553
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
553
መዘግየትህን አትጥላዉ !
ነገሮች በፍጥነት እንዲ ሳኩልህ
አትፈልግ ! መዘግየትህን
አትጥላዉ ! በትምህርት ፣ በስራ ፣
በሀብት ፣ በፍቅር ግንኙነት ወይ
በትዳር አንተ እንዳሰብከዉ
አለመሆኑ ለበጎ እንደሆነ
አስብ !
ወደ ኋላ የተንደረደረ
ረጅም ርቀት እንደ ሚተኮስ
አስብ ፤ ወዳጄ ጥያቄህ
ቶሎ ያልተመለሰዉ ጊዜዉ
ስላልደረሰ ወይ ደግሞ ፈጣሪ
የተሻለዉን ሊሰጥህ
ይሆናል ።
አንተ ብቻ ጥረትህን ሳታቋርጥ
ታገስ ፤ የህይወትህ ፀሀይ
መዉጣቷ አይቀርም !
553
የውበት ሚስጥሩ
""""""""""""""""""""""
ከቁንጅናም በላይ የውበት ሚስጥሩ፤
ከላይ መዋብ ሳይሆን አልያም ማማሩ፤
የእርሱ መለያ ከመጥፎ እና ጥሩ፤
ይኸ ነው መለኪያው የሰው ልጅ ምግባሩ።
ተውቦ መታየት በሌሎች ዓይን ላይ፤
ተጊጦ መቅረብ ተሽቀርቅሮ ከላይ፤
ዋጋኮ የለሁም ሊሆን የአፈር ሲሳይ።
✍ጦቢያ
ሐምሌ/22/2008፦አርብ
553
እንባ ለየት ጥቅሙ?
""""""""""""""""""""""""
ዓይን እንባን አዝሎ፤
እንባም ተድቦልቡሎ።
አርጎ ጉንጭን መንገድ፤
ቁልቁል ሲወራርድ።
ሕይወት ድሪቷሟ አብዝታ ፈተና፤
በጎምዛዛ ቃና።
እንባም መፍሰስ ስራው በምሬት ተከቦ፤
እልህን ደርቦ።
ጉንጭም የእንባ መንገድ እንባንም ተጠምቶ፤
ዓይን ውኃ አውጥቶ።
ጥሙን ቢቆርጥለት በእንባ ቢያወረዛው፤
አስክሮ በደስታ አንጀንቱን ቢያወዛው።
ያኔ ምን መጣ? እንባ በመፍሰሱ፤
ምን ጥቅም አስገኘ? ዓይንን ማደፍረሱ።
እልህ አላሰከነ ምሬትን አልከላ፤
ነገር አልቀየረ ሄዶ ወደ ኃላ።
ዓይንን አላጠራ ዕታታን አልገለጠ፤
የተፈለገውን በፍጥነት አልሰጠ።
በአፍንጫ ላይ አርጎ ዓይንን አስጨንቆ፤
ሽፋሽፍት ተፍታቶ ከላይ ታች ተላቆ፤
ቢፈስ ተጨምቆ።
ቢመጣም ጎርፍ ሆኖ እየተሯሯጠ፤
ምን ያደርጋል? ታዲያ መሻትን ካልሰጠ።
አሮጌን ካልናደ አዲስ ካላቆመ፤
የድሮን አውርዶ ዘንድሮን ካልሾመ፤
እንባ በመፍሰሱ ኧረ ምን ጠቀመ?
እናም
ይብቃው ይቅር ወዲያ እንባ ማፍሰስ ዓይኔ፤
ጥሩውን ገላልጦ ካላረገው ጎኔ፤
ፊቴ ካላመጣ ካላሳየኝ ለኔ።
ቢቀርስ ቢመጣ ከቶ ምን ሊረባኝ፤
እንባስ ይቅር ወዲያ አላለቅስም በቃኝ።
✍ጦቢያ
መጋቢት/12/2011 ሐሙስ
553
ውሸትና እውነት
እንዲህ የሚል የጥንት አፈ-ታሪክ አለ፡፡ “ውሸት” እና “እውነት” አንድ ቀን ተገናኙ፡፡ ውሸት ለእውነት፣ “ዛሬ እጅግ ደስ የሚልና አስገራሚ ቀን ነው” አላት፡፡ እውነት ወደ ሰማይ አሻቅባ ካየች በኋላ እውነትም ግሩም ቀን ነበረና በአዎንታ ተነፈሰች፡፡
አብረው ረዘም ላለ ጊዜ ካሳለፉ በኋላ አንድ ኩሬ ጋር ደረሱ፡፡ ውሸት ለእውነት፣ “ውኃው ደስ የሚል ነው፡፡ ለምን አንድ ላይ ውኃ ውስጥ ግብተን አንታጠብም?” አላት፡፡ እውነት በጥርጣሬ ውኃውን ከሞካከረች በኋላ በእርግጥም ጥሩ መሆኑን አረጋገጠች፡፡ ብዙም ሳይቆዩ ልብሳቸውን አውልቀው መታጠብ ጀመሩ፡፡
ውሸት በድንገት ከውኃው በመውጣት የእሱን ልብስ እዛው ትቶና የእውነትን ልብስ ለብሶ ከአካባቢው ተሰወረ፡፡ በድርጊቱ በጣም የተበሳጨችው እውነት በፍጥነት ከውኃው በመውጣት ውሸትን አግኝ ለመያዝና ልብሷን ለማስመለስ ብትሞክርም ልታገኘው ስላልቻለች ወደ ውኃው ተመልሳ ለዘላለም ተደብቃ ቀረች፡፡
ምንም እንኳን ልብሷን ተሰርቃ ራቁቷን ብትሆን እውነት ትሻለናለች በማለት እውነትን የሚፈልጋት ሰው ስለጠፋ ውሸት የእውነትን ልብስ ለብሶ በአለም ዙሪያ እየዞረ የሕብረተሰቡን የውሸት ጥማት እያረካ ይኖራል፡፡
ከእውነት ይልቅ ውሸት የሚወደድበትና የሚፈለግበት ዘመን!
