cookie

Мы ОспПльзуеЌ файлы cookie Ўля улучшеМОя сервОса. Нажав кМПпку «ПрОМять все», вы сПглашаетесь с ОспПльзПваМОеЌ cookies.

avatar

🇪🇹 Ministry of Science and Higher Education

@minster_of_education1 ቀዳሚ ዚተማሪዎቜ ዹመሹጃ ምንጭ 🇪🇹 Share and Support us @minster_of_education1 መሹጃ እና መልዕክት መቀበያ 📧 @ministryofeducation2 @minstryofeducation2 ማስታወቂያ ለማሰራት @minster_of_education1

БПльше
РеклаЌМые пПсты
841
ППЎпОсчОкО
Нет ЎаММых24 часа
Нет ЎаММых7 ЎМей
Нет ЎаММых30 ЎМей

Загрузка ЎаММых...

ПрОрПст пПЎпОсчОкПв

Загрузка ЎаММых...

ፎቶፊ ዚኢፌዎሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ዚሚኒስትሮቜ ልዑክ ቡድን በሮምፀ ጣሊያን ዚሥራ ጉብኝት በማድሚግ ላይ እንደሚገኙ ዹጠ/ሚ ፅ/ቀት አሳውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኚፕሬዝዳንት ሎርጂዮ ማታሬላ ጋር ባደሚጉት ዚሁለትዮሜ ውይይት በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካኚል ስላለው ግንኙነት እንዲሁም በሌሎቜ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮቜ ላይ መክሹዋል ተብሏል። Photo ፊ PMOEthiopia @tikvahethiopia
ППказать все...
ЀПтП МеЎПступМПППказать в Telegram
ዹ12ኛ ክፍል ሀገርአቀፍ ፈተና ዉጀትን ኚዛሬ ለሊት ጀምሮ መመልኚት ይቻላል‌ ለ2014 ትምህርት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ፈተና ውጀት ዹተለቀቀ በመሆኑ ተፈታኞቜ ኚዛሬ ጥር18 2015 ዓ.ም ኚሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ • በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ • በ6284 አጭር ዚጜሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ ዚምዝግባ ቁጥራ቞ውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም • በ቎ሌግራም ላይ https://t.me/eaesbot መመልኚት ትቜላላቜሁ ሲል ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አስታዉቋል፡፡ ሚኒስ቎ሩ አክሎም ፀ ማንኛውም ቅሬታ ያላ቞ው ተፈታኞቜ በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስኚ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድሚስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant ዹሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቅሬታ቞ዉን ማቅሚብ ይቜላሉ ብሏል፡፡ በተጚማሪም ተማሪዎቜ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት አድራሻ ላይ ብቻ ይጠቀሙ ዚተባለ ሲሆን ኚተመሳሳይ እና ዚተዛባ መሹጃ ለማሰራጫት ኚሚሞክሩ አካላት ይጠንቀቁ ሲል ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አሳስቧል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ ዚንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ቎ር ፀ ዚታህሳስ ወር ዚነዳጅ ምርቶቜ መሞጫ ዋጋ በህዳር ወር 2015 ዓ.ም እዚተሞጠበት ባለው ዋጋ ዚሚቀጥል መሆኑን ዛሬ አስታውቋል። ኚዛሬ ኅዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ኚሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ እስኚ ታህሳስ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድሚስ ዚአውሮፕላን ነዳጅን ጚምሮ ዚነዳጅ ምርቶቜ ዚቜርቻሮ መሞጫ ዋጋ በህዳር ወር 2015 ዓ.ም እዚተሞጠበት ባለው ዋጋ ይቀጥላል ብሏል። ምንጭ፩ ዚንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስ቎ር @tikvahethiopia
