“ወሶበ አእመረ አውናን ከመ ኢኮነ ሎቱ ዘርዕ ሶበ ቦአ ኀበ ብእሲተ እኁኁ ከዐወ ዘር ዲበ ምድር ወኮነ እኩየ ቅድመ እግዚአእብሔር ወቀተሎ” ዘፍ 38፡10_11 እንዳለው መጽሐፍ አውናን የሚባል ሰው ዘሩ ወደ ትዕማር ማሕጸን ተቀድቶ ትውልድ እንዳይቀጥል ዘሩን በመሬት ላይ በመድፋቱ እግዚአብሔር ቀሰፈው፡፡
ያላገባብ የሰው ዘር ጠብታ የሚያስከትለው መቅሰፍት እግዚአብሔርን ካስቆጣና የሞት ፍዳ ካስከተለ የአማራ ዘር ዘሬ አይደለም፡፡ ካማራ ጋራ የደም ንክኪ የለኝም በማለት
ከኢትዮጵያ ገጸ ምድር እንዲጠፋ እየታረደ ያለቀው የአማራው ደም በኢትዮጵያ ላይ ሚያስከትለው ተከታታይ ፍዳ በደሙ ፍንጣቂ የተበከለው ራሱ ሲኖዶሱ የህይወት መስዋዕት የሚጠይቅም ቢሆን ከፍሎ በንስሀ ራሱን አጽድቶ በምሳሌነቱ ሁሉም የሚጸዳበትን እቅድ ካልዘረጋ በቀር የእልቂቱ ቀጣይነት እርሰዎ በምሳሌነት የጠቀሱት ሲኖዶስ ጾምና ጸሎት የሚገታው ይመስለወታል?
“ኦ ዘታወጽኦ ለሕጻን እምሐቄ ብእሲ ወትፌንዎ ውስተ ከርሠ ብእሲት ወትጠበልሎ በሰፋድል ረቂቅ ወእንዘ ማይ ውእቱ ታረግኦ በጥበብከ ወትነፍህ ላዕሌሁ መንፈሰ ሕይወት ወበ አርባ እለት ትሰይም ዲቤሁ በዘኮነ ከዊኖ” (አትናቴዎስ ቁ 114፡) ማለትም፦በማህጸን ሳለ በ40 ቀኑ ሰባዊ ቅርጹን የጨረስው ጽንሱ ሙሉ ሰውነቱን አሟልቷል፡፡ ሰው መሆንን ጀምሯልና ማስወረድ መግደል ነው” ብላ የምታስተምረውን ቤተ ክርስቲያን እመራለሁ ከሚለው ሲኖዶስ ሌላ ማነው ተጠያቂው?
“ርዑደ ወድንጉጸ ወሕውከ ኩን ላዕለ ምድር” እንዲል፦ ቃኤል ያንድ የአቤልን ደም በማፍሰሱ ተቅበዝባዥ፡ ተሸባሪና ስኩረ መንፈስ ካስደረገው፡ በሚሊዮን የሚቆጠርውን የሰው ደም ካስፈሰሰና ካፋሰሰ ጋራ የተሰለፈው ሲኖዶስ ይቅርና በዓለም ያለውን ሁሉ የአዳም ዘር ተቅበዝባዥ ተሸባሪና አሸባሪ አያደርገውም ብለው ይገምታሉ?
ኢትዮጵያዊት ቤተ ክርስቲያናችን በራሷ ምድር ከዚህ ቀደም በወረሯት ጠላቶቿ በልጆቿ ላይ ከተፈጸመው የከፋ ግድያ ከዚህ በታች በዘረዘርኳቸው በአራት ማንነቶቻቸው ምክንያቶች በመልካም ምሳሌ በጠቀሱት ሲኖዶስ ተባባሪነት ጭፍጨፋ እየተፈጸመባቸው መሆኑን አያውቁምን?
