597
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
የፕሮግራም ለውጥ
በ2015ዓ.ም የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና(Entrance Exam) ከ600 በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በከንቲባ ጽ/ቤት እውቅና ለመስጠት ለሰኞ ህዳር 10/2016ዓ.ም ፕሮግራም ተይዞ የነበረና በዚህም መሰረት ጥሪ ለተማሪዎች እና ለወላጅ ተላልፎ እንደነበረ ይታወሳል። ሆኖም ዛሬ ማምሻ ላይ ከክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ተደውሎ የእውቅና የፕሮግራም ቀን ለማክሰኞ ህዳር 11/2016ዓ.ም 2 : 00 ሰዓት ላይ የተለወጠ መሆኑን የተገለፀለን ስለሆነ ውድ ተማሪዎቻችን እና ወላጆች ይህንን አውቃችሁ ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ከንቲባ ጽ/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን።
ማስታወቂያ
(ህዳር 5/2016 ዓ.ም) የRemedial ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ምርጫን በተመለከተ
በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ህዳር 12/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡ -
ከታች የተዘረዘሩ ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም የማያስተናግዱ መሆኑን እንገልጻለን።
1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
4. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲ
ትምህርት ሚኒስቴር
የሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ።
የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል።
ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የRemedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡
☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 255 ከ700 ያመጡ
☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 234 ከ700 ያመጡ
☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 218 ከ600 ያመጡ
☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 200 ከ600 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 224 ከ700 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 210 ከ700 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 192 ከ600 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 180 ከ600 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 210 ከ700 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 210 ከ700 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 180 ከ600 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 180 ከ600 ያመጡ
☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 150 ከ500 ያመጡ
☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 150 ከ500 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል።
መረጃውን ትምህርት ሚኒስቴርን ዋቢ በማድረግ ያሰራጨው ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
#የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆኗል
በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለምትከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገልጻለን።
Website: https://result.ethernet.edu.et/
Telegram bot: @moestudentbot
ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ መቀየር የምትፈልጉ ተማሪዎች ነገ ት/ቤት መጥታችሁ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
#ማስታወቂያ
በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፋችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርትቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡
በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ምርጫችሁ ውስጥ በማካተት መመደብ የምትችሉ መሆኑ እናሳውቃለን።
የትምህርት ሚኒስቴር
#ማስታወቂያ
በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፋችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርትቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡
በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ምርጫችሁ ውስጥ በማካተት መመደብ የምትችሉ መሆኑ እናሳውቃለን።
የትምህርት ሚኒስቴር
ውድ ተማሪዎቻችን ከትምህርት ምንስቴር በተገለፀው መሰረት ነገ ዓርብ ጥቅምት 09/2016ዓ.ም ከ3 : 00 ሰዓት ጀምሮ ትምህርት ቤት በመምጣት የዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን እንድታስተካክሉ እናሳስባለን ።
Repost from Don Bosco School G9 (2016)
ለዶን ቦስኮ ካቶሊክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ
እንኳን ለ2016ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!!
ውድ ተማሪዎች እና የተከበራችሁ ወላጆች ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በወረደው መመሪያ መሰረት ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 /2016ዓ.ም እንደሚጀመር የተገለጸ ቢሆንም በት/ቤታችን እየተደረገ ባለው የመማሪያ ክፍሎች እድሳት ምክንያት በዕለቱ ትምህርት የማይጀመር መሆኑን እያሳወቅን ከ11ኛ ክፍል በሰተቀር ማክሰኞ መስከረም 8/2016ዓ.ም ትምህርት የሚጀመር እና በዕለቱ የግማሽ ቀን ት/ት(2 :00 _ 6 :10) የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ፡
1. ውድ ተማሪዎች በዕለቱ የመማሪያ ቁሳቁስ በሟሟላት እና የት/ቤቱ ስርዓት በሚፈቅደው መሰረት የደንብ ልብስ(uniform)በሟሟላት በሰዓቱ ት/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን።
2. የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች የመማሪያ ክፍሎች ዕድሳት ያልተጠናቀቀ ስለሆነ የ11ኛ ክፍል ትምህርት የሚጀምረው ረቡዕ መስከረም 9/2016ዓ. ም መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
🌻ውድ ተማሪዎቻችን እና ወላጆች🌻
እንኳን ለ2016ዓ.ም አዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!! በዓሉ የሰላም፣የደስታ የስኬት እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።
ት/ቤቱ
ውድ የዶንቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት ተማሪዎቻችንና ወላጆች በሙሉ
🌻 እንኳን ለ 2016 ዓ.ም አዲስ ዓመት አደረሳችሁ!!!!🌻
🌻 አዲሱ ዓመት የሰላም ፣ የጤና፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብና የአብሮነት ዘመን ይሁንልን!!!
መልካም አዲስ ዓመት!!!🌻
