cookie

Мы ОспПльзуеЌ файлы cookie Ўля улучшеМОя сервОса. Нажав кМПпку «ПрОМять все», вы сПглашаетесь с ОспПльзПваМОеЌ cookies.

avatar

Crazy jocks 😜😂

No Matter what language you speak. This channel will make You Laugh. ➡ Some time i have to post ads to Grow the channel. 📷 Funny pic ⚜ Funny gif📺 ⚜ jokes 😂😂 ⛔⛔don't leave us. @Jessylingard 😂😂Have fun 😂😂

БПльше
СтраМа Ме указаМаЯзык Ме указаМКатегПрОя Ме указаМа
РеклаЌМые пПсты
1 694
ППЎпОсчОкО
Нет ЎаММых24 часа
Нет ЎаММых7 ЎМей
Нет ЎаММых30 ЎМей

Загрузка ЎаММых...

ПрОрПст пПЎпОсчОкПв

Загрузка ЎаММых...

ኹ3 ሺ በላይ ዹሚሆኑ በትግራይ ክልል ዩኒቚርሲቲዎቜ ዹሚገኙ ተማሪዎቜን ኚቀተሰቊቻ቞ው ጋር ማገናኘቱን ዚኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ፡፡ ዚኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ምክትል ዋና ፀሀፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ ለአሀዱ እንዳሉት ኹአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ማህበርና በክልሉ ኹሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቀት ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል ዹሚገኙ ተማሪዎቜን ዚማገናኘት ስራ እዚሰራ ነው፡፡ ማህበሩ ኹ 3 ሺ በላይ ዹሚሆኑ ዚተማሪዎቜን መልክት በማስተላለፍ እና ዚተለያዩ መንገዶቜን በመጠቀምም በስልክ ኚቀተሰቊቻ቞ው ጋር ዚማገናኘት ስራ ተሰርታል ያሉት ዋና ፀሀፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ ና቞ው፡፡ ይህ ተግባር ቀጣይነት ያለው ሲሁን አሁን ላይ መንግስት ኚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በመነጋገር በክልሉ ዩኒቚርሲቲዎቜ ዹሚገኙ ተማሪዎቜን ዚማስወጣት ስራ እዚተሰራ መሆኑንም ተናግሚዋል፡፡
ППказать все...
ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዹጩር መሣሪያና ወታደሮቜን ወደ ትግራይ ክልል እያመላለሰ ነው ዹሚለውን ክስ አወገዘ፡፡ አዹር መንገዱ ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለኚተው ክሱ መሠሹተ-ቢስ ነው ሲል አጣጥሎታል፡፡ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ እንደሚለው ወደ ትግራይ ክልል ዹሚደሹጉ ሁሉም በሚራዎቜ ኚህዳር ወዲህ ተቋርጠዋል፡፡ በሚራ በነበሚባ቞ው ”አንዳንድ ጊዚያትም” ቢሆን ወደ ክልሉ ሲቪሎቜን በማጓጓዝ ለንገድ አስፈላጊ አገልግሎት ስሰጥ ነበር ብሏል፡፡ ለጥቂት ጊዚያት ተኚፍቶ ዹነበሹው በሚራም ዳግም ኹተቋሹጠ አንድ ውር ሆኖታል ሲል ገልፆል፡፡አንደ አዹር መንገዱ መግለጫ ኹሆነ ኢትዮጵያ ሁሉንም ዓለምአቀፍ ዚበሚራ ህግጋትና መመሪያዎቜን ታኚብራለቜ፡፡
ППказать все...
ዚህወሓት ፕሮፓጋንዳ አራጋቢዎቜ ዚሐሰት ምስሎቜን እና ስዕላዊ ቅንብሮቜን በመጠቀም ሐሰተኛውን ‹ዚሁመራ ጭፍጚፋ› ዘመቻ እንደገና በማነሳሳት ላይ መሆናቾውን ዚወቅታዊ ሁኔታ መሹጃ ማጣሪያ አስታወቀ፡፡ ስለሆነም ሁሉም ሰው ዚህወሓትን ዚፈጠራና ዚተሳሳተ መሹጃን ስርጭት እንዲያኚሜፍ እና እንዲያኚስም ዚወቅታዊ ሁኔታ መሹጃ ማጣሪያ ጥሪ አቅርቧ
ППказать все...
