1 740
Подписчики
Нет данных24 часа
+17 дней
-630 день
Архив постов
በ3ኛ ዙር የወጣቶች ይስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ላይ ለሚሳተፉ አሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ተጀመረ::
የአሰልጣኞች ስልጠናው በዘንድሮ አመት በአስተዳደሩ ለሚሰጠው የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ 3ኛ ዙር ፕሮግራም ላይ ለወጣቶች ስልጠና ለሚሰጡ አሰልጣኝ መምህራን በዛሬው እለት መሰጠት ተጀምሯል::
የ3ኛ ዙር ፕሮግራሙ በስራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በቅርቡ በኮሌጁ ለሚጀምረው የወጣቶች ስልጠና በኮሌጁ ToT ላላቸው አሰልጣኝ መምህራን በተከለሰው የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲሁም የስራ አፈላለግ ስልጠና ላይ የሪፍሬሽመንት ስልጠና እየተሰጠ ሲሆን ይህም የ3ኛው ዙር ስልጠና ፕሮግራም ቅድመ ዝግጅት አንዱ አካል እንደሆነም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 17/2017 ዓ.ም
በአስተዳደሩ ከአራቱም ክላስተሮች ለተወጣጡ ወጣቶች በ Sanitation Concrete Slab ላይ ስልጠና ተሰጠ::
ስልጠናው በጤና ቢሮ አማካኝነት ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ 20 ሰልጣኞች በMarketing Based Sanitation Concrete Slab Training የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞችም ለሰባት ተከታታይ ቀናት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው አጠናቀዋል::
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች የእውቅና ሰርተፊኬቱን ያበረከቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በእለቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሰልጣኞች እዚህ በኮሌጁ የወሰዱትን ስልጠና መሰረት እድርገው በየአካባቢያቸው የሚስተዋለውን የመፀዳጃ ቤት ችግሮችን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባቸውም ተናግረዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 12/2017 ዓ.ም
#ዜና | የፀሀይ ታዳሸ ሀይልን ለወጣቶች የስራ አድል ፈጠራ ያለው አበርክቶት ከፍተኛ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተባለ።
ADRA ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጅት 5.2 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የፀሀይ ሀይል ኤሌትሪክ መሳሪያ ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለገሠ። በ2001 ወደ ስራ የገባው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከደረጃ 1-5 በማንፋክቸሪንግ ኤሌክትሪክ አውቶ እና ሰርቬይንግን ጨምሮ በ9 የትምህርትና የስልጠና ዲፓርትመንቶች እያሰለጠነ ይገኛል።
ኮሌጁ ADRA ኢትዮጵያ ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጀት ጋር በመተባበርና በፀሀይ የኤሌትሪከ ሀይል ማምረቻ ተከላ እና ጥገና ዙሪያ ወጣቶችን እያሰለጠነ ይገኛል። ለሁነቱ የተግባር መማሪያ የሚያስፈልግ 5.2 ኪሎ ዋት የሚያመነጨ የፀሀይ ሀይል ማመንጫ መሳርያ ለኮሌጁ ለግሶል።
በኩነቱ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ስራ ከህሎት አና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል አና የቴክኒክ ሞያ ኤጀንሲ ሀላፊ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ ስራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥርት ወጣቶችን ስልጠናውን እንዲወስዱ እየተደረገ ይገኛሉ ብለዋል።በተለይም የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ከማድረግ ጎን ለጎን ወጣቶችን በማደራጀት የስራ እድል ተጠቃሚ አንዲሆኑ ያደርጋል ሲሉ ገልፀዋል።
የADRA ኢትዮጵያ የፕሮጀከት ዳይሬክተር ዶክተር ዘሪሁን ሀዋኖ በበኩላቸው ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ባለፉት 2 አመታት 90 ወጣቶችን በዘርፉ ማሰልጠናቸውን ገልፀው እርዳታው ሰልጣኞች በዘረፉ በቂ እውቀት እንዲጨብጡ እንዲሁም የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ ያደረጋል ብለዋል።
#DireTv አማርኛ የካቲት 4/2017
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የተቋሙን የ6ወር አፈፃፀም እና የEASE ፕሮጀክትን እስካሁን ተደረሰበትን አፈፃፀም ሪፖርት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸውም እንደ ተቋም ከዚህ አመት ጀምሮ በርካታ ዘርፈብዙ ስራዎችን ለማከናወን የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅዶችን በመንደፍ ወደተግበራ መገባቱን አስታውሰው ይህ ውጤታማ እንዲሆንም የኮሌጁን ማህበረሰብ የነቃ ተሳትፎን ከመቼው ጊዜ በላይ የሚጠይቅ ወቅት በመሆኑ ሁሉም አካል በዚህ አግባብ ተነሳሽነት በማሳይት ተልኮን መፈፅም እንደሚገባም ገልፀዋል::
በእለቱ በተካሄደው መድረክ የኮሌጁን የ2017 በጀት አመት የ6ወር አፈፃፀም ያቀረቡት የኮሌጁ የእቅድና በጀት ስራ ክፍል ሀላፊ አቶ አለማየሁ ብርሃኑ ሲሆኑ በቀረበው ሪፖርትም ኮሌጁ የበጀት አመቱን ትግበራን ከጀመረበት የዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት አንስቶ በ6ወር ውስጥ የነበረውን አጠቃላይ ንቅስቃሴ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን አክለውም ኮሌጁ እስከ በጀት አመቱ መጠናቀቂያ ድረስ ለትግበራ በእቅድ የያዛቸውን ተግባራት ለመድረኩ ተሳታፊዎች አመላክተዋል::
በመቀጠል የEASE ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ከገባበት ጊዜ አንስቶ የተከናወኑ ስራዎችን አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀምም የፕሮጀክቱን ባለሙያዎች ከማዋቀርና የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ ከማቋቋም አንስቶ የፕሮጀክቱ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በልምድ ልውውጥና ስልጠናዎች የማብቃት እንዲሁም 65 ለሚሆኑ የተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል::
