ru
Feedback
EB-ACADEMY GU. 1-8 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

EB-ACADEMY GU. 1-8 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

Открыть в Telegram

"Education is the passport to the future, for tomorrow belongs to those who prepare for it today ". Malcolm X...

БПльше
1 962
ППЎпОсчОкО
-424 часа
Нет ЎаММых7 ЎМей
+2130 ЎеМь
АрхОв пПстПв
ለኢቢ  አካዳሚ ጉለሌ ኹ1ኛ-8ኛ ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ዹ2019 ዓ.ም ነባር ምዝገባ  ኹሀምሌ1-6 ብቻ መሆኑን ኹዚህ በፊት ገልፀን ነበር ሆኖም ግን ምዝገባው እስኚ 10/11/2018 ዓ.ም ዚተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ወላጆቜ ልጆቻቜሁን በተያዘለት ጊዜ ገደብ ሳታስመዘግቡ ቀርታቹ ቊታው ቢሞላ ትምህርት ቀቱ ሀላፊነት እንደማይወስድ እናሳስባለን ። 🇪🇹ኢቢ  እካዳሚ ዚስራ አመራር ኮሚ቎   06/11.2018  ዓ. ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ለኢቢ አካዳሚ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ኹዚህ በፊት በተማሪዎቜ እና በ቎ሌግራም በላክነው መልዕክት ዹደሹጃ ተማሪዎቜ ዚሜልማት ፕሮግራም በ05/11/2018 ዓ.ም እንደሆነ አሳውቀን ነበር ሆኖም ግን ዚፕሮግራም ለውጥ ስለተደሚገ ዚሜልማት ፕሮግራም ዚሚካሄደው በሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሜ በቀን 12/11/2018 ዓ.ም እንደሆነ እናሳውቃለን። 🇪🇹ዚኢቢ አካዳሚ ዚስራ አመራር ኮሚ቎ 04/11/2018 ዓ.ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ኹ1ኛ እስኚ 8ኛ ክፍል በ2018 ዓ.ም ዹ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዹተፈተኑ 32 ተማሪዎቜን 100% በማሳለፍ ኹፍተኛ ውጀት አስመዝግቧል። ውድ ወላጆቜና አሳዳጊዎቜ፣ እንኳን ለዚህ ታላቅ ስኬት ደስ አላቜሁ! ለተማሪዎቻቜን፣ ለመምህራን እና ለወላጆቜ ኚልብ እንኳን ደስ አላቜሁፀ ለቀጣይ ጉዞዎቻቜሁም ዹላቀ ስኬት እንመኛለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ          30/10/2018 ዓ.ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

🇪🇹ለኢቢ አካዳሚ ዚካ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ሰርተፍኬት ዚሚሰጥበት ቀን ነገ ሰኞ በቀን 29/10/2018 ዓ.ም እስኚ 5:30 መሆኑን እያሳወቅን ወላጆቜ ነገ ኹ2:30 ጀምሮ በት/ቀት ቅጥር ግቢ ኚልጆቻቜሁ ጋር ተገኝታቜሁ ሰርተፍኬት እድትወስዱ እናሳስባለን ። 👉ማሳሰቢያ:-ዚልጆቻቜሁን ሰርተፍኬት ዚምትወስዱት ዚትምህርት ቀት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ አጠናቃቜሁ መሆኑን ኚወዲሁ እናሳውቃለን ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ዚካ ቅርንጫፍ                              28/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

