Grace Commission
Открыть в Telegram
2 536
Подписчики
-324 часа
-67 дней
-530 день
Архив постов
2 536
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የክርስትና ታሪክና የተለያየ ሃይማኖታዊ ዳራ ያለባት አገር እንደመሆኗ፣ ወንጌልን የማብሰር ሂደት እንደ አሜሪካ ወይም አውሮፓ ካሉ “ድህረ-ክርስትና” (Post-Christian) ማኅበረሰቦች የተለየ ጥበብን ይጠይቃል፡፡ ወንጌል ተረድተው ላልታዘዙት ብቻ ሳይሆን “ለዳኑትም” ወንጌል ያስፈልጋል የሚለውን የጸሐፊውን ሞጋች ሐሳብ ይበልጥ ለማጠናከር፣ ከኦርቶዶክሳዊ፣ ከእስልምና ወይም ከባህላዊ እምነቶች ለሚመጡ ሰዎች ወንጌልን በምን ዓይነት ቋንቋና አቀራረብ ማድረስ እንደሚቻል (Contextualization) በሰፊው መተንተን ይገባው ነበር፡፡ ይህ የዐውድ ክፍተት መኖሩ መጽሐፉን ዝቅ የሚያደርገው ባይሆንም፣ ለቀጣይ እትሞች ወይም ለሌሎች ጸሐፊዎች እንደ ትልቅ የቤት ሥራ የሚወሰድ ነው፡፡ ስልቶቹን ከኢትዮጵያ ወግና ልማድ ጋር አሳልጦ ማቅረብ፣ ወንጌል በአገራችን ምድር ስር እንዲሰድና የባህል ወረራ ሳይሆን የሕይወት ለውጥ ሆኖ እንዲታይ ያደርገዋል፡፡
* የአስተንትኖ ክፍተት፦ የመጽሐፉ ጸሓፊ የዐሳቡን ተፈላጊነት፣ ጠቃሚነትና ምክንያት አጉልቶ ለማውጣት የተጠቀማቸው ተዛማጅ መረጃዎች ተጨባጭ (ኦብጄክቲቭ) በሆነ መንገድ ለማጣቀስ ሞክሯል፡፡ ነገር ግን ለቀረቡት ተዛማጅ መረጃዎች ልከኛ ወይም ተመጣጣኝ ማስተንተኛዎች ከዚህ በላይ ማድረግ ይችል ነበር፡፡ ጸሐፊው ሐሳቡን ለማጠናከር እጅግ በርካታና ተጨባጭ የሆኑ መረጃዎችን፣ ጥቅሶችንና የታዋቂ ሰዎችንን ንግግሮች ተጠቅሟል፡፡ መረጃዎችን በማከማቸትና በማጣቀስ ረገድ የተሳካ ሥራ ቢሠራም፣ እነዚያን መረጃዎች ከመጽሐፉ ማዕከላዊ ሐሳብ ጋር የማሰናሰልና የማብራራት (Reflective Analysis) አልተመጣጠነም፤ የጸሐፊው የራሱ ድምፅና ትንተና በእነዚህ ጥቅሶች ጥላ ስር ተጋርዶ ይታያል፡፡
* መጽሐፉ በየክፍሉ ማጠቃለያ ጥያቄዎች ቢካተቱበት አንባቢዎችን ይበልጥ አሳታፊ እና እንደ ማጥኛ መመሪያ የመሆን ዕድሉን ይበልጥ ያሰፋው ነበር፡፡ መጽሐፉ ይዘቱ ግልጽና መረጃዎቹ ስልታዊ ቢሆኑም፣ በየምዕራፉ ማጠቃለያ ላይ የአንባቢን ግንዛቤ የሚፈትሹ ወይም ለቡድን ውይይት የሚጋብዙ “የማጠቃለያ ጥያቄዎች” አለመካተታቸው አንዱ የታየ ክፍተት ነው፡፡ ይህ ነጥብ መጽሐፉ ሊኖረው የሚችለውን ሰፊ ተፅዕኖ ገድቦታል ብዬ አምናለሁ፡፡
ባጠቃላይ፣ “ወንጌል ይዘቱና አቀራረቡ” መጽሐፍ ሊያሳካው ከነደፈው ዓላማ አንጻር ሲመዘን፣ ግቡን የመታ ስኬታማ ሥራ ነው፡፡ መጽሐፉ ሊያስተላልፍ የፈለገውን መልእክት በዝርዝር የሚተነትኑ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ ከአወቃቀሩ ስሙርነት ባሻገር መረጃዎችን የሚያቀርብበት መንገድ እጅግ ማራኪ ነው፡፡ ከሌሎች ተመሳሳይ ጭብጥ ካላቸው መጻሕፍት በተለየ መልኩ፣ የመልእክቱ አለመወሳሰብ እና የቋንቋው ግልጽነት ለማንኛውም የአንባቢያን ደረጃ (አማኞችም ሆነ ገና ወንጌልን የሚሰሙ ሰዎች) ምቹ ያደርገዋል፡፡ ጸሐፊው፣ ወንጌልን ከመረዳት አልፎ እንዴት መመስከር እንደሚቻል ያስቀመጣቸው ተግባራዊ መመሪያዎች መጽሐፉን ልዩ ያደርጉታል፡፡
ይህ መጽሐፍ በቤተ ክርስቲያን መደርደሪያዎች ላይ ብቻ ተቀምጦ እንዲቀር ሳይሆን፣ እያንዳንዱ አማኝ አንብቦትና ተረድቶት በሕይወቱ እንዲለማመደው እመክራለሁ፡፡ መጽሐፉ የያዘው እውነት ለብዙዎች እንዲደርስና በወንጌል አገልግሎታቸው ላይ አዲስ መነሳሳትን እንዲፈጥርላቸው መመኘቴን እገልጻለሁ፡፡ በመሆኑም፣ ወንጌልን በትክክል ለመረዳት፣ ለመኖርና ለመመስከር ለምትፈልጉ ሁሉ ይህንን መጽሐፍ በታላቅ ዐክብሮት እጋብዛለሁ፡፡
ዳሠሣ አቅራቢው፦ ዓለማየሁ አየለ
2 536
የመጽሐፉ ርእስ፦ ወንጌል ይዘቱና አቀራረቡ