ППказать все...
#DrAlQaradawi ዚሙስሊም ምሁራን ፌዎሬሜን መስራቜና ፌዎሬሜኑን ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ዚመሩት እውቁ ዚእስልምና ምሁር ግብፃዊ ዶክተር ሌክ ዩሱፍ አል ቃራዳዊ በ96 ዓመታ቞ው ህይወታ቞ው አልፏል። ህልፈታ቞ውን ልጃቾው አብዱል ራህማን ዩሱፍ አል ቃራዳዊ አሚጋግጠዋል። ዶ/ር አልቃራዳዊ ህይወታ቞ው ያለፈው ኳታርፀ ዶሃ ውስጥ ነው። እኀአ 2004 ዹተቋቋመውን (እሳ቞ው መስራቜ ነበሩ) ዓለም አቀፉ ዚሙስሊም ምሁራን ፌዎሬሜን ኹተቋቋመበተ ጊዜ አንስቶ ለ14 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት መርተዋል። ዶ/ር አልቃራዳዊ ኚሙስሊም ወንድማማ቟ቜ ጋር ግንኙነት ዚነበራ቞ው ሲሆን ዚኳታር ዜግነት ተሰጥቷ቞ው ህይወታ቞ው እስክታለፍ ድሚስ ኑሯ቞ውን በኳታር፣ዶሃ አድርገው ነበር። አልቃራዳዊ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ወቅት በግብፅ በ1926 ነበር ዚተወለዱት። ገና በለጋ እድሜያ቞ው እስላማዊ ትምህርትን መኚታተል ዚጀመሩት አልቃራዳዊ በፀሹ ቅኝ አገዛዛ ላይ እንቅስቃሎ ያደርጉ ነበር። በ1950 ዎቹ ኚፖለቲካዊ እንቅስቃሎና ኚሙስሊም ወንድማማ቟ቜ ንቅናቄ ጋር በተገናኘ ብዙ ጊዜ ለእስር ተዳርገው ነበር። ኹ120 በላይ መፅሀፍትን ያሳተሙት ዶ/ር አል ቃራዳዊ ለእስልምና ባበሚኚቱት አስተዋፆ 8 ዓለም አቀፍ ሜልማቶቜን መሾለም እንደቻሉ ተገልጿል። ዶ/ር አል ቃራዳዊ በክፈለ ዘመኑ በጣም ታዋቂ ኹሆኑ ዚእስልምና ሊቃውንት አንዱ እንደነበሩ ተዘግቧል። በህይወት በነበሩበት ወቅት በተለያዩ ሚዲያዎቜ በተለያዩ ጉዳዮቜ ዙሪያ አመለካኚታ቞ውን ሲያጋሩ ዹነበሹ ሲሆን በሚያነሷ቞ው ሀሳቊቜ ዹሚደግፏቾው እንዳሉ ሁሉ ሀሳባ቞ውን ዹሚቃወሙም ነበሩ። ዚዶ/ር አልቃራዳዊን ህልፈት ተኚትሎ ፀ ዚተርክዬ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኀርዶጋን  ለልጃቾው አብዱል ራህማን በመደወል ዹተሰማቾውን ሀዘን ገልፀው አፅናንተዋል። @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ሐይቅ ! ዹሐይቅ ኹተማ አስተዳደርና ዚተሁለደሬ ወሚዳ ዚጞጥታ ም/ቀት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ፊ -  ዚባለ 3 እግር ተሜኚርካሪና አነስተኛና መለስተኛ ዚህዝብ ማመላለሻ ተሜኚርካሪዎቜ ላይ ኚምሜቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ዚእንቅስቃሎ ገደብ ተጥሏል። - ዚመጠጥ ግሮሰሪዎቜ ኚምሜቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ተኚልክሏል። - ህግ ኚሚያስኚብሩ ዚጞጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ዹኹተማው ነዋሪ ኚምሜቱ 2፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተኚልክሏል። - በዚጫት ቀቱና መቃሚያ ቀቶቜ በማንኛውም ሰዓት መሰባሰብፀ በነዚህ አካባቢዎቜ መቃምና መገኘት ተኚልክሏል። - ኚጞጥታ ኃይሉ ውጭ በዘመቻ ሰበብ ኚመንግስት እውቅና ውጭ ማንኛውንም ወታደራዊ አገልግሎት ዚሚሰጥ አልባሳት፣ ትጥቅ፣ ዹጩር መሳሪያና ዚመሳሰሉትን በማንኛውም ሰዓት በኹተማው ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተኚልክሏል። - ተፈናቅይም ሆነ ሌሎቜ ወደኹተማው ዚሚገቡ ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜ አገልግሎት በሚያገኙበት ተቋም ራሳ቞ውን ዹመግለፅ እንዲሁም ተቋማቱም መጠዹቅ እንዳለባ቞ው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። - በኹተማው አሉባልታ መንዛት፣ ህዝቡን በማሾበር አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ፣ ዹግል ንብሚት እና እቃ እንዲሰብሰብ ማነሳሳት በጥብቅ ተኚልክሏል። ነዋሪዎቜ ማንኛውም ጥቆማ ካላ቞ው በ 033 222 0481 ፣ 033 222 0955 ፣ 0333 222 0006 በመደወል መጠቆም ይቜላሉ ተብሏል። (ተጚማሪ ኹላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ЀПтП МеЎПступМПППказать в Telegram
