ru
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Открыть в Telegram
1 740
Подписчики
Нет данных24 часа
+17 дней
-630 день
Архив постов
photo content
+9

ከደቡብ ኮርያ የመጣ የቮለንተር ቡድን በኮሌጁ ሙያዊ ልምድ ልውውጥ አካሄደ:: ቡድኑ ከWitness of christ Church ጋር በመተባበር በሚያደርገው ድጋፍ አማካኝነት በኮሌጁ ተገኝቶ ልምድ ልውውጥ ያደረ ሲሆን በዚህም ከኮሌጁ ጋር በትብብር ለመስራት በሚችሉበት አግባብ ዙሪያ ከኮሌጁ ሀላፊዎች ጋር ተወያይተዋል:: በተጨማሪም የቮለንተር ቡድኑ በWitness of christ Church አጫጭር ስልጠና ተማሪዎች አማካኝነት በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን የተመለከቱ ሲሆን የኮሌጁን የት/ትና ስልጠና ወርክ ሾፖችንም ተዘዋዉረው ተመልክተዋል:: ይህ ከደቡብ ኮርያ የመጣው ቡድን በውስጡ ከተለያዩ ቴክኒካል ሞያዎች የተወጣጡ ባለሙያዎችን ያቀፈ ሲሆን በቀጣይ ከሙያዊ ድጋፍ ጀምሮ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን ቆይታም አድርገዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሰኔ 20/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ፑል አመራር አባላት ስለ ኤች አይ ቪ/ኤድስ ሜንስትሪምንግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከጤና ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች አማካኝነት የአስተዳደሩን ወቅታዊ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ሁኔታ ግንዛቤ ለመስጠት የሚረዳ እንዲሁም በተቋሙ የኤድስ ፈንድ ለማስጀመር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለኮሌጁ ፑል አመራር አባላት አካሂዷል። በመድረኩ ለኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት መንስኤም ሆነ የሚያስከትለው ተፅዕኖ ዘርፈ-ብዙ ከመሆኑ አንፃር ቫይረሱን ለመከላከልና ኤድስ የሚያስከትላቸውን አሉታዊ ተጽዕኖዎች የመቀነሱና የመከላከሉ ሥራ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ የኮሌጁ ማህበረሰብም የበኩሉን መውጣት እንደሚገባው በመድረኩ ተግልፇል:: በቀጣይም ስለ ኤድስ ፈንድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ በቂ ግንዛቤን በመፍጠር የኤድስ ፈንድ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ መገባት እንዳለበት በመድረኩ የተገለፀ ሲሆን ከኤድስ ፈንድ ጋር ተያያዥ የሆኑ ሥራዎች በቶሎ እንዲከናወኑ የሚያስችሉ ውሳኔዎች እንዲሰጡም በውይይቱ ወቅት ተጠቁሟል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሰኔ 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

photo content
+9

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተተገበረ የሚገኘው የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት በ 2016 ዓ.ም የተሰሩ ስራዎችና የተገኙ ልምዶችን የሚያሳይ ሪፖርት ለባለ ድርሻ አካላት አቀረበ:: የፕሮጀቱ አመታዊ ሪፖርት በፕሮጀክቱ ማናጀር አማካኝነት ለመድረኩ የቀረበ ሲሆን በዚህም የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት በዓመቱ ያከናወናቸው ተግባራቶች በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን ፕሮጀክቱ ያስገኛቸው ጥሩ ልምዶችን ጨምሮ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም ጠቅለል ተደርገው ቀርበውበታል:: በተጨማሪም በመድረኩ የቀረበው አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በSolar Pv installation and maintenance እያሰለጠናቸው የሚገኙ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ሰልጥኞቹ የስራ ላይ ልምድ የሚያገኙበትን እድል በማመቻቸቱ ረግድ የተሰሩ ስራዎች በመድረኩ ቀርበዋል:: በዚህም ሰልጣኞች ስራ እየሰሩ ልምድ የሚያዳብሩበን መንገድ ከጤና ቢሮ፣ከትምህርት ቢሮ እና ከኢነርጂ ቢሮ ጋር በመነጋገር የገጠር ሶላር ስራ ላይ የጥገና ስራ እንዲሰሩ መንገድ የተመቻችላቸው ሲሆን ከፊልድ ስራ ሲመለሱ የብቃት ምዘና(COC) በመውሰድ ወደ ስራው ዓለም እንደሚሰማሩ ይጠበቃል:: በፕሮጀክቱ እቅድ መሰረት 40% በቅጥር 60% ደግሞ የራስ ስራ በመፍጠር ወደ ስራ ይሰማራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለዚህም ይሆን ዘንድ ከፐብሊክ ሰርቪስ በተላከ ባለሞያ አማክኝነት በተደረገው ገለፃ መሰረት እንደ አገርም አዲስ የሆነውን የሶላር ባለሙያ JOB BOX በማዘጋጀት የመጀመሪያ ድራፍት ዶክመንት በዛሬው እለት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ የተተቸ ሲሆን በቀጣይም በተሰጠው ግብረ መልስ መሰረት ማስተካከያ ተደርጎበት እንደሚፀድቅ ተገልፇል:: በመጨረሻም በቀጣይ ለሚገቡት ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የምልመላ መስፈርት ላይ በመድረኩ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግና መስፈርቱንም በማሻሻል መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሰኔ 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

እንኳን አደረሳችሁ!! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛ ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል::☪️ #ኢድ
እንኳን አደረሳችሁ!! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛ  ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል::☪️ #ኢድ_ሙባረክ

በአስተዳደሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሞያ ስልጠና ኮሌጆች የሰነቁትን ራዕይ እንዲያሳኩ አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ። ======================== የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እያደረገ ባለው የመስክ ምልከታው በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣልያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን የ2016 በጀት አመት ማጠቃለያ እቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ አድረገ። ቋሚ ኮሚቴው በዋናነት የኮሌጁን የበጀት አመቱ እቅድ አፈፃፀም፣ ከዚህ በፊት ቋሚ ኮሚቴው ባደረገው የመስክ ምልከታው ኮሌጁን በተመለከተ ለሰጠው ግብረ_መልስ የተሰጠ ምላሽ እና በምክር ቤት  የውክልና አሰጣጥ መድረኮች ከህዝብ ለተነሱ  ጥያቄዎች ኮሌጁ ምላሽ የሰጠበትን አግባብ እንዲሁም የፕሮጀክት አፈፃፀምና ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድ ያለውን አፈፃፀም የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት ገምግሟል። የኮሌጁ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን አፈፃፀሙን በመገምገም በጥንካሬ የሚታዩ እንዲሁም ያሉ ውስንነቶችን በመለየት በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በሚቻልበት አግባብ በጋራ ለመስራት የሚረዳ ሰፋ ያለ ውይይትም አድርገዋል። በዚሁ አግባብ በአፈፃፀም ሂደት ኮሌጁ ራዕዩን ለማሳካት እያደረገ  በሚገኘው ጥረት እያጋጠሙ ያሉትን ተግዳሮቶች የኮሌጁ አመራሮች ለቋሚ ኮሚቴው ያብራሩ ሲሆን ችግሮቹን ለመፍታትም ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጠይቀዋል። በውይይቱ ማጠቃለያም ኮሌጁ በበጀት አመቱ ያስመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው አባላት የገለፁ ሲሆን ከዚህም ባለፈ በተለይም በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ችግር ፈቺና ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ስልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑን በማበረታታት በቀጣይም ዘርፉ የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖረው በአስተዳደሩ ከሚገኙ የሚመለከታቸው ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት ጋር ከእቅድ እስከ ተግባር አፈፃፀም ወጥነት ባለው መልኩ ተቀናጅቶ በጋራ መስራት እንደሚገባና ለተግባራዊነቱም ቋሚ ኮሚቴው ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል  የሚያደርግ መሆኑን የቋሚ  ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ ተናግረዋል።   የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም አክለውም በአስተዳደሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሞያ ስልጠና ኮሌጆች የሰነቁትን ራዕይ እንዲያሳኩ እና ለአስተዳደሩ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ሊያደርጉላቸው እንደሚገባም አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው አባላት በኮሌጁ የሚገኙ የስልጠና ዎርክሾፖች እና ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ምንጭ - Dire Dawa Adiminstration Council DDCP ሰኔ 6/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በተሳተፉበት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊ ሆኑ:: የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስል
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በተሳተፉበት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊ ሆኑ:: የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በ2016 የበጀት ዓመት በኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን ዘርፍ በተደረገው የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና ቴክኖሎጂ ውድድር ኮሌጃችንን ወክለው የተወዳደሩ አሰልጣኝ መምህራን በሁለቱም ዘርፍ ውድድር አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ በመውጣት የሰርተፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት ከስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ እና ጥሪ ከተደረገላቸው የቢሮ ኃላፊዎች ሽልማታቸውን ተረክበዋል። ሁሌም በሁሉም ዘርፍ ቀዳሚ የሆነው ኮሌጃችንም በውድድሩ ተሳትፈው አሸናፊ ለሆኑት ተቋማችንን ላስጠሩ አሰልጥኝ መምህራኖች እንኳን ደስ ያላቹ እንኳን ደስ አለን ይላል። 🏆🏆🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ግንቦት 29/2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚማሩ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::  የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር በጋራ የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ በመቀጠል ያልፉትን 2ቀናት በሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ሰፋ ያለ ግንዛቤን የመፍጠር ስራ ሰርቷል:: የግንዛቤ ማስጨበጫው የተሰጠው በት/ቤቱ ለሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆን መድረኩ በኦሮምኛ ቋንቋ ትምህታቸውን የሚከታተሉትንም ያማከለና በሁለት መድረክ የተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክም ነበር:: የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ለተማሪዎቹ የሰጡት የኮሌጃችን ዋና ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ በመድረኩ ተማሪዎቹ ስለ ቴክኒክና ሞያ ዘርፍ ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት የሚቀርፍና የቴክኒክና ሞያ ነባራዊ ሁኔታን ቁልጭ አርጎ በሚያሳይ መልኩ በመተንተን ዘርፉ ለተማሪዎቹ የሚያስገኘውን ምቹ አጋጣሚ ሰፋ ባለ ማብራሪያ የሰጧቸው ሲሆን ተማሪዎች የነገ መዳረሻችውን ከዚሁ ትኩረት ሰተው በጥንቃቄ መምረጥ እንደሚገባቸውም ምክር ለግሰዋል:: በተጨማሪም በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ መሰረት እነዚህ ተማርዎች 11 እና 12 ላይ የቴክኒክና ሞያ ትምህትና ስልጠናዎችንም አያይዘው የሚሰለጥኑ በመሆኑ በዘርፉ የሚሰጡትን የስልጠና አይነቶች በግልፅ እንዲረዷቸው በማድረግ ከፍላጎታቸው ጋር የሚጣጣመውን የስልጠና አይነት ለይተው ምርጫቸው እንዲያደርጉ የሚረዳቸውን ግንዛቤ መስጠት ትችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ግንቦት 29/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ፅዱ የስራ አካባቢን እንፍጠር በሚል በኮሌጁና አካባቢው ተማሪዎችን ያሳተፈ የፅዳት ዘመቻ በዛሬው እለት አካሂድዋል::