ጸሓፊ፦ በርናባስ ዘመነ
ዐታሚ፦ ርኆቦት አታሚዎች
ዘውግ፦ ስልታዊና ተግባራዊ ሥነ መለኮት
የታተመበት ዓ.ም፦ 2017 ዓ.ም
የገጽ ብዛት፦ vii+78
#የመጽሐፉ #ጭብጥ
የመጽሐፉ ዋና ጭብጥ፣ “የወንጌልን ትክክለኛ ምንነት መረዳትና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለሌሎች ማድረስ” የሚል ነው፡፡ መጽሐፉ፣ ወንጌል ዝም ብሎ የሚነገር ወሬ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይዘት ያለው፣ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል የሚከናወንና የሰውን ልጅ ሕይወት ከውድቀት ወደ ክብር የሚመልስ መለኮታዊ መልእክት መሆኑን ያብራራል፡፡ መጽሐፉ ለአማኞችም ይኹን ላላመኑ ሰዎች፣ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ለማዳን እና ወደ መንግሥቱ ለማምጣት ስለላከው ልጁ እና በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ስላደረገው የሚናገረውን ምሥራቹን ቃል ወይም ወንጌልን ይተነትናል፡፡ ወንጌል ምንድነው፣ ባለቤቱ ማነው፣ ስለ ማን ነው፣ ምን አይደለም? የሚሉትን በማንሳት ጪምር ያብራራል፡፡ መጽሐፉ ወንጌልን ከመተርገም ባለፈ፣ እንዴት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማብሰር እንደሚቻል መጽሐፍ ቅዱሳዊና ስልታዊ መመሪያዎችን ያስቀምጣል፡፡ በተጨማሪም፣ ለተብራራው ወንጌል የሰው ምላሽ ምን መሆን አለበት የሚለውን የወንጌል መመሪያዎች (ዐምስቱ “መ” ዎች) በሚለው ክፍል በሰፊው ያትታል፡፡
#የመጽሐፉ #አወቃቀርና #ይዘት
መጽሐፉ፣ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎችና በንዑሳን ክፍሎች የተዋቀረ ነው፡፡
ክፍል አንድ፦ ስለ ወንጌል ምንነት እና ባለቤት ይናገራል፡፡ ወንጌል ምንድነው? እና የማነው? ለሚሉ ጥያቄዎች ግልጽ መልስ ያቀርባል፡፡ ጸሐፊው በመጽሐፉ መጀመሪያ ላይ ትኩረት የሚሰጠው “ወንጌል” የሚለውን ቃል ካለው ልማዳዊ አጠቃቀም አስቀድሞ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይዘቱን ለማሳየት ይሞክራል፡፡ ወንጌል ምንድን ነው? ወንጌል የሚለው ቃል “ኤዋንጌሊዮን” (Euaggelion) ከሚለው የግሪክ ቃል የመነጨ ሲሆን ትርጉሙም “ደስ የሚያሰኝ ዜና ወይም የምሥራች” ማለት እንደሆነ ጸሐፊው ያብራራል፡፡ ሆኖም ይህ ዜና ከማንኛውም ዓለማዊ ብሥራት የሚለይባቸውን ነጥቦች እንዲህ ያስቀምጣል፡፡ ከመረጃ በላይ ነው፤ ወንጌል ተራ የቃላት ውቅር ወይም የመረጃ ስብስብ ሳይሆን፣ የሰውን ሕይወት የመለወጥ አቅም ያለው “መለኮታዊ ኃይል” ነው፡፡ የማዳን ኃይል ነው፤ በሮሜ 1፥16 ላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ በመጥቀስ፣ ወንጌል በኃጢአት ምክንያት የፈረሰውን የሰው ሕይወት የሚጠግንና መንፈሳዊ ሙሉነትን የሚመልስ ኃይል መሆኑን ስቲቭ ስትራውስን እና ቶማስ ሀሌን ዋቢ በማድረግ ያሳያል፡፡
በመቀጠልም የወንጌል ባለቤት ማነው? ለሚለው ጥያቄ መጽሐፉ ወንጌል የሰዎች ፈጠራ ወይም በጎ ምኞት አለመሆኑን በጥብቅ ይሞግታል፡፡ ምንጩ እግዚአብሔር ነው፤ ወንጌል “የእግዚአብሔር ወንጌል” ተብሎ የሚጠራው ባለቤቱ እግዚአብሔር ስለሆነ ነው፡፡ ጸሐፊው ዶ/ር በድሉ ይርጋን በመጥቀስ፣ ወንጌል ከሰው ያልተጀመረና በሰው ችሎታ ያልመጣ፣ ይልቁንም እግዚአብሔር ያዘጋጀው መሆኑን ያስረዳል፡፡ ማዕከሉ ኢየሱስ ነው፤ ወንጌሉ ስለ እግዚአብሔር ልጅ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት፣ አገልግሎት፣ ሞትና ትንሣኤ የሚናገር በመሆኑ “የልጁ ወንጌል” ተብሎ እንደሚጠራም በስፋት ይተነትናል፡፡