#SafaricomEthiopia #DireDawa ለሲም ካርድ ሜያጭ ምዝገባ፣ ለስልክ ቀፎዎቜ ግዢ ፣ ለአዹር ሰዓት እና ልዩ ልዩ ዚደንበኞቜ አገልግሎት ኹ3ቱ ዚሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሜያጭ ማዕኚላት (ኚዚራ፣ መስቀለኛ፣ ኮኔል ኚሚገኙት) በተጚማሪ ብራንድድ በሆኑ በሁሉም ዹኹተማው ሱቆቜ #ሲም_ካርድ እና #አዹር_ሰዓት ማግኘት እንደሚቻል ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል። #SafaricomEthiopia #ድሬዳዋ #DireDawa @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#KOBO ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ " ቆቩ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ። ዚኢፌዎሪ መንግስት ኮሚኒኬሜን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት ዹሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም ዹቆቩ ኹተማን ኹውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል። በሌላ በኩል ደግሞ በኹተማ ውስጥ ሠርጎ ገቊቜን በማሥሚግ ዚሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ ዹኹተማ ውስጥ ውጊያ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ሁኔታ እዚፈጠሚ ይገኛል ብሏል። በዚህም ፀ " ዚሕዝብን ኹፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ ዚመኚላኚያ ኃይል ዹቆቩ ኹተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመኹላኹል ዚሚስቜለውን ወታደራዊ ይዞታዎቜን ለመያዝ ተገዷል " ሲል አሳውቋል። ዚኢፌዎሪ መንግስት ኮሚኒኬሜን ፥ " አሞባሪው ኃይል ዚትግራይን ወጣት እዚማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መኚላኚያ ሕጋዊ ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዎታውን ለመወጣት ዚሚገደድ ይሆናል " ብሏል። ምንም እንኳን ኚተለያዚ አቅጣጫ ሰላም እንዲሰፍን እና መሳሪያ ወርዶ ንግግር እንዲጀመር ጥሪዎቜ ቢቀርቡም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገሚሞው ግጭት ኚዕለት ወደ ዕለት እዚተባባሰ መጥቷል። @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopiaAirlines ኢትዮጵያ አዹር መንገድ ፀ ኚካርቱም ወደ አዲስ አበባ ሲበር ዹነበሹ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚበሚራ ቁጥር ET343 አውሮፕላን ነሀሮ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ኚአዲስ አበባ አዹር ትራፊክ ቁጥጥር ጋር ያለው ግንኙነት ለጊዜው ተቋርጩ እንደነበር ዹሚጠቁም ሪፖርት እንደደሚሰው አመልክቷል። ሆኖም ግንኙነቱ ኹተመለሰ በኋላ አውሮኘላኑ በሰላም እንዳሚፈ ገልጿል። ተጚማሪ #ምርመራ እስኚሚያጠናቅቅ ጉዳዩ ዚሚመለኚታ቞ው ሠራተኞቜ ኚሥራ ታግደው ይቆያሉም ብሏል። በምርመራው ውጀት መሰሚት ተገቢውን ዚእርምት እርምጃ ይወሰዳል ያለው ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ደህንነትን ማስጠበቅ  ዹሁልጊዜም ዚመጀመሪያው ተግባሩ ሆኖ እንደሚቀጥል አሚጋግጧል። @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ЀПтП МеЎПступМПППказать в Telegram