🇪🇹ለኢቢ አካዳሚ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ በሙሉ ባለፈው ኚት/ቀት በልጆቻቜሁ በላክነው መልዕክት እንዲሁም በ቎ሌግራም ቻናል በላክነው መልዕክት ተለዋጭ ፕሮግራም ካለ በቻናል እናሳውቃለን ባልነው መሰሚት ሰርተፍኬት ዚሚሰጥበት ቀን ነገ ቅዳሜ በቀን 27/10/2018 ዓ.ም መሆኑን እያሳወቅን ወላጆቜ ነገ ኹ2:30 ጀምሮ በት/ቀት ቅጥር ግቢ ኚልጆቻቜሁ ጋር ተገኝታቜሁ ሰርተፍኬት እድትወስዱ እናሳስባለን ። 👉ማሳሰቢያ:-ዚልጆቻቜሁን ሰርተፍኬት ዚምትወስዱት ዚትምህርት ቀት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ አጠናቃቜሁ መሆኑን ኚወዲሁ እናሳስባለን ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ 26/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ኹ1ኛ እስኚ 8ኛ ክፍል በ2018 ዓ.ም ዹ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዹተፈተኑ 133 ተማሪዎቜን 99% በማሳለፍ ኹፍተኛ ውጀት አስመዝግቧል። ውድ ወላጆቜና አሳዳጊዎቜ፣ እንኳን ለዚህ ታላቅ ስኬት ደስ አላቜሁ! ለተማሪዎቻቜን፣ ለመምህራን እና ለወላጆቜ ኚልብ እንኳን ደስ አላቜሁፀ ለቀጣይ ጉዞዎቻቜሁም ዹላቀ ስኬት እንመኛለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ    22/10/2018 ዓ.ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ ኹ1ኛ-8ኛ ወላጆቜ/አሳዳጊዋቜ በሙሉ ዹ2018 ዓ.ም ዹ2ኛው መ/ዓመት ዚማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም መሰሚት ልጆቻቜሁ ለፈተና ዝግጅት እንዲያደርጉ አስፈላጊ ክትትልና ድጋፍ እንድታደርጉ ኚወዲሁ እናሳስባለን ። 👉ማሳሰቢያፊፈተና 6:00 ስለሚያጠናቁ ወላጆቜ በሰዓቱ ተገኝታቹ ልጆቜ እንድትወስዱ እናሳውቃለን።             🇪🇹መልካም ፈተና🇪🇹 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ              12/10/2017 ዓ.ም🇪🇹

በኢቢ አካዳሚ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ዹ8ኛ ክፍል ዚመካኚለኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚሚሰጥ ይሆናል ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ነገ ሐሙስ በትምህርት ቀት ቅጥር ግቢ ኚጠዋቱ 1:30 ሁላቜሁም እንድትገኙ እናሳስባለን። 🇪🇹መልካም ፈተና🇪🇹 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ 10/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

🇪🇹በኢቢ አካዳሚ 1ኛ-8ኛ አንደኛ ደሹጃ ዚስድስተኛ ክፍል ተማሪ ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ። ኹሰኞ 08/10/2018 ዓ.ም እስኚ ሚቡዕ10/10/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ይዘው ዚሚመጡት:- 👉 እርሳስ 👉ላጲስ እና 👉መቅሚጫ እንዲሁም ምሳ቞ውንና ዚመጠጥ ውኃ ብቻ እንደሆነ እያሳወቅን ቁርሳ቞ውን በደንብ እንዲመገቡ በማድሚግ ጠዋት 1:30 ትምህርት ቀት ግቢ እንዲገኙ ምሳ áŠ¥á‰ƒá‰žá‹áŠ• ት/ቀታ቞ው በማስቀመጥ áˆšáˆá‰°áŠ‘á‰ á‰µ ት/ቀት 1:50 መገኘት ስላለባ቞ው በተባለው ሰዓት እንዲደርሱ ያድርጉልን ዘንድ ለውድ ወላጆቜ መልክት እያስተላለፍን á¢ ኚተባለው ሰዓት አርፍደው ለሚገኙ ተማሪዎቜ ሀላፊነቱን ት/ቀቱ እንደማይወስድ እናሳውቃለን።          🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ          7/10/2018 ዓ.ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