553
ተመስገን ነው🙏🙏🙏
""""""""""""""""
ይመስገን ነው ለሠጠኝም ለነጠቀኝ አልሆን ወቃሽ፤
ሠው ተጓዡ 😏ለሄደውም ለመጣሁም ተመላላሽ፤
አይከፋኝም ተመስገን ነው የኔ ምላሽ።
አይቻለሁ እልፍ ቀናት የአይኔ ባህር ተደፋርሶ፤
ሞግቻለሁ ከመቅደሱ ለምን ብዬ በእንባ ለቅሶ።
አንገቴንም ሰግጌለት ስዕሉ ፊት ተገትሬ፤
ፍርደ ገምድል ብዬዋለሁ በሀዘን ብሶት ተሰብሬ።
ግና ዛሬ*2....
ምን በወጣኝ በ'ሱ ስራ እኔ ጥልቅ፤
አምላክነት የባህሪው ሁሉን ፈጥሮ ሁሉን የሚያቅ፥
ስለሆነ....*2
ለሡ ትውት "ለምን"ን ቃል፤
በተመስገን አፌን ቃኝቷል።
ተመስገን ነው.....
ሠው እግረኛው እዚህም እዚያም የለመደ፤
ና ሳይባል እንደመጣ ሂድ ሳይባል ለምን ሄደ።
ለምን ሸሸ ወሰድክብኝ አልለሁም፤
ካልመለስከው ብዬ አምላክን አልሞግትም፥
እንደሁም.....
እሰይ ሄደ ሁሉን ሰሪ በየጊዜው፤
ቢመጣልኝ ባይጠቅመኝ ነው የወሰድከው።
ቆሜ የምለው ተመስገን ነው ከመቅደሱ፤
ያውቅ የለም ወይ ሚበጀኝን አምላክ እሱ፤
አላማርር መች ልገባ ስራው የሱ።
ሄደ ብዬ የምን ትንንቅ፤😏
ሚሆነኝን ከአንተ በላይ ማንስ ሊያውቅ።
ቤትህ ብርክክ ፊቴን በእንባ በተመስገን ቆሜ እርስ፤
ካ'ንተ ወዲያ ፍቅርን ለኔ ማን ሊለግስ፤
ካ'ንተ በቀር ማንስ ሊያነሳኝ ሊያጎነብስ፤
ይዤ አልመጣም አቤቱታ የለምን ክስ፤
በተመስገን አፌን እርስ።
ተመስገን ነው🙏🙏
✍ጦቢያ
553
😔 ደህና ነኝ🖤🖤
ደህና መሆን ማለት በስቃይ ላይ ስቃይ በህመም ላይ ህመም ማለት ከሆን እውነት ነው ደህና ነኝ ። ደህና መሆን ማለት እየሳቁ መስሎ ማልቀስ ተደብቆ ማንባት ከሆነ የምር ደህና ነኝ ። ደህና መሆን ማለት ሰው ሁሉ እያለ እየከፋኝ መደበቅ ከሆነ እውነት ስላቹ ደህና ነኝ ። ደህና መሆን ማለት ውስጥ እያለቀሰ ልብ እየደማ ከላይ መሳቅ ከሆነ እመን ደህና ነኝ ። 100 ሚሊዮኖች በሞሉበት ሀገር የልብን ሚጋራ የውስጥን ሚረዳ አንድ ሰው እንኳን ማጣት ደህና መሆን ከሆነ ደህና ነኝ ። ግን እውነት ደህና አደለሁም ደህና ነኝ ደህና ነኝ ያበዛሁት ቢያንስ ደህና አለመሆኔ ከገባቹህ ብዬ ነበር...... ግን ሚገባቹ አይመስለኝም😫😫
እስኪ እንደኔ ደህና የሆናችሁ ደህና ነኝ በሉ
553
ለጠየቅሽኝ እንቆቅልሽ ፣ ሲጠፋብኝ እኔ መልሱ
"ሀገር ስጠኝ" የምትዪኝ ፣ መልስ አታውቂም አንቺ ራሱ!😂
።።
ሁሉ ሀገሩን ተከፋፍሎ፣ ክልልሎችን እያጠረ
ኬት አምጥቼ ሀገር ልስጥሽ ?፣ ሀገር ማለት ሰው ነበረ።
ሰውም በዘር ተደራጅቶ ፣ ሀገር መሆን አቅቶታል
ገድሎ ሚኖር ተበራክቶ ፣ ሞቶ ሚያኖር ከሀገር ጠፍቷል!