" በአስር ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዜጎቜ በአስኚፊ ቜግር ውስጥ ናቾው " - ዚሶማሌ ክልል ዚሶማሌ ክልላዊ መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ፀ በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ አካባቢዎቜ በሚገኙ አካባቢዎቜ ላይ በተፈጠሹው ግጭት ምክንያት በአስር ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዜጎቜ በአስኚፊ ቜግር ውስጥ እንደሚገኙ ገልጿል። ክልሉ ኚግጭቱ ጋር በተያያዘ ዝርዝር መሹጃ አልሰጠም። ኚመኖሪያ ቀዬአ቞ው ዚተፈናቀሉት ዜጎቜ በአሁኑ ወቅት በሲቲ ዞን ኀሚር ወሚዳ አስቡሊ እና በድዌይ በሚባል አካባቢ ዚተሰባሰቡ ቢሆንም በክሚምቱ ኚባድ ዝናብ ምክንያት መንገዶቜ በመቆራሚጣ቞ውና ወደ አካባቢው ተሜኚርካሪ ሊገባ ባለመቻሉ ምንም አይነት ዚእለት ደራሜ እርዳታ áˆˆáˆ›á‰…ሚብ አልተቻለም ብሏል። በአሁኑ ወቅት ተፈናቃዮቹ በኹፍተኛ ቜግር ውስጥ ይገኛሉ ያለው ዹክልሉ መንግስት ኚፌዎራል መንግሥት ጋር በመቀናጀት አፋጣኝ እርዳታ ለማቅሚብ ጥሚትና ርብርብ እያደሚገ እንደሚገኝ ገልጿል። ለዚህም ዚሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ እና ም/ርዕሰ መስተደድር ኢብራሂም ኡስማን ዚተካተቱበት ዹክልሉ ኹፍተኛ አመራሮቜ ልኡካን ቡድን ተፈናቃዮቜ በሚገኙበት በሲቲ ዞን በመገኘት ሰብአዊ ድጋፍ ለማድሚስ በማስተባበር ላይ ይገኛሉ ሲል ክልሉ አሳውቋል። @tikvahethiopia
ППказать все...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ዚተሰራጚው ሀሰተኛ ወሬ ነው " - ዚሶማሌ ክልል መንግስት ዚሶማሌ ክልል መንግስት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ á‰ áŠ­áˆáˆ‰ ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ሙሁመድ ላይ "ዚግድያ ሙኚራ ተደሚገባ቞ው" በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ዚተሰራጚው መሹጃ ሀሰተኛ ነው ብሏል። ዹክልሉ መንግስት " በትላንትናው እለት በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎቜ በሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ ላይ ዚግድያ ሙኚራ ተደሹገ ተብሎ ዚተሰራጚው ዜና ኚእውነት ዚራቀ ሀሰተኛ ወሬ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን " ብሏል። በትላንትናው ዕለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎቜ ዚሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደርን ዚሚመለኚቱ መሚጃዎቜ ሲሰራጩ ነበር። አንደኛው ይኾው "ዚግድያ ሙኚራ ተደሚገባ቞ው" ዹሚለው ሲሆን ዚግድያ ሙኚራ ተደሚገባ቞ው ዚተባለው ለስራ ጉዳይ "ቢኪ" ዚሚባል ቊታ በሄዱበት ወቅት ነው። ሌላኛው ደግሞፀ ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ወደዚሁ "ቢኪ" ዚተባለ ስፍራ በሄዱበት ወቅት ወጣቱን ጚምሮፀ ህብሚተሰቡ በመቆጣቱ ኹፍተኛ ተቃውሞ እንደነበርፀ ድንጋይም እስኚመወርወር ዹደሹሰ ክስተት እንደተፈጠሚ ዹሚገልፅ መሹጃ ተሰራጭቷል። ዹክልሉ መንግስትፀ በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ላይ "ዚግድያ ሙኚራ አልተደሚገባ቞ውም ውሞት ነው" ዹሚል መግለጫ ቢሰጥም በተመሳሳይ ሰዓት ስለተሰራጚው ዹ "ቢኪ" ኹፍተኛ ተቃውሞ በተመለኹተ እንዲሁም ርዕሰ መስተዳደሩ ወደ ተባለው ስፍራ አቅንተው እንደሆነፀ ሄደውስ ምን እንደተፈጠሚ ዹገለፀው ነገር ዚለምፀ ማስተባበያም አልሰጠም። ዘግዚት ብሎ ኚሲቲ ዞን ዚቲክቫህ ቀተሰብ አባላት በደሹሰን መልዕክት ትላንት ፕ/ት ሙስጠፌ ቢኪ ላይ ተቃውሞ ገጥሟ቞ው እንደነበርፀ በዚህም ኚፀጥታ ኃይሎቜ ጋር ግጭት እንደነበርፀ በኃላም ሁኔታውን እንደተቆጣጠሩ፣ ዚግድያ ሙኚራ ዚተባለው ግን ትክክል እንዳልሆነ ገልፀዋል። @tikvahethiopia
ППказать все...