ክፍል ሁለት፦ የወንጌል ይዘት ላይ ያተኩራል፡፡ በዚህ ክፍል ጸሐፊው ወንጌልን ከሌሎች የሰው ልጅ አስተሳሰቦች ጋር በማነጻጸር ትክክለኛውን መልክ ያስይዛል፡፡ ወንጌል ስለ ማን ነው? የሚለውን በማንሳት ጸሐፊው ወንጌል ስለ አንድ አካል የሚነገር ምሥራች መሆኑን አጥብቆ ያሳያል፡፡ ወንጌል ስለ መርሆዎች ወይም ስለ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ሳይሆን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይህም የኢየሱስ ማንነት (ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለተወለደው፣ በትንሣኤው ደግሞ የእግዚአብሔር ልጅነቱ በኃይል ስለተገለጠው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገር መልእክት ነው (ሮሜ 1፥3-4)፣ የኢየሱስ ሥራ (ወንጌል የክርስቶስን ሕይወት፣ ቤዛዊ ሞት እና ትንሣኤ ማዕከል ያደርጋል፡፡ ጸሐፊው እንደሚያብራራው፣ ወንጌል “ስለ ልጁ” የሚነገር ዜና በመሆኑ፣ ክርስቶስ የሌለበት ስብከት ወንጌል ሊባል አይችልም) እንዲሁም ወንጌሉ ፍሬ እንዳለው( ወንጌል ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያደረገውን የማዳን ሥራ የሚያበስር በመሆኑ፣ የሰው ልጅ በእርሱ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቅበት ብቸኛው መንገድ ነው) ያትታል፡፡
በመቀጠልም ወንጌል ስለማን መሆኑን ከነገረን በኋላ ምን አይደለም? የሚለውንም በማንሳት ንጽጽራዊ ትንተና ያደርጋል፡፡ ሰዎች ወንጌልን በስሕተት ከሚረዱባቸው መንገዶች አንጻር ጸሐፊው የሚከተሉትን ነጥቦች ያነሳል፡፡ የሰው ፍልስፍና አይደለም፤ ዶ/ር አስቻለው አበበን በመጥቀስ፣ ወንጌል በሰው ጥበብ የተዋቀረ ፍልስፍና አለመሆኑን ያሳያል፡፡ የሕግ ዝርዝር አይደለም፤ ወንጌል “ይህንን አድርግ፣ ያንን አታድርግ” የሚል የሥርዓት ሸክም ሳይሆን፣ በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተመሠረተ የጸጋ ስጦታ ነው፡፡ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ መሆኑን (ሮሜ 10፥4) በማንሳት ሰውን ነጻ የሚያወጣ ምሥራች መሆኑን ያብራራል፡፡ ታምራትና ድንቅ አይደለም፤ ታምራት ወንጌልን የሚያጸኑ ምልክቶች እንጂ ወንጌሉ ራሱ አለመሆናቸውን በማሳሰብ፣ ትኩረታችን ከመልእክቱ እንዳይሰረቅ ያስጠነቅቃል፡፡ የብልጽግና ወሬ አይደለም፤ ወንጌል በዋናነት ስለ ነፍስ መዳንና ስለ ዘላለም ሕይወት እንጂ ስለ ምድራዊና ቁሳዊ ስኬት ብቻ የሚሰብክ የብልጽግና ወሬ አለመሆኑን ይተነትናል፡፡
ጸሐፊው ወንጌልን በጽንሰ-ሐሳብ ደረጃ ምን እንደሆነ ካብራራ በኋላ፣ ይህ “ምሥራች” በአራቱ ወንጌላውያን ዘንድ እንዴት እንደቀረበ በዝርዝር ያሳያል፡፡ ማቴዎስ፣ ክርስቶስን እንደ “ንጉሥና መሲህ” ያቀርበዋል፡፡ ትኩረቱም ለአይሁድ ማኅበረ ሰብ በመሆኑ፣ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን የተነገረለት መሲህ መሆኑን ያጎላል፡፡ ማርቆስ፣ ክርስቶስን እንደ “ታዛዥ አገልጋይ ወይም ሥቅዩ ሎሌ” ይስለዋል፡፡ መልእክቱ ለሮማውያን እንደመሆኑ፣ በንግግር ላይ ሳይሆን በክርስቶስ ተግባራዊ ተልእኮና ታምራት ላይ ያተኩራል፡፡ ሉቃስ፣ ክርስቶስን እንደ “ፍጹም ሰው” ይገልጸዋል፡፡ ለግሪካውያንና ለአሕዛብ እንደመጻፉ፣ የክርስቶስን ርኅራኄና ለሰው ልጆች ሁሉ ያለውን አዳኝነት ያሳያል፡፡ ዮሐንስ፦ ክርስቶስን እንደ “እግዚአብሔር ልጅ” (አምላክ) ያሳያል፡፡ ይህ ወንጌል ከሦስቱ (ሲኖፕቲክ) ወንጌላት ለየት ባለ መልኩ የክርስቶስን መለኮታዊነትና የቃልን ሥጋ መሆን ያበስራል፡፡