።።።
ይህን እውነት እያወቅሽው ፣
ሀገር ስጠኝ አትበዪኝ ፣ በእንቆቅልሽ ልትለውጭኝ
ክልልና ዘር ነው ያለኝ ፣ ውሰጅና ሀገር ስጭኝ😂!
[ በላይ በቀለ ወያ ]
553
"በቃ ደስ ትለኛለህ"ለጠየከኝ ጥያቄ መልስ መስጠቴ ነበር😐"ብቀርብሽ ደስ ይለኛል"የሚያስብል ምላሽ ግን አልጠበኩም.........ልቤ ግማሽ ነው የተከፈለው...ውስጤን በረደኝ ቅዝቃዜ ተሰማኝ ለብርዱና ለሕመሙ ትከሻዬ ላይ የጣልኩትን ፎጣ ወደ አንገቴ የሙጥኝ ሳብኩት ቢያሞቀኝ ብዬ ከውስጥ ያልወጣ ሙቀት ላይን ያግል ይመስል...ልጠጣሁ ወደአፌ ያስጠጋሁትን የቡና ስኒ መለስኩት...ግራ ገባኝ ከውስጤ አንዳች አካሌ ተገምሶ የወደቀ መሠለኝ መልስ አጣሁ.. ምን ይባላል?🤔....ማባበል አልችልበትም ሲያለቅሱ ማዘን ስጎዳ ወደ ውስጤ ማልቀስ እንጂ ያካበትኩት🤷♀ውስጤን መግለጽ አልችልም መሠል መሄዱን ፈቀድኩለት...ፈልጌ አልነበረም ለዚህ አይነቱ ግብረ መልስ ስለማላውቅ እንጂ...ልቤ ያለሁን መንገር ስለማልችል እንጂ....ደስታው ከኔ ካልሆነ ብዬ ለቀኩት ስለያዝኩት....እንደወደደ...
ይዞኝ ካልበጀሁት ለቆኝ አይጎዳም ብዬ......ወይም ጨርሶ አልያዘኝ ይሆን🤔
ለስሜቴ ቅርቡ ብዕሬ ነው ላዋየሁ አነሳሁት ቢያስታምመኝ😔
"መጻፍ መጻፍ አለኝ፥ማቅለም ወረቀት፤
ብዕሬን ማስቆጣት፥ቀይ ደም ማስተፋት።"
ያለው ባለቅኔ ማን ነበር?🤔አመሠግነዋለሁ🙏🙏ያሽረኝ ከሆነ ልጣላው ሄድኩ.....ወረቀትና ብዕሬን
ብዕር ባይኖር ምን ይውጠኝ ነበር🤔
ዛሬ ጻፍኩት
✍ጦቢያ
553
አንዲት ምስኪን ሀገር
ዘወትር ጠዋት ማታ
ቁራሽ እንዲሰጣት አምላኳን ስትለምን
እጆችዋን ዘርግታ
መስጠት ማይሰለቸው
ቸር የሆነው አምላክ
ዘውትር ይሰጣታል
የእለት እንጀራዋን
እጆቹን በመላክ
/ታድያ እኛ ልጆችዋ/
መገንዘብ ተስኖን የበሬውን ፅናት የገበሬን ውጥን
ይህ ለምልም መሬትዋ
ሳይታረስ ቀረ ዘር እየመረጥን
/ታድያ እኛ ልጆችዋ/
ማድጋዋ ሞልቶን ገበታው ሳይጎድል
እየተራብን ነው
አጎራረሱ ላይ መስማማት አቅቶን
/ እስከመቼ ድረስ/
/እስከመቼ ድረስ/
/እስከመቼ ድረስ/
መብራት እየቻልን በጨለማ እንጓዝ
/እስከመቼ ድረስ/
ሸክም ሆኖ ይኑር የጥላቻችን ጓዝ
/እስከመቼ ድረስ/
ትርጉም ባጣ ቀመር
ግብ በሌለው አደን
ለቂም ተሰልፈን
ለፀብ እንቧደን
/እስከመቼ ድረስ/
/እስከመቼ ድረስ/
/እስከመቼ ድረስ/
በመጦርያዋ እለት
እናት በልጅ ታልቅስ
/ይልቅስ/
ተባብረን እናጥፋው ልክ ያልሆነን ምፀት
ይቅር ለመባባል ከልብ እንፀፀት
ሞት በፍቅር ይሙት ለፍቅር እንትጋ
የቆሰለ ያውቀዋል የሰላምን ዋጋ
ከርምጃችን ይጥፋ በራስ እግር ማንቀፍ
ነገን ለመሻገር እስኪ እንተቃቀፍ
/እስኪ እንተቃቀፍ/
/እስኪ እንተቃቀፍ/
/እስኪ እንተቃቀፍ/
ለሰላም እንዘርጋ የእጃችንን ልኬት
ጥፋትን ማመን ነው ሰው የመሆን ስኬት
/እስኪ እንተቃቀፍ/
ይቅር ለመባል ነው ይቅር ማለት እጣው
ትላንት ላይ ቆመን ነገን እንዳናጣው
/እስኪ እንተቃቀፍ/
/እስኪ እንተቃቀፍ/
እስኪ እንተቃቀፍ....♥️
@strangersthere
@strangersthere
553
"ባጭር ቀረን" ስንል - እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን
ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
።።።።
ፊታችንን ዐይተው
እንደተቸገርን - ካይናችን ላወቁ
ስለማርያም ብለን
እስክንለምናቸው - ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!!
