cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

መባቻ ©

የግጥምና የስነ ፅሑፍ ገጽ ፤ በዚህ ቻናል ህልቆ መሳፍርት የጥበብ ስራዋች ይቀርባሉ፡፡ ፍቅር፤ታሪክ፤ፖለቲካ፤ ፍልስፍና፤ ማህበራዊ፤ ሽንቆጣ፤ ሙግት፤ነቆራ ወዘተ…በግጥምና በመጣጥፍ መልክ ይከተቡበታል''ኑ አብረን እያነበብን አብረን እንግጠም'' ለአስተያየት 👉 @miki1221 ይጠቀሙ፡፡ ስለተቀላቀሉን እጅጉን እናመሰግናለን፡፡መባቻ የግጥም መጽሔት፡፡

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
302
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

#ግጠምልኝ ------------------ . ሚካኤል እንዳለ . ለመልክዐ መልክሽ ፥ እጅ መንሻ ቃላት ለውዳሴ ገላ ፥ የሚሆን የቤት ምት ከፊደላት ፈትለህ ፥ ግጠምልኝ ላልሽው እንግዲያስ ያውልሽ ፥ ግጥሜን ቅመሽው - - - የጣና ዳር እንኮይ ቁመተ ለግላጋ የገነት ቄጤማ ፥ የጊዮን ዳር ሎጋ የገላሽ ንጣቱ ፥ እንደ ግምጃ አለላ ከንፈርሽ እንጆሪ ፥ የስንዴ ራስ ዛላ እያልኩኝ ጽፊያለው ግጠም ብለሽኛል ይህው ገጥሜያለው - - - እንቡጥ ጽጌሬዳ ፥ የመሰለ ጉንጭሽ ለቀመሰው ጣፋጭ ፥ እ'ዳገዳ ጥንቅሽ የግንቦት ሰማይ ነው ፥ የቆዳሽ ጥራቱ የጠረንሽ ነገር ፥ አልባስጥሮስ ሽቱ እያልኩኝ ጽፊያለው ግጠም ብለሽኛል ይህው ገጥሜያለው - - - ፀጉርሽ ጢስ አባይ የምድር መቀነት ፥ ወርዶ እማያበቃ አይንሽ ብሩህ ኮከብ የሚያስንቅ ጨረቃ ብርቱካኑ ፊትሽ ፥ ቢታኘክ ቢመጥጥ እንደ ኤደን አፍላግ ጥምን የሚቆርጥ እያልኩኝ ጽፊያለው ግጠም ብለሽኛል ይህው ገጥሜያለው - - - እናም ሳስታውስሽ በስተመጨረሻ ይሄንም ልንገርሽ እኔ ለዚህ ውበት ቃላት ስደረድር እንደ ባለ ቅኔ ፥ ፊደላት ስከምር እጅጉን አትሳቂ በደስታ ፍልቅ'ልቅ ፥ ብለሽ አቱደቂ ሞትሽን ካረሳሽ ለአፈር መግጠሜ ፥ መሆኑን እወቂ
Показать все...
'ላምላኩ ሊታረድ ፥ በአባቱ ካራ ይስሐቅ ሊሰዋ ፥ ሲወጣ ተራራ አዘቅዝቆ ቢያየው ያ እግዜር ጸፀተው ሞቱን ላለማየት ፥ በበጉ ለወጠው ይህው ዛሬ ደርሶ ሰው ከበጎች አንሶ በእግዜሩ ቦታ ፥ ተረኝነት ነግሶ ከሰው ልጆች በላይ ግዑዛን ከበሩ እንስሶች ተለቁ በግፈኞች ፍትህ በጎች ተቀምጠው ይሳቆች አለቁ . #ሚካኤል_እንዳለ @MEBACHA
Показать все...
ለጉርሻ ተናንቀህ ፥ ለቅምሻ ስትለፋ መሶቡ ተወስዶ ፥ 'ራብ እንዳይደፋህ ወትሮም ተጋፊ ሰው ብርጭቆን ይመስላል ቦታ እንደጠበበው ፥ አሥሬ ይጋጫል እንግዲ ይፈታ ፥ ትርጉሙን እወቀው ጉርሻው ዘረኝነት ፥ መሶቡም ሐገር ነው . #ሚካኤል_እንዳለ . ጉርሻ ሳይሆን መሶብ ያስረከቡህን አባቶች አስብ ፡፡
Показать все...
ማን ይብላን ? ----------- ስለጠፋ ታማኝ ተመራጭ የሰው ዘር ጌታ ውረድና ፥ ምርጫ ተወዳደር እኛም በዚው ይብቃን ትለፍ ይቺ ምድር ተብሎ ቢፈረድ ማንም አይማርም ስልጣን ያወራቸው እረስተዋልና  ፥ መሬት ማለፏንም  ብለን አስተምረን እውነትን ተናግረን 'ሚሰማ ብናጣ ፥ ነፍሳችንን ይዘን ከጅብ አፍ ለመዳን ዛፍ ብኖጣም ሸሽተን እጅጉን የጠማው ፥ ነብር ተቀበለን ስለዚህ ማን ይብላን ? ሆኖብናል ምርጫው ጅብም ቢሉ ነብር ፥ መንጋጋቸው ሥል ነው በሁለቱም ቢሆኑ ፥ ለ'ኛ ሞት አንድ ነው #ሚካኤል_እንዳለ
