cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Ibnu Abrar ኢብኑ አብራር ابن أبرار

ይህ ቻናል የኢስላም ጠላቶች እስልምናን ለማጠልሸት በሚል አላማ እስልምና ላይ ለሚያነሱት ጥያቄ አንፃራዊ ምላሽ የሚሰጥበት ነዉ። ሀሳብና አስታየት ያላቹ 👇👇👇👇 @lbnuuabrar 👆👆👆👆 በዚ ማናገር ትችላላቹ

Больше
Рекламные посты
586
Подписчики
Нет данных24 часа
-27 дней
-1230 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ቢደዓን አስመልክቶ በኢብኑ አብራር የተፃፉ ፅሁፎችን ከስር ባሉት ሊንኮች እየገባቹ በቅደም ተከተል ልታነቡ ተጋብዛቹሀል። ከወገንተኝነት እራሳቹን አግልላቹ እያመዛዘናቹ ካነበባችሁ በአላህ ፈቃድ ትጠቀሙበታላችሁ። መልካም ንባብ...... ለጥሩ ቢደዓ ቁርአናዊ ማስረጃ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/361 ኩሉ ቢደዓቲን ደላላ? 👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/362 ለጥሩ ቢደዓ ሀዲሳዊ ማስረጃዎች 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/364 ጥሩ ቢደዓና ሰለፎች 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/379 ጥሩ ቢደዓና ጅምሁር ዑለሞች 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/388 ጥሩ ቢደዓና የምላስ ከልካዮቹ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/IbnuAbra/390
Показать все...
አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱህ፣ውድ የኢስላም ቤተሰቦች ➡️ ይህ የአል–ዒምራን(cmc) የቁርአንና ኢስላማዊ ትምህርት ተቋም official ቻናል ሲሆን፣በዚህ ቻናል ➲ ስለ ተቋሙና በስሩ ስላሉ ቅርንጫፎች የተለያዩ መረጃዎች ይለቀቃሉ ➲ እለታዊና ወቅታዊ ምክሮች ➲ ሳምንታዊና ወርሓዊ የዳዕዋ ፕሮግራሞች የሚለቀቁበትም ይሆናል። ቻናሉ ተደራሽነት እንዲኖረው ለሌሎች በማጋራት የበኩሎን ይወጡ። https://t.me/alimranislamic
Показать все...
መሻኢኾቻችን በዙሪያቸዉ የሚያዩትንና የሚሰሙትን ሁሉ ከአላህና ከመልዕክተኛዉ ጋር የማገናኘት ልማዳቸዉ ይገርመኛል፡፡ በአንድ ወቅት ዳንዩል አወል በመንገድ ሲያልፉ አንዲት እንስት ድምጽ ተሰማ፡፡ ምን እንደተፈጠረ ሲጠይቁ እንዲህ እያንጎራጎረች መሆኑ ተነገራቸዉ፡- አለቅሳለሁ ባይኔ፣ አብሳለሁ በጄ፤ እንደሰማይ ኮከብ ርቆብኝ ወዳጄ፤ መልዕክቱ ነዘራቸዉ፡፡ ወደጦይባ ምድር፣ወደወለላዬ ቀዬ አመሩ፡፡ ለርሳቸዉ ሁሉም ነገር የሚያዜመዉ ስለዘይኑል ዉጁድ (ሶ.ዐ.ወ) ብቻ ነው፡፡ የዩኒቨርሱ ቅኝት ከርሳቸዉ ፍቅርና ትዝታ የወጣ ሊሆን ከቶ አይችልም፡፡ ‹‹እንደ ሰማይ ኮከብ የራቁ›› ወዳጃቸዉን በዚያዉ ቅጽበት አሰቡና ተንሰቅስቀዉ አለቀሱ፡፡ ከአጠገባቸው የነበሩ ሁሉም ለቅሷቸውን ተጋሩ። ግጥሟን ወደዐረብኛ ቀይረዋታል ይባላል፡፡ ካልተሳሳትኩ እንዲህ ትመስለኛለች፡- أبكأ بعيني أمسح بيدي كنجوم السما بعيد محي الدي አላህ ይዘንላቸዉ፡፡ ስለፍቅር ኖረዉ በፍቅር አልፈዋል፡፡ የሙሀባን ለዛ ለትዉልዶች አስሞጥለዋል፡፡ ራምሳን አሰናድተዉ ሚሊዮኖችን ‹‹ዘይኑል ዉጁድ›› እያሰኙ በሶለዋት ወዝዉዘዋል፡፡ ዚክሩ፣ዒልሙ፣አደቡ፣ተርቢያዉ ከዛ ማማ ላይ እንደጉድ ዘንቦ ጎርፉ በአራቱም አቅጣጫ በመፍሰስ ሀገርን አረስርሷል፡፡ በመስኖ እየተጠለፈ ሺዎች ዓሊሞችንና ዐቢዶችን አልምቷል፡፡ ያበሻ ሙስሊም ከዚያ ጣፋጭ የዚክሩ ጅረት፣ከዚያ የሙሀባ ጠጅ እንደየአቅሙ፣በገንቦም፣በጋንም፣በብርጭቆም፣በጅም እየቀዳ ተጎንጭቷል፡- ጠጣዉና ሁሉም የፍቅርዎን ጠጅ የቀመሰለትን ጥንት ሲያደራጅ እንደሰዉነቱ ነዉ መጠጫዊ እንጅ በገንቦም በጋንም በብርጭቆም በጅ ዘግኖም በግድፉ ፉት ያለ እንደልጅ መገን የሀበሻ መሻኢኾች፤ አላህ ይዘንላቸዉ፡፡ https://t.me/hassentaju
Показать все...