በተጨማሪም በቀረበው ሪፖርት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አመራሮችና ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀየር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱም በሪፖርቱ ከቀረቡት ነጥቦች የሚጠቀሱ ናቸው::
በመጨረሻም የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለመፈፀም በእቅዱ ላይ የተመላከት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተቋሙ የሪኢኖቬሽን ስራዎች ፣ የአሰልጥኞች ስልጠና፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች፣ የሴቶችን መደገፍና ማብቃት እንዲሁ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠዎችን ተግባራዊ ለማድረግ መያዙ ከብዙ ጥቂቱ መሆኑን በቀረበው እቅድ ተመላክቷል::
የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣይ እቅድን መነሻ በማድረግ ለቀጣይ ትግባራት ውጤታማነት የሚረዱ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦች በስፋት አንስተው ውይይት ተደርጎበት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 1/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የመደበኛ ስራ 6ወር አፈፃፀምና የEASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈጻጸምን ለኮሌጁ የቦርድ አባላት አቀረበ፡፡
የተቋሙን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የEASE ፕሮጀክት አፈጻጸም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆኑ በዚህም ኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ ጀምሮ በ6ወሩ ውስጥ የነበረውን የእቅድ አፈፃፀምና የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም የተገኙ ውጤቶችን የገለፁ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊሰሩ በእቅድ የተያዙ ስራዎችን ለቦርድ አባላት አቅርበዋል፡:
በመድረኩ የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ሀሳብ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል::
በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በኮሌጁ እቅድ አፈፃፀም እንዲሁም በፕሮጀክቱ ትግበራ አፈጻጸም ላይ ማጠቃለያ እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያም ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥር 30/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈፃፀምና የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ::
በዛሬው እለት በተካሄደው መድረክ የEASE ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ እስከ እሁን የነበረውን የአፈፃፅም ትግበራ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድን መነሻ በማድረግ ከፕሮጀክቱ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት ጋር የውይይት መድረክ በሀረር ተካሂዷል::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው እንደገልፁት ምንም እንኳን የEASE ፕሮጀክትን ወደ ትግበራ ከገባ አጭር ጊዜ ቢሆንም እስካሁን በደረስንበት አፈፃፀም መሰረት ወቅቱን ጠብቆ ከባለድርሻ አካላት ጋር መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ይህን መድረክ ተዘጋጅቷል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም በመድረኩ በሚቀርበው የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከኢንዱስትሪው አኳያ ማካተት ሚገባንና የተዘነጉ ጉዳዮች ካሉ ከመድረኩ በሚገኘው ግብዓት መሰረት እቅዱን ለማሻሻል ተቋማችን ዝግጁ እንደሆነም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት ሲነደፍ እንደ ሀገር ማስመዝገብ የተፈለገው ውጤት እንዳለ ጠቅሰው በዚህም መሰረት Result Framework በሚኒስቴር መ/ቤቱ ፀድቆ ሲመጣ በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት የኛ መመዘኛ እሱ ይሆናልም ብለዋል::
በፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ወ/ሮ ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀምም የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ ከማቋቋም ጀምሮ የፕሮጀክቱ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በልምድ ልውውጥና ስልጠናዎች የማብቃት እንዲሁም 65 ለሚሆኑ የተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል::
በተጨማሪም በቀረበው ሪፖርት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አመራሮችና ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀየር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱም በሪፖርቱ ከቀረቡት ነጥቦች ይገኙበታል::
በመቀጠልም የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለመፈፀም በእቅዱ ላይ የተመላከት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተቋሙ የሪኢኖቬሽን ስራዎች ፣ የአሰልጥኞች ስልጠና፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች እንዲሁ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠዎችን ተግባራዊ ለማድረግ መያዙ ከብዙ ጥቂቱ መሆኑን በቀረበው እቅድ ተመላክቷል::
የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የፕሮጀክቱ አፈፃፀምና የቀጣይ እቅድን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የሚረዱ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት የተካሄበት ሲሆን ኮሌጁን ጨምሮ የኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላትም ለቀጣይ የየድርሻቸውን አሳይመንቶችን በመውሰድ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥር 24/2017 ዓ.ም
ሀረር
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