።።።።
ወድቀው ለማይጥሉ -ነግሰው ለሚያነግሱ
ነውራችንን ዐይተው
ልክ እንደ ድመት ኩስ ፣ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው ፣ ፈጥነው ለሚረሱ
ቺርስ!!!!
።።።።።።
ላባ ላረጉልን ፣ የመከራ ሸክሙን
ቀልደው ላሳቁን ፣ ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ...
ስጋ ለበስ ትንግርት -ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!!
።።።።።።።።።።።
(By Bewketu Seyoum )
መልካም ልደት በውቄ!!!
ግጥም ብቻ
553
"✍ አለቃ ገብረ ሃና ✍
በተለይ ዐፄ ምኒልክ የአለቃን ነጻነት ያከብሩላቸው ነበር ይባላል።
ራሳቸው ዐፄ ምኒልክ በታመሙ እና በተበሳጩ ጊዜ የሕመማቸው መፈወሻ፣ የስቃያቸው ማስታገሻ፣ አለቃ ገብረሐና ነበሩ።
እንደዛም ሆኖ በአንድ ወቅት አለቃ ገብረሐና እና ዐፄ ምኒልክ ተጣልተው እስከመለያየት ደርሰው ነበር። የጥላቸው መንስኤ ግን ከዐፄ ቴዎድሮስ እና እቴጌ ጣይቱ ጋር እንደነበረው በቀልድ የተነሣ አልነበረም።
የአለቃ ገብረሐና እና የዐፄ ምኒልክ ጠብ በቀለብ(በደመወዝ) ጉዳይ የተነሣ ነበር። በጥንት ጊዜ ሹማምንት እና ሊቃውንት፣ በደመወዝ ምትክ ከመንግስት 'ይህን ያህል ጋሻ መሬት'፣ 'ይህን ያህል ዳውላ እህል' እየተባለ ነበር የሚሰጣቸው።
በዚሁ መሠረት አለቃ ገብረሐና ለዓመት ቀለባቸው የተመደበላቸው ሠላሳ ዳውላ እህል ነበር። አንድ ዳውላ በዘመኑ አለካክ የአንድ ኩንታል ያህል መጠን አለው።
አንድ ቀን የአለቃ ገብረሐና ወዳጆች ይመጡና "አለቃ እርስዎ ታላቅ ሊቅ ነዎት፣ በዛው ላይ ያለብዎት ኃላፊነት ቀላል አይደለም፤ ታዲያ ለምንድነው እነ ደጃዝማች እገሌ እነ ቀኛዝማች እገሌ ሃምሳ ሃምሳ ዳውላ ሲሰፈርላቸው፣ የእርስዎ ሠላሳ መሆኑ? ስለዚህ ይሒዱና ዐፄ ምኒልክን ይጠይቁዋቸው" አሉዋቸው።
አለቃም የወዳጆቻቸውን ምክር በመቀበል ወደ ዐፄ ምኒልክ አመሩ። እንደሔዱም "ጃንሆይ ሠላሳ ዳውላ ቀለብ ብቻ የሚሰፍሩልኝ ከእነ ደጃዝማች ከእነ ቀኛዝማች እገሌ በምን አንሼ ነው?" ይላሉ።
ዐፄ ምኒልክም "እነርሱ ሃምሳ ዳውላ እንዲሆንላቸው ያደረግኩት በሥራቸው የሚተዳደሩ በርካታ አሽከሮች እና ወታደሮች ስላልዋቸው ነው። እርስዎ ግን ብቻዎትን ነዎት፣ ምን ያደርግልዎታል?" በማለት ረጋ ብለው መለሱላቸው።
አለቃ ገብረሐና ግን ከበፊቱ የበለጠ የቁጣ እና የንዴት ስሜት አሳዩ። በዚህን ጊዜ ዐፄ ምኒልክ ተናደው "እንዲያውም ከዛሬ ጀምሮ ከሠላሳ ዳውላ ሃያ ሰባቱን አንስቼ ሦስት ዳውላ ብቻ እንዲሆን አድርጌያለሁ፣ ይኸው ይበቃዎታል" ሲሉ መለሱላቸው።
አለቃ ገብረሐና በዐፄ ምኒልክ ምላሽ አኩርፈው፣ አዲስ አበባን ጥለው ወደ ደብረ ታቦር አመሩ። ደብረ ታቦር እንደደረሱ ሰዎች "ምነው አለቃ ቤተ መንግሥትን ያህል ሥፍራ ትተው መጡ?"ቢሏቸው