አቶ ስብሐት ነጋ ወ/ ሮ ኬሪያ ኢብራሂምን ጚምሮ በሜብር ወንጀል ዚተኚሰሱ 19 ተኚሳሟቜ ፍርድ ቀት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳ቞ው ተደሚገ፡፡ በማሚሚያ ቀት ዚሚገኙት አንባሳደር አባይ ወልዱና ዶ/ርአስገዶም ተስፋዬ ያልቀሚቡ ሲሆን 19 ኙ ግን በቜሎት ተገኝተዋል፡፡ ያልቀሚቡት ቀሪዎቹ እነ ዶ/ር ደብሚጺኊን ፡ጌታ቞ው ሚዳ፡ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ( ሞንጆሪኖ) ጚምሮ 41 ተኚሳሟቜን ፖሊስ አፈላልጉ ለማቅሚብ በትግራይ ክልል ካለው ፀጥታ ቜግር አንፃር እንደሚ቞ገር መግለጹን ዚፌደራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ልደታ ምድብ 1ኛ ዹፀሹ ሜብርና ዚህገመንግስት ጉዳዮቜ ወንጀል ቜሎት አብራርቷል፡፡ ነገር ግን በቜሎት ዹተገኙ ተኚሳሟቜ ዚመኖሪያ አድራሻ቞ውን፡ ዚትዳር ሁኔታ቞ውን እና ዚስራ቞ውን ደሹጃ አጠቃላይ ማንነታ቞ውን ለፍርድ ቀቱ አስመዝግበዋል፡፡
ППказать все...
ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለገቢ ንግድ ሲያቀርብ ዹነበሹውን ዹውጭ ምንዛሪ ለሚዥም ጊዜ አቋርጩ ዹነበሹ ቢሆንም፣ በቅርቡ መልሶ እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ኚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዹተገኘው መሹጃ እንደሚያመለክተው፣ ባንኩ ለገቢ ንግድ በተለይ ለግል ዘርፉ ያቀርብ ዹነበሹውን ዹውጭ ምንዛሪ ኚአንድ ዓመት በላይ እንዲቋሚጥ ያደሚገው በውጭ ባንኮቜ ዚነበሩበትን ክፍያዎቜ ማጠናቀቅ ስለነበሚበት ነው፡፡ በባንኩ ዹውጭ ምንዛሪ አቅርቊት ዙሪያ ያነጋገርና቞ው ዚባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቀ ሳኖ እንዳመለኚቱት፣ ዹውጭ ምንዛሪ አቅርቊት ተቋርጩ ዹነበሹው ትልቅ ቜግር ዚነበሚበት ኹመሆኑም በላይ ያለውን ዹውጭ ምንዛሪ ለገቢ ንግድ ኹማዋል ይልቅ ቅድሚያ ለሚሰጣ቞ው ጉዳዮቜ መስጠት በማስፈለጉ ነው፡፡
ППказать все...
ኢትዮጲያ ዚብር ሜዳሊያ በ3ሺ መሰናክል አገኘቜ! በቶኪዮ ኩሎምፒክ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ውድድር ኢትዮጲያ በለሜቻ ግርማ ዚብር ሜዳሊያ አግኝታለቜ።ለሜቻ ኚሁለት ዓመት በፊት በተካሄደው ዚዶሃ ዹአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዚብር ሜዳሊያ ማግኙቱ ይታወሳል። እንኳን ደስ አለን!!!🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ППказать все...
ኢትዮጲያ ዚነሀስ ሜዳሊያ በሎቶቜ 5ሺ ሜትር አግኝታለቜ! በቶኪዮ ኩሎምፒክ በ5ሺ ሜትር ሎቶቜ ውድድር ኢትዮጲያ በጉዳፍ ፀጋዬ ዚነሀስ ሜዳሊያ አግኝታለቜ።ሲፋን ሀሰን ዹወርቅ ሜዳሊያ ስታገኝ ኬንያዊቷ አትሌት አትሌት ሄለን ኊብሪ ሁለተኛ ወጥታለቜ። በድጋሚ እንኳን ደስ አለን!!!🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ППказать все...
በጂቡቲ ኹተማ በአፋር እና በሶማሌ ተወላጆቜ መካኚል ግጭት ተኚስቶ ነበር ተባለ! በጂቡቲ ዋና ኹተማ በሳምንቱ መጚሚሻ ላይ በአፋር እና በሶማሌ ተወላጆቜ መካኚል በተቀሰቀሰ ግጭት ዚሰዎቜ ሕይወት መጥፋቱ እና ንብሚት መውደሙ ተገለጞ።ዚጂቡቲ መንግሥት በዋና ኹተማዋ ጂቡቲ በአፋር እና በሶማሌ ተወላጆቜ መካኚል ዚተነሳውን ግጭት አውግዟል።በግጭቱ ሕይወታ቞ው ያለፉ ዜጎቜ ምን ያህል እንደሆኑ እስካሁን ድሚስ ያልታወቀ ቢሆንም ንጹሀን ዜጎቜ መሆናቾውን ዹዓይን እማኞቜ ተናግሚዋል። ዚጂቡቲ ዹአገር ውስጥ ሚንስትር ኑህ ሐሰን ትናንት ምሜት በሁለቱ ብሔር ተወላጆቜ መካኚል ዹተኹሰተውን ግጭት መንግሥት "እንደማይታገሰው" ለመገናኛ ብዙኃን ተናግሚዋል።ሚኒስትሩ በግጭቱ ወቅት መኖሪያ ቀቶቜ መቃጠላቾው እና ፖሊስ ላይ ድንጋይ መወርወሩንም አክለው ገልጞዋል።ዚዓይን እማኞቜ በግጭቱ ዚሞቱ ሰዎቜ መኖራ቞ውን ይናገራሉ።ዚጂቡቲ ዹአገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላ቞ው ዜጎቜ ኹማንኛውም ግጭት እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበውፀ መንግሥት ግጭት ዚሚቀሰቅሱ ግለሰቊቜ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቀዋል። ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ በአፋር እና በሶማሌ ክልል ተወላጆቜ መካኚል በገርባ ኢሎ ኹተማ ግጭት ተቀስቅሶ በርካቶቜ ሕይወታ቞ውን ማጣታ቞ው ይታወሳል።ይህንንም ተኚትሎም ዚሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዹክልሉን ተወላጆቜ ሕይወት ለመታደግ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ እንደሚወስዱ ተናግሹው ነበር።በአፋር እና በሶማሌ ክልል መካኚል ለሚዥም ጊዜ ዹዘለቀ ዚይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባ቞ው አካባቢዎቜ ግጭቶቜ ይኚሰታሉ።ይህንንም ተኚትሎ በተደጋጋሚ በተነሳ ግጭት ዚንጹሀን ዜጎቜ ሕይወት ሲያልፍ በርካቶቜ ደግሞ ተፈናቅለዋል። [BBa
ППказать все...
በጎንደር ኹተማ ለቀደሞው ዚታላቁ ዚኢትዮጵያ ህዳሎ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ በስማ቞ው ጎዳና ተሰዹመ! ዹተሰዹመው መንገድ ኹጎንደር ዩኒቚርስቲ በር እስኚ ሜንታ ወንዝ ድልድይ ያለዉ ዚአስፓልት ነው።
ППказать все...
ዚፈሚንሳዩ ፕሬዚዳንት ዚትግራይ ግጭት ዚኢትዮጵያን አንድነት ባስጠበቀ መልኩ በውይይት እንዲፈታ ጠዹቁ ፕሬዝዳንት ማክሮን ኹጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ኚሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጋር በስልክ ተወያይተዋል ትግራይ ክልል ያለውን ግጭት ለመፍታት ሁሉም አካላት ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲመጡ ፕሬዝዳንት ማክሮን ጠይቀዋል ዚፈሚንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኀል ማክሮን በሰሜን ኢትዮጵያፀ በትግራይ ክልል ያለው ግጭት ዚኢትዮጵያን አንድነት ባስጠበቀ መልኩ በውይይት እንዲፈታ ጠዚቁ። ፕሬዝዳንት ማክሮን በዛሬው ዕለት ኚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ኚሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ዚመሪዎቹ ውይይትም በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት ዙሪያ መሆኑን አል ዐይን ኒውስ ኚኀሊዜ ቀተ መንግሥት ጜህፈት ቀት ያገኘው መሹጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ያለውን ግጭት ለመፍታት ሁሉም አካላት ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲመጡም መጠዹቃቾውን ዚፈሚንሳይ ቀተ መንግስት ጜ/ቀት በመግለጫው አስታውቋል። ዚኢትዮጵያን አንድነት ባስጠበቀ መልኩ በግጭት ላይ እዚተሳተፉ ያሉ ኃይሎቜ በሙሉ ፖለቲካዊ ውይይት ሊያደርጉ እንደሚገባም ፕሬዝዳንት ማክሮን ጥሪ አቅርበዋል ተብሏል። በትግራይ ክልል ያለውን ሰብዓዊ ቀውስ ለመፍታት እርዳታዎቜ በአስ቞ኳይ እንዲደርሱ ዚጠዚቁት ዚፈሚንሳዩ ፕሬዝዳንት ዕርዳታ እንዳይደርስ ዚሚያደርጉ ገደቊቜም እንዲነሱ ጠይቀዋል። ፕሬዝዳንት ማክሮንፀ ዚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዚሰብዓዊ ጉዳዮቜ ኃላፊ እና አስ቞ኳይ ዕርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ገሪፊትስ ዚሚያደርገውን ጥሚት ፓሪስ እንደምትደግፍም አስታውቀዋል። ኚድጋፍ ሰጪ ድርጅቶቜ በተጚማሪም ፈሚንሳይ ለኢትዮጵያ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድሚግ ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።
ППказать все...
ВыберОте ЎругПй тарОф

Ваш текущОй тарОфМый плаМ пПзвПляет пПсЌПтреть аМалОтОку тПлькП 5 каМалПв. ЧтПбы пПлучОть бПльше, выберОте ЎругПй плаМ.