የኡስታዝ ፈድሉ ወሲያ 💥°°°°°°°°°°°°°💥 ወሲያ/ኑዛዜ ያልኩት እኔ ነኝ እንጂ እሱ «በኑዛዜ መልክ ነው የተናገርኩት» አላለም፡፡ ወደ ማይቀረው ዓለም ሊሸጋገር ጥቂት ቀናት ብቻ ሲቀሩት የተናገረው በመሆኑ ነው በኑዛዜነት የገለፅኩት፡፡ እስከዛሬ ድረስ ከዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ሳልፅፈው የቆየሁበት ምክንያትም አንዳንድ ወዳጆች አግባብነት ባለው አረዳድ ሳይረዱት ቀርተው ከትግል ሜዳ እንዳይሳነፉ በመስጋት ነበር፡፡ ይህን ፅሑፍ ሰሞኑን ልፅፈው ባሰብኩ ጊዜ ((ሳላውቅ ከንግግሩ/ከሀሳቡ ላይ በመጨመርና በመቀነስ አማናን እንዳላጎል በመስጋት)) ከዛሬ ዓመት በፊት የነገረኝን ወዳጄ ሰሞኑን በድጋሚ ደውዬ ጠይቄዋለሁ፡፡ ♻️ለግንዛቤ ያህል፡👇 •••••••••••••••••••• እንደሚታወቀው አላህ /ሱ.ወ/ ዛኪር ለሆኑ ባሮቹና ለወዳጆቹ ሚፈልገውን ነገር ይገልጥላቸዋል። ከሩቅ-ሚስጥር/ከገይብ ውስጥ ሚፈልገውን ያሳውቃቸዋል። አላህ በእንዲህ መልኩ ሚገልፅላቸው ባሮች ከሶሐቦች ዘመን ጀምሮ እስከዘመናችን ድረስ አልተቋረጡም። ለዚህም ስፍር ቁጥር የሌላቸው ደሊሎች/ማስረጃዎች ሞልተዋል። ለምሳሌ ሰዪዲና ዑመር ኢብኑል-ኸጣብ መዲና ላይ ኹጥባ እያደረጉ ሳለ በኹጥባቸው መሃል ስንት ሺ ኪሎ ሜትር አቋርጦ ወደ ፐርሺያ (ኢራን አካባቢ) ጂሃድ ላይ የነበረውን ሠራዊታቸው አላህ ገልጦላቸው ነበር። ኹጥባቸውን አቋርጠው ደጋግመው «ያ ሳሪየተ-ልጀበል» በማለት ከመዲና ለሠራዊቱ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውንና ሠራዊቱም ከስንትና ስንት ሺ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ ያለአንዳች ሳተላይት ግንኙነት የሰዪዲና ዑመርን ድምፅ ጥርት አድርጎ መስማቱን እና ትዕዛዙንም መቀበሉን ሁላችሁም ምታውቁት ነው። እንዲህ ዓይነት ማሳያዎች በየዘመናቱ በሚታክት መጠን ሞልተውላችኋል። በዘመናችን በአቅራቢያችን ከሚኖሩ ከተመሰከረላቸው ከሻፎች ውስጥ ኡስታዝ ፈድሉ አንዱ እንደነበር ደጋግሜ ሰምቻለሁ። እሱ የተናገራቸው ነገሮች ጠብ ሳይሉ እንደሚከሰቱ ብዙዎች አረጋግጠውልኛል። ❇ወደ ነጥቡ ስገባ:👇 •••••••••••••••••••• ከዛሬ ዓመት ቀደም ብሎ የብልፄ-መጅሊስ አባላት ተመራርጠው ከዋናው ከሙፍቲ ሐጂ ዑመር መጅሊስ ትዩዩ የሆነ ህገ-ወጥ መጅሊስ መስርተው ነበር፡፡ ይህን ህገ-ወጥ መጅሊስ ወንድማችን ሐሰን ኢንጃሞ ‹‹የቤርጎው-መጅሊስ›› የሚል ገላጭ ስያሜ ሰጥቶት እኛም ተቀባብለነው ነበር፡፡ በተመሳሳይ ወቅት ላይ ደግሞ ኡስታዝ ፈድሉ በህመም ላይ ይገኝ ነበር፡፡ የብልፄ-መጅሊስም ዋናውን መጅሊስ ገንጥሎ ገና አልገባም ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ላይ ነበር ኡስታዝ ፈድሉ ወደ አኼራ የተጓዘው፡፡ ኡስታዝ ፈድሉ ወደማይቀረው አኼራ ከመጓዙ ከሁለት ቀናት በፊት አንድ ወዳጄ ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ ለሊቱን ሙሉ ከኡስታዝ ፈድሉ ጋር አሳልፎ ነበር፡፡ የዚያን ለሊት ኡስታዝ ፈድሉ ነቃ ብሎ ሲጫወትና ከእነሱ ጋር ሲሳሳቅ ነበር ያደረው፡፡ ያችን ለሊት ስለተለያዩ ጉዳዮች ሲጨዋወቱ ነበር ያሳለፏት፡፡ በዚያች ለሊት ከተነሱ ጉዳዮች መካከል በወቅቱ ስለነበረው የሙስሊሞች ጉዳይ አንዱ ነበር፡፡ ከላይ እንደገለፅኩላችሁ በወቅቱ ሙፍቲ ሚመሩት ህጋዊው መጅሊስ እያለ ትይዩ ህገ-ወጥ መጅሊስም (የቤርጎ መጅሊስ) በብልፅግና መንግስት ድጋፍ ተቋቁሞ ነበር፡፡ በዚህ ዙሪያ እና በሌሎችም ሙስሊሙን በሚመለከቱ ዙሪያዎች ወዳጄና ጓደኞቹ ከኡስታዝ ፈድሉ ጋር ለሊቱን ሐሳብ ሲለዋወጡ ነበር ያደሩት፡፡ ከዚያም ከሁለት ቀናት በኋላ ኡስታዝ ፈድሉ ወደ አላህ ራሕመት አቀና፡፡ 🔥ኡስታዝ ፈድሉ በወቅቱ ከተናገራቸው ነገሮች ውስጥ የሚከተለው ይገኝበታል፤ ((ንግግሩን ቃል በቃል አይደለም የፃፍኩት)) ፡👇 ••••••••••••••••••••• 👉‹‹እነሱ (የብልፄ ኡስታዞች) በሚያደርጉት ነገር ብዙም አትሸበሩ፤ አትጨነቁ፡፡ ከፊት-ለፊታችን እጅግ አስፈሪ ጊዜ ይመጣል፡፡ እነሱን አላህ ከፊት ያስቀመጣቸው ፊዳእ ሊያደርጋቸው ፈልጎ ነው፡፡ ሱፊያውም ቢሆን ቀልቡ አንድ አይደለም፡፡ ተለያይቷል፡፡ ራቅ ብላችሁ ተመልከቷቸው፡፡ የሸኽ ልጅ ሳይቀር ተቀይሮ ሌላ ሆኗል፡፡ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ ማንን ረግማችሁ ማንን ልትተዉ ነው!? ነገሩ ተደበላልቋል፡፡››👈 •••••••••••••••••••••••• በወቅቱ ይህን ለነገረኝ ወዳጄ .. ‹‹ኡስታዝ ፈድሉ ትግልን ተዉ ማለቱ ነው ዎይ?›› •• ብዬ ጠይቄው ነበር፡፡ እሱም ሲመልስልኝ •• ‹‹እንደዛ ማለቱ አይደለም፡፡ እነሱ በሚፈፅሙት ወንጀል/ግፍ እራሳችሁን ከልክ በላይ አታስጨንቁ፤ ሚጠበቅባችሁን ብቻ እያደረጋችሁ ቆዩ ማለቱ ነው» •• ብሎ ነበር የመለሰልኝ፡፡ እጅግ የሚገርመው ኡስታዝ ፈድሉ አስቀድሞ የተናገራቸው ነገሮች እሱ ወደ አኼራ ካለፈ በኋላ ወዲያው ሆነው አገኘናቸው፡፡ አንዳንድ በሱፊያ ስም የሚነግዱ ሸኾች ወይ ለጥቅማቸው አሊያም ለዘራቸው ሲሉ ጎራ ለውጠው ተመለከትን፡፡ አንዳንድ የትላልቅ መሻኢኽ ልጆች የአባቶቻቸውን መንገድ ረግጠው ከዱርዬው ቡ^ድን ጋር ተቀላቅለው ታዘብን፡፡ ከዚያ በኋላም ቢሆን ይህ በመንግስት ድጋፍ የመጅሊስን በር ሰብሮ የገባው የብልፄ-መጅሊስ ገና አንዲት