Alétheia- Truth
👉 ለሰው ልጆች ሁሉ የተገለጠ የእግዚአብሔር እውነት “እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል።”” ዮሐንስ 8፥32
Больше258
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
- Подписчики
- Просмотры постов
- ER - коэффициент вовлеченности
Загрузка данных...
Прирост подписчиков
Загрузка данных...
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰው ይወጣሉ ሰውንም ያረክሳሉ ካላቸው ነገሮች ውስጥ ስም ማጥፋት እና ስንፍና የሚጠቀሱ ናቸው።
"ከውስጥ፣ ከሰው ልብ የሚወጡት ክፉ ሐሳብ፣ ምንዝር፣ ስርቆት፤ ሰው መግደል፣ ዝሙት፣ መስገብገብ፣ ክፋት፣ ማታለል፣ መዳራት፣ ምቀኝነት፣ ስም ማጥፋት፣ ትዕቢት፣ ስንፍና ናቸው። እነዚህ ክፉ ነገሮች ሁሉ ከሰው ይወጣሉ ሰውንም ያረክሱታል።” (ማር 7:21-23)
❤ 1
አንድ ሰባኪ እንዲህ አለ "ልጆቼ ሕፃናት በነበሩ ጊዜ በጣም ነበር የሚያስቁኝ፤ ምክንያቱም ስጦታ ስንሰጣቸው ለስጦታው ቦታ ሳይሰጡት ስጦታው የተጠቀለለበትን ካርቶን በማግኘታቸው እጀክ በጣም ይደሰቱ ነበር። ስጦታውን ከካርቶኑ ውስጥ በማውጣት ካርቶኑን በራሳቸው ላይ አስቀምጠው "ካርቶኑን እወደዋለሁ" እያሉ በደስታ ይጨፍራሉ። በእውነት ሕፃናት ለመጠቅለያው እንጂ እኛ ለተጨነቅንበት ለስጦታው ግድ የላቸውም።ይህ እጀክ በጣም አስቂኝ ነገር ነው።"
ከስጦታው በላይ ስጦታህ ድንቅ ነው
አንድያ ልጀህን መስዋዕት አረከው
ታዲያ ለዚህ ጌታ ምን ይከፍለዋል
ተመስገንም ብለው በጣም ሲያንስብህ ነዉ
❤ 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
“አባት ለልጆቹ እንደሚራራ፣ እግዚአብሔር ለሚፈሩት እንዲሁ ይራራል።” መዝ 103፥13
❤ 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
ፀጋ ስለመልካም ስራችን የሚሰጥ ዋጋ አይደለም
“በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ቤዛነት እንዲያው በጸጋው ጸድቀዋል፤” ሮሜ 3፥24
👍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በምንድነው የምታምኑ ለሚሉን። የእምነታችን መሰረቶች እነዚህ 👆ናቸው። በክርስቶስ አዳኝነት ብቻ፣ በእርሱ ጸጋ ብቻ፣ በእርሱ በማመን ብቻ በሚገኝ ድነት ብቻ፣ ክብር በሚገባው በእግዚአብሔር ብቻ፣ በመጸሐፍ ቅዱስ ብቻ እናምናለን
ብዙውን ጊዜ ጥያቄዎች የሚነሱት “በኢየሱስ አምላክነት” ላይ ቢሆንም እንኳን ከዚያ ባልተናነሰ መልኩ “በኢየሱስ ሰውነትም” ላይ የተሳሳቱ አመለካከቶች ይንጸባረቃሉ። ከእነዚህ ውስጥ ጥቂቶቹ፦
ኢየሱስ ሰው ነው ነገር ግን ሙሉ በሙሉ (እንደ እኛ) ሰው ግን አይደለም
ኢየሱስ ስጋን እንደ ልብስ ለበሰው እንጂ እርሱ አምላክ ነው
ኢየሱስ ሰው ነው ነገር ግን ከእኛ ከፍ ያለ፤ የተለየ ”ሱፐር ማን” ነው!
ኢየሱስ የተወሰነ የሰው ባህሪ፤ የተወሰነ ደግሞ የአምላክ ባህሪ የተላበሰ ነው
ሰው ነው ነገር ግን እንደ እኛ ዓይነት አእምሮ፣ ፍቃድ እና ስሜት ግን አልነበረውም
እነዚህ ከላይ የጠቀስናቸው አመለካከቶች በሙሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች ናቸው። ኢየሱስ ይሄንን ጹሑፍ የምታነበውን ሰው አንተን! አዎ አንተን! ነው የሆነው። ከዳዊት የዘር ሐረግ ከቅድስት ድንግል ማሪያም ተወለደ፣ ሁሉን አውቆ አልተወለደም ነገር ግን አንደማንኛውም ሕጻን ልጅ በእውቅት፣ በቁመት፣ በሞገስ አደገ፣ ቤተሰቡን እያገለገለ አደገ። እርሱ ፍጹም አምላክ መሆኑን እንደምናምን ሁሉ ሳንጨምርና ሳንቀንስ ሰው መሆኑንም መቀበል ይገባናል።
ልክ እንደ እኛ በፈተናዎች ሁሉ የተፈተነ፤ በሐዘን በደስታ፣ በማጣት በማግኘት፣ በሰዎች አጀብና በብቸኝነት፣ በመጠላት በመገፋት፣በመወደድ እና በመጠላት፣ በሞትና በትንሳኤም አልፎዋል...እኛ ያለፍንበትንና የምናልፍበት ሁሉ ተፈትኖ ያለፈ ነገር ግን በፈተና ሳይወድቅ ያለፈ ነው እርሱ። “...እንደ እኛ በማንኛውም ነገር የተፈተነ ሊቀ ካህናት አለን፤ ይሁን እንጂ ምንም ኀጢአት አልሠራም።” ዕብ 4፡15
አዝነንም ይሁን አክብረን፤ ኢየሱስን ከሰው በጥቂቱም ይሁን በብዙ “ልዩ ሰው” ማድረግ የአጋንንት ትምህርት ነው! መጸሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል
“ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ወጥተዋል። እንዲህ ያለ ማንኛውም ሰው አታላይና የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።” 2ዩሐ 1፡7
“ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚቀበል መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤።” 1ዩሐ 4፡2
Выберите другой тариф
Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.