የጽሐፊው ይህ ገለጻ ወንጌልን በአንድ ወገን ብቻ ከመመልከት ይልቅ፣ አራቱ ወንጌላውያን ክርስቶስን ያዩበትን የተለያዩ አቅጣጫዎች በማምጣት፣ ወንጌል ለሁሉም የሰው ልጅ ክፍሎች (ለአይሁድ፣ ለሮማውያን፣ ለግሪካውያንና ለዓለም ሁሉ) የሚስማማ መሆኑን አብራርቷል፡፡ መጽሐፉ ስለ ወንጌል ሲያስተምር የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪካዊና ሥነ-ጽሑፋዊ ቅንጅት ሳይዘነጋ፣ የሲኖፕቲክ ወንጌላትንና የዮሐንስ ወንጌልን አንድነትና ልዩነት (Unity and Diversity) በማሳየቱ ለአንባቢያን ግንዛቤን ይሰጣል፡፡
2 536
''ዓሣ እኮ በተፈጥሮው ወደ ጀልባ ዘልሎ አይገባም'' ሪክ ዋረን
"መረብ ይዞ ወደ ዓሣዎቹ መሄድ የግድ ልናደርገው የሚገባን ሥራ ነው።" ማሙሻ ፈንታ (ዶ/ር)፣ መንፈሳዊ ብስለት ገጽ 81
2 536
መስቀል፣ በጎልጎታ ኮረብታ ላይ ከመተከሉ በፊት በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ ተተክሎ ነበረ። መስቀሉ ከጎልጎታ ኮረብታ ቢነቀልም፣ በእግዚአብሔር ልብ ላይ ያለው መስቀል ግን እስካሁንም አለ። _ ጳውሎስ ፈቃዱ፣ የተሰቀለው፣ ገጽ 52
2 536
"ነገረ መለኮታዊ ጭቅጭቆችና ውዝግቦች ለጥንቁቅ ክርስቲያናዊ መንፈስ የሚያስጠሉ ናቸው። እንዲህ ያለውን ነገር ደስ ልንሰኝበት ብንሞክር፥ ወዮልን!" _ ጆን ስቶት
ትርጉም፦ የአምላክ-ቸርነት በዛብህ
2 536
በዚህ የመላእክት ምስክርነት ውስጥ ሦስት ነገር እናስተውላለን፡፡ በዚህ ምስክርነት ውስጥ በመጀመሪያ የምናስተውለው የተወለደው መድኀኒት ነው የሚለውን ነው፡፡ የዕብራውያን ጽሐፊ “ኀጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ” እንዲል የተወለደው ከኀጢአት የሚያጥብ ነው፡፡
ኹለተኛው በምስክርነቱ ውስጥ የምናስተውለው ቁም ነገር የተወለደው ክርስቶስ ነው የሚለውን ነው፡፡ ክርስቶስ የሚለዉ የግሪክ ቃል ሲሆን “የተቀባ” ማለት ነዉ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም የተቀባ መኾኑን ሐዋርያት ሥራ 10÷38 እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅደስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበረና፤” በማለት ኢየሱስ የተቀባ አገልጋይ መኾኑን ይገልጻል፡፡ ኢየሱስን ክርስቶስ ነው ብሎ ማመን አንድ የእምነታችን መሠረት ነውና (1ዮሐ. 5÷1)፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የዚህ ምስክርነት መልእክት፣ የተወለደው ጌታ ነው የሚል ይኾናል፡፡ ኩሪዮስ (kurios koo’-ree-os) የሚለው የግሪክ ቃል ሲኾን ገዥ፣ አለቃ፣ የበላይ ማለት ሲኾን አዶን ወይም አዶናይ እንዲኹም ኤሎሂይም ከሚለው የእግዚአብሔር ስም ጋራ አቻ ትርጉም አለው፡፡
የሰማይ ደስታ እና የምድር ሰላም (ቁ. 13–14): የእግዚአብሔር ተልእኮ ማስታረቅ ነው
በድንገት፣ ሰማዩ እግዚአብሔርን በሚያመሰግኑ መላእክት ተሞላ፡፡ ሰማይ ዝም ብሎ መቆየት አልቻለም፡፡ የሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከተገለጠው መልአክ ጋር በአንድነት “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”፡፡ የመላእክት መዝሙር “ሰላምም በምድር” ስሜታዊ ግጥም አይደለም፤ የእግዚአብሔርን የማስታረቅ ተልእኮ መግለጫ ነው፡፡ ሰላም (ሻሎም) ማለት ሙሉነት፣ መልሶ ማቋቋም እና ከእግዚአብሔር እና ከሌሎች ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ከአሁን በኋላ ሩቅ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ከአኛ ጋር ሁኗል(አማኑኤል)፣ ዓለምን ቀውስ ውስጥ የከተተው ኀጢአት መድኀኒቱ መጥቷል፡፡ ተስፋ ወደ ጨለማው ዓለም ውስጥ ገብቷል፡፡ እግዚአብሔር ያደረገውን ስንረዳ ዝም ማለት አንችልም፡፡