1ኛ፦በኦርቶዶክስ እምነታቸው
2ኛ፦ ባማራነታቸው
3ኛ፦ባመረኛ ተናጋሪነያቸው
4ኛ፦በኢትዮጵያዊነታቸው
ከአማራው ሕብረተ ሰብ ውጭ ያለው ህዝብ በአማራው ላይ ቀጥታ ከተሰነዘረበት ሰይፍ ቢያመልጥም አማራኛ በመናገሩና በኢትዮጵያውነቱ ሙስሊሙም ከመገደል እንዳላመለጠ ሳይሰሙ ሳያውቁ ቀርተው ነው? አማራ ሳይሆን በኦርቶዶክስ ክርስትናው ከአማራው ጋራ ንክኪ ያለው ሁሉ ከግዳያው እንዳላመለጠ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ በትግራይ የሚኖረው ኦርቶዶክሱም በወያኔወች ዘመን በአማራው ላይ ሲፈጸም የነበረው እልቂት በትግሬንቱ ሳይነካው ቢቆይም፡፡ የወያኔ መንግሥት ከፈረሰ በኋላ የደረሰበት እልቂት በኢትዮጵያውነቱና በኦርቶድክስ እምነቱ እስካሁን እያለቀ ነው፡፡ ለዚህስ በተቀዳሚ ሊጠየቅ የሚገባው ማነው?
በሚካሄደው ጭፍጨፋ የኢትዮጵያ ምድር ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በኢትዮጵያውያን ሬሳ ተሸፍኗል፡፡ አፈሩ
በኢትዮጵያውያን ሥጋ ደምና አጥንት ወደ ጭቃነት ተለውጧል፡፡ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚፈሱት ወንዞች ሳያቋርጥ ከሚጎርፈው ኢትዮጵያውያን ደም ጋራ ተቀላቅለዋል፡
፡ ሲኖዶስም ጭምር ህዝቡ የሚጠጣው ውሀ ከወገን ደም ጋራ የተቀላቀለውን ነው፡፡ የሚነፍሰውም አየር ከደም ጋራ የተቀላቀለውን አፈር እየጋፈ የሲኖዶሱን አባል ሁሉ ባፍንጫው እየጋተው ነው፡፡ መጋት ብቻ አይደለም፡፡ ከወገን አጥንትና ሥጋ የተቀላቀለውን አፈር እየጋፈ በሲኖዶሱ ላይ በመበተን ሲኖዶሱን በቁሙ እየቀበረው ነው፡፡
በመንግሥት አልባነት ይኖራል ተብሎ በማይገመት ሕብርተሰብ ላይ ይፈጸማል ተብሎ የማይገመት ይህ ሁሉ ድርብርብ ግፍና በደል በህዝበ ክርስቲያኑና በኢትዮጵያዊው ሁሉ ዜጋ ሲፈጸም ግፈኛውን መንግሥት በመተባበር ያደፈጠውን ሲኖዶስ እኮ ነው ለመከላከል በመታገል ላይ ላለው ፋኖ ምሳሌ ይሁንልህ የሚሉት፡፡
የሚጨፈጨፈው ሕዝበ ክርስቲያን ከደረሰበት መከራ አምላኩ እንዲያወጣው እየተሳለ የሚሰጠውን የስለት ገንዘብ እየበላ በትረ ምንግሥቱን እየተቀባበሉ ከሚፈጁት አረመኔወች ጋራ በመተባበር ያደፈጠውን ሲኖዶስ ለፋኖ “Fanno can benefit from two recent experiences: ብለው ሲጠቅሱ እጽፍ ድርብ በደል እይመስለወትምን? ከዚህ በመቀጠል ስለቱን እየበላ እንደ ድልብ በሬ ሰውነቱን አወፍሮ ከብልጽግ
ጋራ ከሚያናፋው ሲኖዶሱ ይልቅ ፋኖ እጅግ በተሻለ ሞራላዊ እርከን ላይ እንዳለ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡
2ኛ ከሲኖዶሱ አቋም የፋኖ አቋም በእጅጉ የተሻለ ነው፡፡
ከዚህ ቀደም በተለያዩ ዘመናት የወረሩን የተለያዩ ጠላቶች ከሰነዘሩበን የአመጽ ብትር የከፋውን ብትር ከዚህ በታች በምገልጻቸው በአራት ማንነቶቻቸው በኢትዮጵያውያን ላይ ሰንዝሯል፡፡