Показать все...
#አትማረኝ 🙏 --------------- #ሚካኤል_እንዳለ . ታመው የተነሱ እግዜርን እረሱ የሚል ተረት አለ ፥ እሱን ያስታወሰ ከዕለታት አንድ ቀን ፥ በኔ ላይ ደረሰ ፡፡፡፡ ለ'ለታት ሰባት ቀን ፥ ህመም ተሸክሜ ከቤቴ ወሳንሳ ለአንድ ሱባ'ዬ የጎን ተጋድሜ በሞትና በህይወት በመሄድ በመምጣት በሁለት አቅጣጫ ፥ ሥጋዬ ሲገፋ ከቤት ስላልወጣሁ ፥ ሃጢያት 'ካይኔ ጠፋ ፡፡፡፡ ወትሮም በደካሚ በሌለበት ቋሚ በዛ ዝለት ጊዜ ፥ ከጓዳው ተኝቶ እንደ ባህታዊ ፥ በሩን ደጁን ዘግቶ ከጊዚያዊ ታዛ ፥ ከዚህ ቅዘት ዓለም እረፍትን ፍለጋ ፥ በዐቱን ለሚያልም ገዳም እንደመግባት ለነፍስ እፎይታዋ ፥ ነው ለካ መታመም !! ፡፡፡፡ ታዲያ ምን ያደርጋል ተኝቼ አልተኛሁኝ ቀርቼ አልቀረሁኝ በሳምንቱ እራስጌ ፥ ከህመሜ ዳንኩኝ ከደጄ እንደወጣው በመንገድ ላይ ዳሌ ፥ 'ካለም ተዋወኩኝ ፡፡፡፡፡ ለዚህ ለዚህ ነበር ከቤት ውስጥ መተኛት መታመም ጥቅሙ እንደ ጥሩ መናኝ በርን አዘግቶ ይለያል 'ካለሙ እናም ተመስገን ነው በደዌ ሲመቱ ሲታመሙ ማለት ጉድጓድ እስካልገቡ እድሳት ነውና ህመም ለሰውነት ፡፡፡፡፡ እኔም ይሄን ይዤ ሥጋዬን በድካም ክፉኛ ሰቅዤ እንደ ጣናው ፃድቅ እንደ አባ አትማረኝ በሽታዬ እንዳይድን ፥ ፈጣሪን ለመንኩኝ ከዝሙት የሚያርቅ ህመም ምንኩስና መሆኑን አወቁኝ . #ሚካኤል_እንዳለ @mebacha
Показать все...
ያንተ ልጅ ሲበላ የኔ ልጅ ያለቅሳል ያንተ ቤት ተከድኖ የኔ ቤት ያፈሳል ያንተ መሬት ታርሶ የኔ ዳዋ ለብሷል ወይ ካንተ ወይ ከኔ ያንዳችን ቀን ደርሷል ጊዜ መሃንዲስ ነው ይሰራል ያፈርሳል
Показать все...
አንተን የሚያስንቁ ፥ 'ባይናችን ስላየን ለስከዛሬው ሁሉ ሰይጣን ይቅር በለን . #ሚካኤል_እንዳለ
Показать все...
የፍጥረት ውሃ ልክ --‐---------------- #ሚካኤል_እንዳለ . ከሴት ልጅ የፀዳች ፥ ዓለምን ፈጥሬ  ዠርገግ ባልኩባት ፥ ባረፍኩባት ኖሬ የምትል ቋጠሮ ቤት መምቻ እሮሮ . . . አስቤ ልገጥም ለካስ ሴት ከሌለች እናትም አትኖርም !! የሚል መደምደሚያ ከባድ ስንኝ ቢያንቀኝ ሰረዝኩት ሃሳቤን ወንድ የሆንኩበት ሴትነት ቢገባኝ . . . እናማ ካዘለች ፈትላ ካዋሃደች ከተሰጣት ዘንዳ መምሰል ጽጌሬዳ እሾህን ከጣዕም በአድ ላይ ገምዳ ካስተባበረችው ፥ በተፈጥሮ ፀጋ መቻል ግዴታ ነው ማሯን እስከላሱ ንቢት ስትዋጋ . . . በሚለው እውነታ ቁጭ አርገው ከግርጌ 'ካውድማው ጉብታ እንዲ ብለው ነበር ሲመክሩኝ 'የኔታ . . . ክፉን አሳልፈህ ለመኖር ከፈለክ ዘላለም አብረካት በፍጥረት ውሃ ልክ በ'ናትነት ይሁን ሴትን ስትለካት !!! @mebacha @mebacha
Показать все...
አፉማ የግልሽ ፥ ሰንደቋም የኔ ናት ከንፈርሽ ይቅርብኝ ፥ ሐገሬን ልሳማት (ሚካኤል እንዳለ) @ethio_art @mebacha
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.