የተገለጠላቸው ለእግዚአብሔር የሰጡትን “ምላሽ”(ቁ. 15-17)
“እንሂድ” (ቁ. 15-16): መገናኘት ወደ እንቅስቃሴ ይመራል
ቤተ ክርስቲያን ተልእኮን አትፈጥርም፤ በእግዚአብሔር ተልእኮ ውስጥ ትሳተፋለች፡፡ አብ ወልድን እንደላከው ሁሉ፣ ወልድም ቤተ ክርስቲያንን ይልካል (ዮሐ. 20፥21)፡፡ የኢየሱስ ልደት የቤተ ክርስቲያን ሕይወትና ምስክርነት ምሳሌ ይሆናል፡፡ እረኞች የመጀመሪያዎቹ ሚስዮናውያን ናቸው፡፡ ክርስቶስን ካገኙ በኋላ ስለ ሕጻኑ የተወራላቸውን ገልጠው አወሩ (ሉቃስ 2፥17) አ.መ.ት፡፡
ልክ እንደ እረኞቹ፣ ልጁን በእውነት የምታይ ቤተ ክርስቲያን ዝም አትልም፡፡ እረኞች አልተከራከሩም፡፡ አልዘገዩም፡፡ “ወደ ቤተልሔም እንሂድ” አሉ(አ.መ.ት)፡፡ ተልእኮ ሁልጊዜ የሚጀምረው ለመሄድ በመወሰን ነው፡፡ ይህንን ልብ እንበል፣ እረኞቹ በጎቻቸውን ትተው ነበር፡፡ ያ አደገኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ክርስቶስን መገናኘት ሁልጊዜ የምንተወውን ነገር በእግዚአብሔር እንድንታመን ይጠይቀናል፡፡ ዛሬም፣ ተልእኮ እንቅስቃሴ ይጠይቃል፡፡ ከምቾት ወደ ታዛዥነት፣ ከፍርሃት ወደ እምነት፣ ከማወቅ ወደ መሄድ፡፡
“አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።”(ቁ. 17): ካዩም በኋላ ስለ ሕፃኑ የተነገራቸውን ግለጠው አወሩ(አ.መ.ት)
እረኞቹ ኢየሱስን ካዩ በኋላ በሴሚናር ላይ አልተገኙም፡፡ መደበኛ ስልጠና አልወሰዱም፡፡ እረጆቹ ያዩትንና የሰሙትን ብቻ ተናገሩ፡፡ ተልእኮ ሁሉንም መልሶች ስለማግኘት አይደለም፡፡ ክርስቶስ ለእኛ ያደረገውን ስለማካፈል ነው፡፡ እረኞቹ ምስራቹን ሰምተዋል፣ የሰማይን መላእክት ዝማሬ ሰምተዋል፣ የጌታን ክብር አይተዋል፣ ወደ ቤተልሔም ሄደውም ሕፃኑን ተመልክተዋል፡፡ ነገር ግን ታሪኩ እዚያ ላይ አላበቃም። ሉቃስ 2፥17 እረኞቹ “አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።” ይለናል፡፡
ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለን ትልቁ ችግር "አይተን ዝም ማለታችን" ነው፡፡ ብርሃኑን አይተናል ግን ጨለማ ውስጥ ላሉት አልበራንም፤ መድኀኒቱን አግኝተናል ግን ለታመመው ዓለም አልሰጠንም፡፡ እረኞቹ ግን የታያቸውንና የተነገራቸውን ነገር ምስክር ሳይሆኑ ሊቀሩ አልቻሉም፡፡ እረኞቹ መልእክቱን በሰሙ ጊዜ "እስቲ እንሂድና እንይ" አሉ። ምሥራቹን ለማብሰር መጀመሪያ ወደ ክርስቶስ መቅረብና እርሱን ማየት ያስፈልጋል፡፡
ለአሁኗ ቤተ ክርስቲያን፦ ተልእኮ የሚጀምረው በምቾት ወንበር ላይ ተቀምጦ ፕሮግራም በማድነቅ አይደለም፡፡ ተልእኮ የሚጀምረው የክርስቶስን ፍቅር ቀምሶ፣ ያንን ፍቅር ለሌላው ለማካፈል ካለ ጉልበት ነው፡፡ ዓለም በኀጢአትና በጭንቀት እየተቃጠለች ባለችበት በዚህ ዘመን፣ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢዋ ውስጥ ብቻ መሸሸግ የለባትም፡፡ እረኞቹ መንጋቸውን(ጊዜያዊ ማደሪያ በረት) ጥለው እንደወጡ፣ እኛም ከሃይማኖታዊ ልማዳችን ወጥተን ወደ ሰው ልብ መጓዝ አለብን።
እረኞቹ የተናገሩት የራሳቸውን ፍልስፍና ሳይሆን ስለ ሕፃኑ የተነገረላቸውን ነው፡፡ ዛሬ ዓለም የሚያስፈልጋት የሰውን ንግግር ሳይሆን ስለ ክርስቶስ የሚነገር ምስክርነትን ነው። የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ (የእኛ ተልእኮ) የክርስቶስን ማንነትና ሥራ ለሰዎች ማሳወቅ ነው፡፡ ሰዎችን ወደ ሃይማኖት ሳይሆን ወደ ሕያው ጌታ ማገናኘት ነው፡፡ አንድ የታመመ ሰው መድኀኒት አግኝቶ ከዳ በኋላ፣ መድኀኒቱን ለሌሎች ታማሚዎች ሳይናገር ዝም ቢል ይህ ጭካኔ ነው። እኛም የዘላለም ሕይወት አግኝተን ለሚጠፋው ዓለም ዝም ካልን ትልቅ ዕዳ አለብን፡፡ ዝምታችን የብዙዎችን ሕይወት ሊያስከፍል ይችላል!