ዓመቱን እንኳ ሳይደፍን አላህ እርቃኑን አስቀረው፡፡ ሀፍረቱን አከናነበው፡፡ ዕውነተኛ ማንነቱ ተጋለጠ። የገዛ ቲፎዞዎቹና አጨብጫቢዎቹ ሳይቀሩ በእጅጉ ተሳቀቁበት፤ አፈሩበትም፡፡ እንግዲህ በእኔ ምልከታ ከሆነ ኡስታዝ ፈድሉ የተናገረው እስካሁን ድረስ ያየነውን ብቻ ለመግለፅ ፈልጎ አይደለም፡፡ ይህ ገና ጅማሮ ብቻ ይመስለኛል፡፡ ገና ማሟሻ ነው። ከዚህ በእጅጉ የከፋው ጉድ ከፊታችን ተደቅኖ እንደሚጠብቀን እገምታለሁ፡፡ አላህ ነጃ ከሚወጡት ያድርገን! የአላህ ሰፊ ዕዝነትና ምሕረት በኡስታዝ ፈድሉ ላይ ይስፈን! HASA HAMSA
Показать все...
በኒቃቡ አጀንዳ ዙሪያ •••••••••••••••••••• በአሁኑ ወቅት በጉራጌ ዞን ከኒቃብ ጋር በተያያዘ የተነሳው ውዝግብ ከበፊትም የነበረ ቢሆንም በዚህ ሰዓት መጦዙና ይበልጥ የመወዘጋገቡ ሁኔታ ግን ሆን ተብሎ የተደረገ ሰው ሰራሽ ውዝግብ መሆኑን አልጠራጠርም፡፡ ከዚህ አንፃር 3 ዓይነት ሰዎችን እናያለን፡፡ ሁለቱ ደጋፊና ተቃዋሚ በመምሰል ከኒቃቡ በስተጀርባ ያለውን ፖለቲካዊ ግብን ማስፈፀም በአግባቡ እየተወጡ ሲሆን ሦስተኞቹ ሰዎች ግን የፖለቲካ ቁማሩን ሳይረዱ ከግል አመለካከታቸው በመነሳት የሚደግፉ ወይም የሚቃወሙ ናቸው፡፡ ጉዳዩን በቅርበት መከታተል ባልችልም እንደሚታወቀው የጉራጌ ሕዝብ የክልልነትን ጥያቄ በማንሳት ሙስሊም ክርስቲያን ሳይል በአንድነት ተናቦ በሰለጠነ መንገድ እየተቃወመ እንደነበር እናውቃለን፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ሌሎች የክልል ፕሬዝደንቶች በቅርቡ ወልቂጤ ሄደው ስብሰባ እስከማድረግ ደርሰው ነበር፡፡ የስብሰባው ውጤት በአጭሩ ሲገለፅ የክልልነት ጥያቄ መብት ለጉራጌ ሕዝብ እንደማይሰጥ የሚያረዳ መርዶ ነበር፡፡ እንደዚያም ሆኖ ሕዝቡ እስከ አሁን ድረስ ተቃውሞውን እንደቀጠለ እየሰማን ነው፡፡ ((«ለምን ለጉራጌ ሕዝብ የክልልነት መብት ተነፈገ?» ለሚለው ጥያቄ የግል ምልከታዬን በሌላ ፅሑፍ ለመግለፅ እሞክራለሁ)) ታዲያ ይህን ያለሃይማኖት ልዩነት በአንድነትና በአንድ ድምፅ ለህገመንግስታዊ መብቱ የሚታገለውን የጉራጌ ሕዝብ ማርገብ ባለመቻሉ የግዴታ የሆነ ልዩነት ሊፈጥር የሚችልን ችግር ማራገብ እና የሕዝቡን አንድነት መበታተን አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ለዚህ ደግሞ የሃይማኖት ጉዳይ ሁነኛ መሳሪያ ሆኖ ተገኘ፡፡ በመሆኑም ከላይ ከጠቀስኳቸው 3 ዓይነት ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ለመንግስት አጀንዳ የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን የመንግስትን