"አይ የደመወዜ ሸክም ከብዶኝ ስለነበር ያንን አስቀንሼ መምጣቴ ነው።" ሲሉ መለሱላቸው ይባላል።
አለቃ ከዐፄ ምኒልክ ጋር ተጣልተው ወደ ትውልድ ሀገራቸው በተመለሱ በዓመቱ፣ በሀገሩ ሁሉ ርሓብ ገባ።
በዚህ ጊዜ አለቃ ገብረሐና ልጃቸው ተክሌን አስጠሩና "ና በአስቸኳይ አዲስ አበባ ሒድና፣ ዐፄ ምኒልክን አባቴ ስለሞቱ ለተዝካር መደገሻ የሚሆን ገንዘብ ይስጡኝ ብለህ የሚሰጡህን ይዘህ ተመለስ" ብለው፣ ራሳቸውን የሞቱ አስመስለው መልዕክት ላኩ።
ተክሌም በታዘዘው መሠረት አባቱ ያሉትን ለዐፄ ምኒልክ አስረዳ። ዐፄ ምኒልክም እውነት መስሏቸው በአለቃ መሞት በጣም አዘኑ።
በመጨረሻም ለአለቃ ገብረሐና ተዝካር ማውጫ ይሆን ዘንድ አምስት መቶ ብር ከግምጃ ቤታቸው ወጪ ሆኖ ለልጃቸው ለተክሌ እንዲሰጥ አዘዙ።
አለቃ ገብረሐናም የተላከላቸውን ጭነት ሙሉ ብር ተቀብለው ክፉውን ጊዜ በሰላም እና በጥጋብ አሳለፉ።
በኋላ ግን ዐፄ ምኒልክ በሕይወት መኖሬን ከሌላ ሰምተው ከሚቀጡኝ እኔው ሔጄ ልንገራቸው ይሉና ወደ አዲስ አበባ መጡ። ዐፄ ምኒልክ የአለቃ ገብረሐናን መምጣት በእልፍኝ አስከልካያቸው ሲሰሙ በመታለላቸው አልተቆጡም። ይልቁንም አለቃን በፈገግታ እና በፍቅር ተቀበሏቸው።
እንደተገናኙም "ለመሆኑ መሞትህ ውሸት ነበር ወይስ ከመቃብር ተነሥተህ ነው የመጣኸው?" ሲሉ በቀልድ ጠይቁዋቸው።
አለቃም "ኧረ ጃንሆይ ውሸት አይደለም፣ ማን እንደ እምዬ ምኒልክ ቤት? መንግስተ ሰማያት ስሙ ነው እንጂ፣ ምን አለ ብለው ነው? አይበላበት፣ አይጠጣበት፣ ስለዚህ የምኒልክ ቤት ይሻለኛል ብዬ መጣሁ" ብለው አሳቁዋቸው።
ከካሕሳይ ገ/እግዚአብሔር
ኅብረ-ብዕር (የብዕር ዘመራ) መጽሐፍ የተወሰደ
ምንጭ፦ቅኔ ቡክስ ቻናል🙏🙏
553
ሴማ የተፈጥሮ ይዘቱን ጠበቆ የተዘጋጀ ቡና
በፈለጉት መጠን እናቀርባለን1Kg,500Gm,250Gm
ለማዘዝ 0930773515 ይደውሉ ባሉበት ቦታ እናቀርባለን
ቀንዎን በጥሩ ቡና ይጀምሩ
ምረጫዎ ስላደረጉን እናመሰግናለን
553
°የጽጌሬዳዋ እንጉርጉሮ...
(ያንዳንድ ወጣቶች ዜማ)
____
.
ድንገት እያለፍኩኝ....
አንዲት ፅጌሬዳ
ከመንገዱ ዳር ላይ ፈክታ የበቀለች፣
ስታዜም ሰማኋት እንደዚህ እያለች.....
<<እኔ ፅጌሬዳ....
እኔ ውብ አበባ....
(ግንዴ ትኩስ እሾህ.....)
መዐዛዬ መልካም....
መልኬ እምቡጥ ፍማም....
(በቀያይ ቅጠሎች የተዥጎረጎረ፣)
ይሄን ሁሉ ፀጋ ወድጄው ነበረ፡፡
ግና ምን ያደርጋል?!
መጠውለግ "ሰሞኑን--
መጣለሁ "ይለኛል.....
(ማበቤን መፍካቴን-- በጥሪ ተርጉሞት፣)
አልገባውም እንጂ...
እኔ ፍላጎቴ....
(እንዳበብኩኝ መጥፋት )
እንደፈካሁ መሞት፡፡
አዎ!
ውበት ደስ ቢልም፣
(አይን ቢያባብልም....)
የማታ የማታ ያስፈራል እርጅና፣
እንደፈኩ መጥፋት....