እነዚያ እረኞች በዚያች ሌሊት የቤተልሔም አውራ ጎዳናዎችን በደስታ ጩኸት ሞሉት! "አገኘነው! መድኃኒቱ መጥቷል! ሰላሙን አየነው!" እያሉ ሲጮኹ፣ ዓለም በመደነቅ ተሞላች(ቁ.18)፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋት ይህንን ነው፡፡ ያየችውንና የቀመሰችውን እውነት ለሚጠፋው ዓለም በኀይል የምታውጅ ምስክር መሆን፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ዛሬም ጌታ እንዲህ ይላታል፡- ባየሽው ብርሃን ጨለማውን ውጊ፤ በሰማሽው ቃል የተጠሙትን አርኪ፤ በጨበጥሽው እውነት የታሰሩትን ፍቺ፡፡
ማጠቃለያ፡
ግርግሙ ከእግዚአብሔር ወደ ቤተ ክርስቲያን የቀረበ ግብዣ ነው፡፡ ወደ ዝቅተኛ ቦታዎች መሄድ፣ ለተራ ሰዎች መናገር፡፡ እረኞቹ ሕፃኑን ሲያዩ ዝም ማለት አልቻሉም፡፡ ያዩትንና የተነገራቸውን ነገር ወዲያውኑ ማውራት (መመስከር) ጀመሩ፡፡ ማየት ወደ ማውራት ይመራል፡፡ ክርስቶስን በትክክል ያየ ሰው ዝም ሊል አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር መገለጥ ዛሬም በቃሉ በኩል ለእኛ ደርሷል፡፡ ጥያቄው ግን፦ የእኛ ምላሽ ምንድነው? እንደ እረኞቹ ሮጠን ወደ እርሱ እንቀርባለን? ወይስ ሰምተን እንዳላየን እናልፋለን? በግርግም የጀመረው የእግዚአብሔር ተልእኮ እያንዳንዱ ነገድ፣ ቋንቋ እና ሕዝብ ምሥራቹን እስኪሰማ ድረስ በታክ ውስጥ ቀጥሏል፤ አኹንም በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ይቀጥላል፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፡፡
(ዓለማየሁ አየለ፣ ታህሳስ፣ 2018 ዓ.ም)
የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን!
2 536
ምሥራቹ እና ለምስራቹ የተሰጠው ምላሽ
(ሉቃስ 2፥7-17)
በክርስቶስ የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች፣ እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ፡፡
በሕይወታችን ብዙ ምሥራች ሰምተናል፡፡ የሥራ ዕድል ማግኘት፣ የታመመ መፈወስ፣ ጦርነት አብቅቶ ሰላም መውረድ፣ ወይንም የሕፃን ልጅ መወለድ... ወዘተ. እነዚህ ኹሉ ያስደስታሉ፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ምሥራቾች ሁሉ "ውስንነት" አለባቸው፡፡ የሰው ምሥራች አድሎአዊ ነው፤ የአንዱ ድል የሌላው ሽንፈት ነው፡፡ የሰው ምሥራች ጊዜያዊ ነው፤ የዛሬው ደስታ በነገው ጭንቀት ይዋጣል፡፡ የሰው ምሥራች ውድ ነው፤ ለማግኘት ድካምና መከፈል ያለበት ዋጋ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ጽሑፍ ከሰው ምሥራች ሁሉ የሚበልጥ፣ ሰማይ ለምድር የላከውን፣ ታሪክን ለሁለት የከፈለውንና የሰው ልጅን ዕጣ ፈንታ የለወጠውን ታላቅ ምሥራች እናያለን፡፡ እርሱም የኢየሱስ መወለድ ነው፡፡ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ብዙ ድንቅ ክስተቶች ተከስተዋል፡፡ ነገር ግን የሰማይ ጌታ ሥጋ ለብሶ(ሰው ኹኖ) ወደ ምድር የመጣበትን ያህል ታላቅ ዜና የለም። በምንመለከተው በዚህ ክፍል ውስጥ ኹለት ትልልቅ እውነታዎች ላይ እናተኩታለን፡፡ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያደረገው “መገለጥ” እና የተገለጠላቸው