የመከፋፈል አጀንዳ በአግባቡ እየተወጡ ይገኛሉ፡፡ አንደኛዎቹ ወገኖች ለእስልምና እና ለኒቃብ የተቆረቆሩ በመምሰል አጀንዳውን በማራገብ ክፍፍልን ይፈጥራሉ፡፡ ሁለተኛዎቹ ወገኖች ደግሞ ኒቃብን የተቃወሙ በመምሰል ለአንደኛው ወገን ተፃራሪ ምላሽ በመስጠት ይበልጥ ልዩነትን ያሰፋሉ፡፡ ሁለቱም ወገኖች ግን ዓላማቸው አንድ ነው፡፡ አንዱ ከሌላው ተቃራኒ ሳይድ በመቆም ልዩነትን መፍጠርና አጀንዳውን በማጦዝ የሕዝብን አንድነት መበታተን ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ወገኖች እያንዳንዳቸው ከበስተኋላቸው ቁማሩን ያልተረዱ ምስኪን ቲፎዞዎችን በማሰለፍ እርስበርስ ማቃቃርን ይሰራሉ፡፡ ሦስተኛዎቹ ወገኖች እነዚህ ቲፎዞዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሦስተኛዎቹ ወገኖች ከእነዚህ ሁለት ወገኖች ጀርባ ተሰልፈው ቁማሩን ባለመረዳት በየጎራቸው የሁለቱን ወገኖች ሐሳብ በመደገፍ ጉዳዩን ያራግባሉ፡፡ ሲጠቃለል፡ •••••••••• ስስ የሆኑ ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን በማንሳት፣ መስጂድን ወይም ቤተክርስቲያንን በማጥቃት፣ ቁርአንን ወይም መጽሐፍ ቅዱስን በማቃጠል፣ ምዕመናንን በመደብደብና በመግደል ወይም ደግሞ ሌላ የምዕመናንን ስሜት በቀላሉ ሊጎዱ የሚችሉ ትንኮሳዎችን በመፈፀም ሊያነሳሱን እና ለአጀንዳቸው መጠቀሚያነት ሊያውሉን ቢሹ ጠንቀቅ ማለት ይገባናል፡፡ በደመነፍስ ተንደርድሮ ከመሮጥ ይልቅ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ ከበስተጀርባ ያለውን ፖለቲካዊ ሴራና ቁማር መረዳት ይኖርብናል፡፡ ሁሌም በቀደዱልን ቦይ መፍሰስና ወደነዱን አቅጣጫ በጭፍን መነዳት ልክ አይመስለኝም፡፡ በወንድም👉Hamsa Hamsa
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ግርማ ሞገስ እራሱ እንደሳቸው ግርማ ሞገስ የለውም። ምክንያቱም ስጦታው ከ«ዙልጀላሊ-ወልኢክራም» ነውና።
Показать все...
ፈትፍተህ ብታጎርሰው እንኳ እንዳይገባው በአዘል ሒጃብ ተደርጎበት፣ ዓመቱ በመጣ ቁጥር 👉 “የሸዋል ዒድ ሚባል ነገር የለም፣ ቢድዐ ነው” .. ወዘተ .. እያለ ለሚጨቃጨቅ መሕሩም ማገዶ ከምትፈጅ እንዲህ በለው፡👇 . . . . . . . . . . . 👉👉👉 «እንኳን!»
Показать все...
አላህ ማለት የቤቶችህን በሮች ዘጋግተህ ልታምፀዉ መሆኑን እያወቀ በበሩ በታች በኩል ባለ ቀዳዳ እንድትተነፍስ አየር የሚልክልህ እጅግ በጣም ሩህሩህና አዛኝ ጌታ ነዉ።❤
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.