እንዳማሩ መሞት ከየት ይገኝና?!
.
እናም እባክህን ...
እባክህ አንተ ሰው....
(አንተ ወጭ ወራጅ)
...........ያለህ በጎዳና፣
(ነፍሴ መጠውለግን ትፈራለችና)
እሾህ አላት ብለህ ፈርተህ አትለፈኝ፣
(አንተስ ብትደማ ነው....)
እኔ ሳልጠወልግ-- ሳላረጅ ቅጠፈኝ፡፡>>
{}
|በቃሉ ሹምዬ|
ህዳር 3-2015ዓ.ም553
#እባብ_እና_አንዳንድ_ጠቃሚ_የቤት_እንስሳት…🤣😂
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
.......................
ልጅ ሳለሁ አንድ ጓደኛ ነበረኝ - አባቱ ምትሀተኛ (Magician) ናቸው፡፡ ጥሩ ቢዝነስ አላቸው፡፡ ቢዝነሳቸው ምን መሰላችሁ - ጥቂት እባቦች አሏቸው፡፡ ቤታቸው አዘውትሬ እሄድ ስለነበር ቀስ በቀስ 97 ፐርሰንት ያህል እባቦች መርዝ እንደሌላቸው ተረዳሁ፡፡ 3 ፐርሰንቱ ብቻ ናቸው መርዝ ያላቸው፤ ከነዚህም ውስጥ አንድ ፐርሰንት የሚሆኑት ኮብራዎች ናቸው በጣም አደገኞቹ፡፡
ኮብራ ከነደፈህ መዳን ከባድ ነው፡፡ ሞት እርግጥ ነው ማለት ይቻላል፡፡ እባቦች ደግሞ በጣም ነው የሚመሳሰሉት፡፡
አባትዬው መርዝ የሌላቸው እባቦች ነበሯቸው፡፡ እናም ልጃቸውን፣ ጓደኛዬን፣ እባብ ሰው ቤት እንዲጥል ይልኩታል፡፡ እኔም አብሬው እሄዳለሁ፡፡
እኔ እና ጓደኛዬ እባቦቹን ሰዎቹ ቤት ጊቢ ውስጥ እንጥላለን፡፡ ጥቂት ቆይተው አባትዬው ለእባብ መያዣ የሚጠቀሙባቸውን የሙዚቃ መሳሪያዎቻቸውን ይዘው በዛ ሰፈር እያለፉ፣ “ቤቱ ውስጥ እባብ ገብቶ ያስቸገረው … ባለሞያዎች ነን እንይዛለን” እያሉ ይለፍፋሉ፡፡
የሙዚቃ መሳሪያዎቻቸውን መጫወት ሲጀመሩ እኛ ጊቢ ውስጥ የለቀቅናቸው እባቦች ወደ ሰውዬው መምጣት ይጀምራሉ፡፡ ለሰጡት አገልግሎትም የቤቱ ባለቤት ደስ ብሎት እያመሰገነ ይከፍላል፡፡ ይሄ ነው መተዳደሪያቸው፡፡
የቤቱ ባለቤት ገንዘቡን እየከፈለ፣ “እግዛቤር ይስጦት አባባ … እስኪ እንዲሁ እየመጡ ይያዙልን … እኛ አትክልት ቦታው ውስጥ እባብ እንዳለ መች አውቀን” ይላል፡፡
…
መርዝ የሌላቸው እባቦች የትኞቹ እንደሆኑ ስለማውቅ፣ በኪሴ እባብ ይዤ ትምህርት ቤት እሄድ ነበር፡፡ ከዛም እባቡን ክፍሉ ውስጥ አስተማሪው ጠረጴዛ ላይ ቁጭ ሳደርገው አስተማሪው ጮሆ ወንበሩ ላይ ወጥቶ፣ “አድኑኝ” ይላል፡፡ ተማሪው ሁሉ በሩጫ ከክፍሉ ይወጣል፡፡ እና ታዲያ ማን ሊያድነው ነው - ከእኔ ውጪ ?
“አድንሃለሁ … ግን ሕይወትህን እንዳዳንኩት ማስታወስ አለብህ፡፡ ሁለተኛ ታስቸግረኛለህ? ቃል ግባ !!!”
