጉዳዩ የአፍሪካ መሆኑን የሚያሳዩ መልዕክቶች በስፋት መተላለፍ አለባቸው። ሰልፈኞቹ በአቋም መግለጫቸው ቤተ ክርስቲያን ያላትን አስተዋፅኦና የተፈጠረውን የሚገልፅ ዝርዝር አዘጋጅተው ለአፍሪካ አገራት ኤምባሲዎች ማስገባት ቢችሉም መልካም ነው።
Показать все...
የተወገዘው ቡድን የመንግስት ታጋች ነው። በዚህ ወቅት በዓለም ላይ እንዲህ ያለ የእገታ ድራማ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም። በፀጥታ ኃይል እያስጠበቀ፣ ስልካቸውን ቀምቶ፣ የቤተ ክርስቲያን በር ሰብሮ አስገብቶ የፃፈውን አንብቡ ይላቸዋል። ዛሬ ይቅርታ የጠየቁት አባት ከእገታ ያመለጡ ናቸው። ቀሪዎቹም እድል ቢያገኙ ማምለጥ ይፈልጋሉ። ስልካቸውን ቢመልሱላቸው የመጀመርያ የሚደውሉት ለአስታራቂ ነው። በዛሬው የቤተ ክርስትያን መረጃ ደግሞ የተሰማው ሌላ ጉድ ነው። መንግስት የታጋቾቹን አግቶ ከማስቀመጡ ባሻገር አቡነ ማቲያስ ከእናንተ ጎን ናቸው በሚል አጭበርብሯቸው ነበር።
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ተቃውሞው ሲበረታ ኢንስፔክተሩን ወደ ስራው መልሰውታል! ኢኒስፔክተር አንተነህ አያሌው አየር ጤና ኪዳነ ምህረት ህገወጡ የጳጳሳት ቡድን ሊገባ ነው መባሉን ተከትሎ የተነሳውን ግርግር በሀላፊነት ማረጋጋቱ አይዘነጋም። ይህንን ባደረገ ማግስት ከስራ ገበታው ላይ መባረሩ ተሰምቶ ነበር። ይህንን መረጃ ለማጣራት የደወልንለት ኢንስፔክተር አንተነህ ለጊዜው ከስራ ታግዶ እንደነበር ገልጿል። ከጊዜያዊ እገዳ ውጪ የደረሰበት ነገር እንደሌለ ያከለው ኢንስፔክተሩ አሁን በመደበኛ ስራው ላይ መሆኑን አረጋግጧል። ኢንስፔክተር አንተነህ በቅርቡ አየር ጤና ሊፈስ የነበረን ደም በብቁ የአመራር ስልት ማክሸፉ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲገለፅ እንደነበር ይታወሳል። ለፈጣን መረጃ የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Gionamhara
Показать все...
በሻሸመኔ ሰማዕትነት ከተቀበሉት መካከል ሃገሩን በታማኝነት አገልግሎ ጡረታ ወጥቶ የነበረው ወታደሩ ሰማእት ይገኝበታል። በገጀራ፣ በዱላና፣ በድንጋይ ቀጥቅጠው ነው የገደሉት። ሆስፒታል ቢገባም ህይወቱ አልተረፈችም።
Показать все...
ናሁ ተረክበ ዘማሰነ ንዋየ ሥላሴ እነሆ የጠፋው የሥላሴ ገንዘብ ተገኘ ‼ ቅዱስ ያሬድ
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.