ለእግዚአብሔር የሰጡትን “ምላሽ” ነው፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በየዓመቱ የሚታወስ ታሪካዊ ክስተት ብቻ አይደለም፤ ዓለምን የመቤዠት የእግዚአብሔር ተልእኮ ወሳኝ ተግባር ነው፡፡ በተልእኮ ሥነ መለኮት ውስጥ፣ ተልእኮ የሚጀምረው በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ እንደሆነ ያስተምራል፡፡ አብ ወልድን ይልካል፤ አብና ወልድ መንፈስ ቅዱስን ይልካሉ፤ ሥሉስ አሐዱ አምላክ ወይም እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ወደ ዓለም ይልካል፡፡ ስለዚህ፣ ግርግሙ እግዚአብሔር ለሕዝብ ኹሉ የሚያደርገው የቤዛነት እንቅስቃሴ መጀመሪያ ነው፡፡
የማቴዎስ ወንጌል ተዛማጅ ክፍል የጌታን ልደት መለኮታዊ ዐላማ መግለጫ ይሰጣል፡፡ ኢየሱስ የተወለደው “ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ለማዳን” ነው(ማቴ. 1፥21)፡፡ ስለዚህ ሥጋዌው በራሱ ፍጻሜ ሳይሆን ቤዛነት የሚከናወንበት አስፈላጊ መንገድ ነው። በርግጥ መጽሐፍ ቅዱሳችን ቃል ሥጋ የመሆኑ ዝርዝር ዓላማዎች በብዙ መንገድ ይገልጻል፡፡ መለኮታዊውን ባሕርይ ለሰው ልጅ ለመግለጥ(ዮሐ. 14፥9፣ ዮሐ. 1፥18)፣ የኀጢአትን ዕዳ ለመክፈል፣ የሰይጣንን ሥራ ለማፍረስ((ዕብ. 2፥14፣ 1ዮሐ. 3፥9)፣ ሊቀ ካህናት ለመሆን ሰው ኾነ(ዕብ. 5፥1)፡፡
ስለ መወለዱ ስናወራ ከሞቱና ከትንሣኤው ነጥለን ሊሆን አይችልም፡፡ የክርስቶስ ልደትና ሞት የአንድ ሳንቲም ኹለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ አንዱ ያለ አንዱ ትርጉም አይሰጥም፡፡ አምላክ በባሕርዩ ዘላለማዊ ነው፤ ሊሞት አይችልም፡፡ ነገር ግን እኛን ለማዳን የግድ መሞት ነበረበት፡፡ ስለዚህ ሥነ-መለኮታዊው ምስጢር እዚህ ጋር ነው፡፡ ክርስቶስ ሰው የሆነው ለመሞት የሚያስችለውን ሰውነት ለማግኘት ጭምር ነው፡፡ በቤተልሔም በረት ውስጥ ድንግል ማርያም ያቀፈችው ያ ሕፃን፣ ለሞት የተዘጋጀ መሥዋዕት ነበር፡፡ ሥጋዌ እግዚአብሔርን ከእኛ ጋር መሆኑን ያሳያል፡፡ መስቀሉ ደግሞ እግዚአብሔርን ለእኛ ይገልጣል፡፡ ትንሣኤ እግዚአብሔርን በእኛ መካከል ድል አድራጊ አድርጎ ያሳያል፡፡ ስለዚህ የማይነጣጠሉ ነገሮች ናቸው፡፡
የምሥራቹ መገለጥ፦ ሰማይ ምድርን ሲጎበኝ (ቁ. 7-14)
በግርግም የተወለደ አዳኝ (ቁ. 7)፡ የእግዚአብሔር ተልእኮ መጀመሪያ
ወደ ሉቃስ ክፍል ስንመጣ፣ ሉቃስ እንደሚነግረን ማርያም “የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።” ቁ.7 ለአፍታ አስቡት፡፡ የዓለም አዳኝ እንስሳት የሚያድሩበት ግርግም ተወለደ፡፡ የክብር ንጉሥ ያለ ጭብጨባ፣ ያለ ምቾት፣ ያለ እውቅና ወደ ዓለም ገባ፡፡ እግዚአብሔር ተልእኮውን የሚጀምረው በዚህ መንገድ ነው፡፡ አጽናፈ ዓለሙን የሚይዘው እርሱ በእናቱ እቅፍ ተያዘ፡፡ ግርግሙ ስለ እግዚአብሔር ልብ ጥልቅ ስሜት የሚፈጥር ነገር ይነግረናል፡፡ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ንፁህ፣ ብቁ ወይም ዝግጁ እስኪሆን አልጠበቀም፡፡ ወደ ቆሻሻ ማንነቱ መጣ፡፡