እባቡ ጠረጴዛው ላይ ሆኖ ማንኛውንም ቃል ማስገባት ይቻላል፡፡
በመጨረሻ ጉዳዩ ርዕሰ መምህሩ ጋር ደረሰ፡፡ የማይሆን የማይሆን ነገር ያደርጋል ብሎ አስማሪው ከሰሰ፡፡ ግን ርዕሰ መምህሩም ያው ነው፡፡
ወደ ቢሮው ሲጠራኝ ሁለት እባቦች በኪሴ ይዤ ሄድኩና ጠረጴዛው ላይ ቁጭ አደረግኳቸው፡፡ ዘሎ ወንበሩ ላይ ቆመ፡፡ የትምህርት ቤቱ ሰው ሁሉ እየሆነ ያለውን በመስኮት እያየ ነው፡፡
“እሺ … የምትለኝ ነገር አለ ?” አልኩት፡፡
“የለም … የለም … ይሄን ነገር ብቻ ከቢሮዬ ይዘህልኝ ውጣ” አለ ርዕሰ መምህሩ፡፡
“እኔ ራሴ ፈልጌ አይደለም የመጣሁት፡፡ አንተ ነህ የጠራኸኝ፡፡ መቼም እንደማታስቸግረኝ ቃል ካልገባህልኝ አልሄድም - እባቦቹም እዚሁ ይሆናሉ”
“እንዴ ምን አይነት ነገር ነው … በቃ ቃል እገባለሁ … አላስቸግርህም”
“እሺ … በዚህ ከተስማማን እኔም እስቲ እባቦቹን አባብዬ ይዣቸው ልሂድ፡፡ ለነገሩ እነሱም ትምህርት ቤት መምጣት አይፈልጉም፡፡ አንተ ነህ በግድ ና ብለኸኝ፡፡ ወይስ እዚሁ ይሁኑ እንዴ…” ስለው፣
“ኧረ እባክህ ይዘህልኝ ሂድ” ይጮሃል ርዕሰ መምህሩ፡፡
…
ሰዎች በመሰል ፍርሃት ውስጥ ኖረዋል፡፡ ምንጊዜም በፍርሃት እንደተከበቡ ነው፡፡ የትኛውም ነገር ፍርሃት ይፈጥርባቸዋል፡፡ ግን እኮ ሰውዬው እንደው በትንሹ እንኳ ነገሩን ቢያየው … እኔ እባቦቹን ከያዝኳቸው የሆነ ማጭበርበር አለ ማለት ነው፡፡ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ግን፣ እባብ የሚለው ቃል ብቻውን በክፍለዘመናት በሰው ልጅ ውስጥ የታመቀውን ፍርሃት ይቀሰቅስባችኋል፡፡
…
ያደረግኩትን ለአባቴ ነገሩት፡፡ “ልጅህ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጣም አደገኛ ነገሮች እያደረገ ነው” ሲሉት፤ አባቴ እንዲህ አለ፣ “ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ ቃል ገብቼለታለሁ፡፡ ልክ እናንተ ቃል እንደገባችሁለት እኔም ላላስቸግረው፣ በእሱ ጉዳይ ጣልቃ ላልገባ ቃል ገብቼለታለሁ፡፡ አለበለዚያ እነዚያኑ እባቦች ነው ቤት ይዞብኝ የሚመወጣው”
****
Source: Osho
553
=====================
ትለኛለህ ደሞ😏😏😏.....
በልኩ ተሰርቶ፤
በፍቅር ተቃኝቶ፤
ዛሬውን አጽድቆ ትናንቱን አጥፍቶ፤
ሃዘኑን ሽሮ ሳቆቹን ተክቶ፤
የትዝታ ቁስሉን ህመሙን ረስቶ፤
ካ'ንቺው ተዋህዶ ካ'ንቺው ተቆራኝቶ።
ክንዴን ተንደርሰሽ ዘላለሜን ብኖር፤
ደስታው ለኔ ነበር......
ዳግም ቀና ብዬ የልቤን ስብራት በፍቅርሽ አክሜ፤
የመውደድን ጎጆ ከአንቺው አዋቅሬ ቢሰራ አለሜ፤
ከፍቅርሽ አዝመራ ባጭድ ታድሜ።
ደስታው ለኔ ነበር.......
ክንዴን አንተርሼሽ ዘላለሜን ብኖር፤
ሆኖም ምን ያረጋል ነበር ቢደረደር፤
ምኞት ሆኖ ባይቀር......
ትናንት ያሳለፍኩት የፍቅር መንገድ፤
ዛሬን እያጠረ አስጠፋኝ መራመድ።
ውስጤ ደካከመው እንደምን ልበርታ፤
በምን አቅሜ ልቁም ካ"ዲስ ሕይወት ተርታ..............
::
::
::
ትለኛለህ ይቅር.......
የኔ ልብ በፍቅር ዝሎና ተዳክሞ፤
እንዲህም አቁስለህኝ ወድሃለሁ ደሞ።
ቁስል ያርግህ አቦ!!!