🇪🇹 ዚተፈታኞቜ መብትና ግዎታ 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ዹፈተና ደንብና ሥርዓት  አኚባበር እንዲሁም ዚመልስ ወሚቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎቜን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎቜ ላይ ዚመሣተፍ ግዎታ አለበት። 📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ቜግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ተፈታኙ/ኟ ዚሰራበትን ዚመልስ ወሚቀት ለፈታኙ በመስጠት  ዚጥያቄ ወሚቀቱን ይዞ መውጣት ይቜላል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ዹፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ኚመጀመሩ በፊት በፈተና ዚመልስ መስጫ ወሚቀት ላይ ዹግል መለያ መሚጃዎቜን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተኹተል ጜፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ ዚመለያ ቁጥር እና ዚትምህርት አይነት ኮድ)። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ዚራሱን ቜሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 📚 ዚሚሠራባ቞ው ዚጥያቄና ዚመልስ መስጫ ወሚቀቶቜ ለሌሎቜ ተፈታኞቜ ዕይታ ዚተጋለጡ እንዳይሆኑ ሾፍኖ መስራት ይኖርበታል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና ዚመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  ዚኀሌክትሮኒክስ ዕቃዎቜን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ ዹተኹለኹለ ነው ። 📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድሚግ አለበት ። 📚 ይህንን ባለማድሚጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ቜግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ ዚሚያውኩ ሁኔታዎቜ ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ቜግሩን በመግለጜ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይቜላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባኚነ ጊዜ ተጚማሪ ሰዓት አይፈቀድም 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ኚሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ኚመፈታኛው ቊታ በመገኘት መቀመጫ቞ውን መያዝ አለባ቞ው። 📚 ፈተናው ኹተጀመሹ ኹ15 ደቂቃ በኋላ ዚሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሜ መግባት አይፈቀድለትም። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። 📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ኹተጀመሹ ኹ45 ደቂቃ በኋላ ኹፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ ዚመልስ ወሚቀቱን ለፈታኙ አስሚክቊ በጞጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ኹ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀሚው ዚሚጚርስ ተፈታኝ ዹሁሉም ተፈታኞቜ ዚመልስ ወሚቀቶቜ እስኪሰበሰቡና ለፈተናው ዹተፈቀደው ዹጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድሚስ በቊታው ተቀምጩ እንዲቆይ ይደሚጋል። 📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ ዹተቀደደ ወይም ዹተበላሾ ዹፈተና ጥያቄ ጥራዝ ኹገጠመው ወይም ዹተሰጠው ዚመልስ ወሚቀት ዹተበላሾ ኹሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሜበት እጁን አንስቶ በመጠዹቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይቜላል። 🇪🇹ለተፈታኞቜ ዚተፈቀዱ ✅ እርሳስ ✅ ዚተማሪዎቜ ዚደንብ ልብስ (UNIFORM) ✅ ADMISSION CARD ✅ ላጲስ፣ መቅሚጫና ማስመሪያ 🇪🇹ለተፈታኞቜ ዹተኹለኹሉ ❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም ❌ ካልኩሌተር ❌ ዚኀሌክትሮኒክስ ዕቃዎቜን ❌ ሰዓት ❌ በሀኪም ኚታዘዘ ውጪ ዹሆኑ መነጜሮቜ ❌ ዚሚነበቡ ጜሁፎቜ በሙሉ  ðŸ‡ªðŸ‡¹áŠ¢á‰¢ አካዳሚ አንደኛና መካኚለኛ ደሚጃ🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ነገ ቅዳሜ ዹ8ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ብቻ በትምህርት ቀታ቞ው ዹመዝናኛ ፕሮግራም ስላላ቞ው ዝግጅቱ ይሚቆዹው ጠዋት ኹ2:30-6:30 ስለሆነ ኹዚህ ሰዓት በኋላ ሁሉም ተማሪዎቜ ወደዚቀታ቞ው ስለምሄዱ ወላጆቜ ልጆቻቜሁ ቀት መግባታ቞ውን ክትትል እንድታሚጉ እናሳስባለን። 🇪🇹ኢቢ አ/ጉ/ቅ/ ዚት/ት አስተዳደር 05/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ 05/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

በኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ ኹ1ኛ-8ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ዚ6ኛ ክፍል  ኹተማ አቀፍ አንደኛ ደሹጃ መልቀቂያ ፈተና ኹ8-10/18 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዚሚታወቅ ሲሆን እንዲሁም ዹ8ኛ ክፍል ኹተማ አቀፍ ዚመካኚለኛ ደሹጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ኹ11-12/18 ዓ.ም ድሚስ ዚሚሰጥ ይሆናል በዚሁ መሰሚት:- 👉ዚ6ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ወደፈተና ጣቢያ ገብተው ዚጠዋት ፈተና ኚጚሚሱ በኋላ ምሳ቞ውን ለመመገብ ወደራሳ቞ው ት/ቀት በመምጣት ስለሚመገቡ ወላጆቜ ለልጆቻቜሁ እንደተለመደው ምሳ቞ውን ዚመጠጥ ውኃ አሲይዛቹ 1:30 ላይ ት/ቀት ቅጥር ግቢ እንዲገኙ እያሳሰብን በተጚማሪ ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ ተማሪዎቜ ዚዕለቱን ፈተና ኚጚሚሱ በኋላ ወደጊቢ ስለሚመለሱ 9:30 ላይ ልጆቻቜሁን በሰዓቱ እንድትወስዱ። 👉ዚ8ኛ ክፍል ዹፈተናው ቀን ኹ11-12/18 ዓ.ም መሆኑን በድጋሚ እያሳወቅን በዕለቱ ተማሪዎቜ ኹመፈተኛ ጣቢያ ዚጠዋቱን ፈተና ኹተፈተኑ በኋላ ለምሳ ወት/ቀት ስለሚመለሱ ማሳ቞ውንና ዚመጠጥ ውኃ ይዘው መምጣት ይኖርባ቞ዋል እንዲሁም ፈተና በሚጀምሩበት ዕለት ጠዋት 1:30 ሁሉም ተመሪ ት/ቀት ቅጥር ግቢ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ        5/10/2018 ዓ.ም🇪🇹