ምስራቹ የተገለጠላቸው ሰዎች እግዚአብሔር ታላቁን ምስጢር (ቃል ሥጋ መሆኑን) ለመግለጥ የመረጠው የቤተ መንግሥት መኳንንትን ሳይሆን፣ በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ ተራ እረኞችን ነው፡፡ ወንጌልን የሰሙት የመጀመሪያዎቹ ካህናት አይደሉም፡፡ ነገሥታት አይደሉም፡፡ ምሁራን አይደሉም፡፡ እረኞች፡፡ እግዚአብሔር ለተናቁት እረኞች ታላቁን ምስጢር(ቃል ሥጋ መሆኑን) መግለጡ ያስደንቃል፡፡ እረኞች ድሆች፣ ቆሻሻዎች እና በኅብረተ ሰቡ ችላ የተባሉ ነበሩ፡፡ ሆኖም እግዚአብሔር በታሪክ ውስጥ እጅግ ታላቅ የሆነውን አዋጅ በዐደራ ሰጣቸው፡፡
የምስራቹ ይዘት
“እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ” ቁ.10
“ለሕዝብ ሁሉ” የሚለው ሐረግ የምሥራቹን ስፋት ወይም የእግዚአብሔርን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ ስፋት ያሳያል፡፡ ትስጉት(የአምላክ ሰው መሆን) እግዚአብሔር በአብርሃም ዘር አማካኝነት ሁሉንም አሕዛብ እንደሚባርክ የሰጠውን የብሉይ ኪዳንን ተስፋዎች ፍጻሜ ነው (ዘፍ. 12፥3)፡፡ ኢየሱስ የእስራኤል መሲሕ ብቻ ሳይሆን የዓለም አዳኝ ሆኖ ተወለደ (ዮሐ. 4፥42)፡፡ የዓለም ዜናዎች "ለተመረጡት" ናቸው፡፡ የኢየሱስ ምሥራች ግን የድንበር አጥር የለውም፡፡ ለእረኞች (ለተናቁት) ተበሰረ፤ ለሰብአ ሰገል (ለጥበበኞች) ተገለጠ፤ ለአይሁድም ለአሕዛብም ሆነ፡፡ ይህ የምሥራች እንደ ሰማይ ዝናብ ነው፡፡ ዝናብ በሀብታም እርሻ ላይ ብቻ አይዘንብም፤ ድሃውም ጋ ይደርሳል፡፡
ነፍሳችን የጠማትን ዕረፍት፣ ልባችን የናፈቀውን ፍቅር ያገኘነው በቤተልሔሙ ሕፃን ውስጥ ነው፡፡ ዓለም ሊሰጠን የማይችለውንና ሊነጥቀን የማይችለውን ሰላም ይዞልን መጣ፡፡ የደስታው ዓይነት “ታላቅ ደስታ” ተብሎ ተገለጸ፡፡ ይህ ደስታ "ታላቅ" የተባለው ከመጠን በላይ ስለሆነና በምድር ስለማይገኝ ነው፡፡ ምድራዊ ደስታ በኪሳችን ሁኔታ፣ በጤናችን ወይንም በሰዎች አመለካከት ላይ ይወሰናል፡፡ የኢየሱስ ደስታ በሞት ሸለቆ ውስጥ ስናልፍ እንኳ የማይጠፋ፣ በችግር እሳት ውስጥ የማይቃጠል፣ በክርስቶስ ማንነት ላይ የተመሠረተ የውስጥ ሰላም ነው፡፡
የሰማይ መልስ ለምድር ፍርሃት ("አትፍሩ!")
መልአኩ "አትፍሩ" አለ፡፡ ዓለም በጨለማ፣ በኃጢአትና በሞት ጥላ ተውጣ በነበረችበት ወቅት ሰው እግዚአብሔርን መፍራት ብቻ ሳይሆን መቅረብም ይፈራ ነበር፡፡ የኢየሱስ መምጣት የፍርሃትን ሰንሰለት ሰባበረ፡፡ እግዚአብሔር ከሰው ጋር ሊጣላ ሳይሆን ሊታረቅ፣ ሊፈርድ ሳይሆን ሊያድን ወደ ምድር ወረደ፡፡ እርሱ ሲመጣ ፍርሃት ቦታውን ለፍቅር፣ ጭንቀት ደግሞ ቦታውን ለሰላም ለቀቀ፡፡ ዛሬም ይህ ምሥራች ለልባችሁ የሚለው፦ "አትፍሩ፤ አዳኝ ተወልዶላችኋል!" የሚል ነው፡፡ መልአኩ “ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና” አለ፡፡ ይህ ስለ ተልእኮ አንድ አስፈላጊ ነገር ይነግረናል፡፡ የእግዚአብሔር መልእክት ለአስፈላጊዎች ብቻ አይደለም፣ ለተረሱት ኹሉ ነው፡፡ በዚያች ሌሊት፣ እረኞች በሰማይ ተመርጠዋል፡፡
የምስራቹ ማንነት
“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” ቁ.11
2 536
እኛ ያለን አንድ ነው፤ እሱም ኢየሱስ። በሁሉም ስፍራ (በሰማይም በምድርም) እርሱን እየመነዘርን እንኖራለን! እርሱ ሁሉን ሆነልን!
2 536
እግዚአብሔር ኀጢአትን የሚጠላ መሆኑን መጠራጠር ስንጀምር፣ መስቀሉን ማሰብ ይኖርብናል፡፡ ልጁ የተቀለደበት፣ የተፌዘበት እና የተገረፈበት ምክንያት ኀጢአት ነው!
_ ፍራንሲስ ቻን
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