======================
✍ጦቢያ
553
...የጥንቱ ፈላስፋ ፊሮ🌿
፨፨፨
የጠርጣሪነት ፍልስፍና (scepticism) ጀማሪ እንደሆነ የሚታመንለት የጥንቱ ፈላስፋ ፊሮ አንድ ቀን ጥበብን ያካፍላቸው ዘንድ ወደጋበዙት ሰዎች በማለዳ አመራ። በቦታው ሲደርስ ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ተሰብስቦ ሲጠብቀው ተመለከተና ወደተዘጋጀለት የከፍታ ቦታ በዕርጋታ ወጥቶ ቆመ። ፊሮ ትምህርቱን ከመጀመሩ በፊት ጥያቄ ወረወረ፦
<<ዛሬ እዚህ የተሰበሰባችሁት ከእኔ ልትማሩ ነው?>> ተማሪዎቹ በአንድ ድምፅ አዎንታቸውን ገለፁ።
<<እንግዲያውስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ ማለት ነዋ?>> አለ ፊሮ።
<<ኧረ ምንም አናውቅም>> አሉ ተማሪዎቹ አሁንም በአንድ ድምፅ።
<<ስለምን እንደማስተምር ካላወቃችሁማ ዝም ብዬ ማውራት አልፈልግም>> አለና ከመድረኩ ወርዶ ወደ ቤቱ አመራ።
በነጋታው አሁንም በዚያው ቦታ ህዝቡ ተሰብስቦ ይጠብቀው ጀመር። ፊሮም መጣና በእርጋታ ወደ መድረኩ ወጣ።
<<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር አውቃችኋልና?>> በማለት ጠየቀ።
የተሰበሰበው ህዝብ በአንድ ቃል አዎንታቸውን ገለፁ።
ፊሮም <<ካወቃችሁትማ ወደ ቤቴ ልሂድ....>> በማለት ከከፍታው ላይ ወረደ።
በሚቀጥለው ቀን ወደ ቦታው ሲያመራ አሁንም ህዝቡ ተሰብስቦ እየጠበቀው ነው። የዚያን ቀን ግን ህዝቡ መልሳቸውን አዘጋጅተው ነበር የጠበቁት።
ፊሮም ወደ ከፍታው ከወጣ በኋላ፦<<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ..?>> አለ።
ህዝቡም፦<<ግማሾቻችን እናውቃለን፤ግማሾቻችን ደግሞ አናውቅም...>> አሉት።
ፊሮም፦<<እንግዲያውስ ግማሾቻችሁ የምታውቁት፤ ለግማሾቹ የማያውቁት ንገሯቸው!..>>
ምንጭ ፦ ጥበብ ከጲላጦስ
፨፨፨
፨ አሁን በእናንተ አረዳድ በፈላስፋው ላይ ነው ወይስ በተከታዮቹ ላይ ነው የሚፈረደው...?
553
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ይኸውልህ...........
ከጅማሮው መንገዳችን ሆኖ ለቅል
ከኔ ሆነህ ከኔ ህይወት ላትበቅል
ማር ቢያዘንቡህ ከንፈሮችህ.....
....ሁሉ አካሌን ብትገዛ
ብትወድም ከኔ መዋል.......
.....ቢማርክህ የአፌ ለዛ
ብንባልም ክርስቲያኖች ቢመሳሰል መጠሪያችን
አንድ አይደለም የዕምነት ልኬት መንገዳችን
ያንተ አስተምሮ.....ያንተ ድህነት-ዕምነት ብቻ
የኔ አስተምሮ-አምኖ ማድረግ...ጎዳናችን ለየብቻ
እኔ በእተ አፍ "ጌታን ከሃጂ"መጠሪያዬ
ያንተም ለኔ"ምንፍቅና"የምትባል በአስተምሮዬ
ያንተ መዳን በአለማዊ ስደድ መጣል
የኔ መሻት በመቅደሱ ተንበርክኮ ማረኝ ሲሉ ሰርክ መዋል
ለኔም ለአንተም ቢሞትልን አንድ ጌታ
ስብከታችን ለየቅል ነው ማይዛመድ በየትም ቦታ
ሆኖም ብለን....
በፍቅር ቃል ብንስማማ አንድ ጎጆ ብንቀልስ
ባንተ ሃዘን ላልደማ በኔ ህመም ላታለቅስ
ደጁ ላትደርስ ላትጠመቅ...ከኔ አምባ መቅደስ ላትቆም
ታቦት ሲያልፍ ላታጅበው...በርከክ ብለህ ላትሳለም
አንድ መሆን አይቻልም በአቅጣጫው ባጋምድም
አንተ ሆዬ.....
የሚታይህ የኔ ተግባር በአንተ ዓይን ጌታን መካድ
እኔ ደሞ ማርያም ማለት እሷን መውደድ
የኔ ኢየሱስ ማያቅ ምልጃ የአን ኢየሱስ የሚያማልድ
ማርያም ማለት ላንተ ሚከብድ እኔ ደሞ ስሟን ስወድ(...ማርያምን ስልህ...)
ምን አለፋህ....
ባጣምርህ ከኔ ምዕራፍ ወደህ ፈቅደህ ላትጋመድ
ጅምሮአችን ለየቅል ነው አንድ አይሆንም የኛ መንገድ
ከኔ አይደለም መቀመጫው ወንጌልህን ይኸው ውሰድ.....
"""""""""""""""""""""""""""""""""
✍ጦቢያ
553
አንድ ቀን ለዘላለም ዝም ትላለህ
አንድ ቀን ለዘላለም ትሄዳለህ⚰
አንድ ቀን እስከወዲያኛው ተረስተህ ትዝታ ትሆናለህ
አንድ ቀን ዳግመኛ ዕድል አይሰጥህም
#ያለህ_አሁን_ነው
የናፈቀህ ጋር ደውለህ አውራው
ያስቀየምከውን ይቅርታ ጠይቅ
#አሁን !
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