1ኛ፦በኦርቶዶክስ እምነታቸው
2ኛ፦ ባማራነታቸው
3ኛ፦ባመረኛ ተናጋሪነያቸው
4ኛ፦በኢትዮጵያዊነታቸው
የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም አማራውን ለመስበር አረመኔወች የሚቀባበሉትን ብትር ለመስበር ፋኖ እንደ ዳዊት የጽድቅ ብትሩን አንስቷል፡፡
ጽድቅ የአመጽ ተቃራኒ ነው፡፡ አመጽ በደል ነው፡፡ አመጸኛ በደለኛ ነው፡፡ አመጽ ፈጻሚው በደለኛ መንግሥት ሲሆን፡፡ መንግሥት ብትሩን የሰነዘረበት ተበዳይ ሕዝብ ነው፡
፡ መንግሥት በህዝብ ላይ የሰነዘረው ብትር የአመጽ ብትር ነው፡፡
ከላይ በተዘረዘሩት ምክንያቶች ሕዝብ በተወለደበት ምንደር ምንግሥት እየተከታተለ እየጨፈጨፈው ነው፡፡ አሁን ደግሞ ተሰዶ በሰፈረበት መንደር ጠላትን ለመከላከል የተሰለፈውን ሠራዊት አዘመተበት፡፡ መንግሥት የሠራዊቱን ብትር ወደ አመጻ ብትርነት ቀየረው፡፡ ሠራዊቱንም በራሱ ሕዝብ ላይ በማዝመት አመጸኛ አደረገው፡፡
ዳዊት “አፍቅርከ ጽድቀ ወአመጻ ጸላእከ በትረ ጽድቅ ወበትረ መንግሥትከ” ማለትም፦ ጽድቅን ወደድክ አመጽን ጠላህ ብሎ በገለጸበት ስንመዝነው የአመጽን ብትር በወገን ላይ ያነሳው ማነው? በወገን ላይ የተሰነዘረውን የአመጽ ብትር ለመከላክል ለዘለቄታውም ለምስበር የጽድቅንስ ብትር ያነሳው ማነው? መቼም ዶክተር ዮናስ የፋኖን ብትር ወደ አመጽ የብልጽግናን ብትር ወደ ጽድቅ እንደማይለውጡት እርግጠኛ ነኝ፡፡
ዶክተር ዮናስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን 151ኛ አድርጋ ደምራ የያዘችውን መዝሙረ ዳዊት ከነ ማህደሩ ወርውረው ብልጽግና የተሸከመውን 150ኛ ማህደር አልባ መዝሙረ ዳዊት እንደማይሸከሙ እርግጠኛ ባልሆንም፡ እነ ፈንታሁንና ፋኖ በደረታቸው ከተሸከሙት ከግእዙ 151ኛ ላይ የተቀደሰውን የዳዊትን መፈክር ከዚህ በታች እጠቅሳለሁ፡፡
“ወቀብዐኒ ቅብዐ ቅዱሰ፡፡
አኅውየሰ ሠናያን ወልሂቃን፡፡
ወኢሠምረ ቦሙ እግዚአብሔር ፡፡
ወወጻእኩ ለተእኅዞቱ ለሕዝብ ነኪር፡፡
ወረገመኒ በአማልክቲሁ ርኩሳን፡፡
ወአንሰ ነሣእኩ አእባነ እምውስተ ፈለግ
ወወጸፍክዎ ውስተ ፍጽሙ፡፡
አሜሃ ወድቀ በኃይለ እግዚአብሔር ፡፡
ወአንሰ ነሣእኩ ዘእምላዕሌሁ ሰይፈ፡፡
ወመተርኩ ርእሶ ለጎልያድ፡፡
ወአሰሰልኩ ጽእለተ እምደቂቀ እስራኤልለ”(መዝ 151)
እርሰዎ በመልካም ምሳሌነት የሚጠቅሱልን የብልጽግናን ጎደሎ መዝሙረዳዊት አንግቦ በወገን ላይ የዘመተውን ሲኖዶስ ነው፡፡ ከዚህ ቀጥየ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያኔ በግዕዙ ቋንቋ አፌን ባሰፈታችኝ በዳዊት መፈክር ላይ የተመሠረተውን የነፈንታሁን ዋቄን አቋም ለመግለጽ እሞክራለሁ፡፡
3ኛ የነፈንታሁን ዋቄ አቋም